• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ዲፕሎማቶች የስደተኞችን ሻንጣ ዘረፉ!

February 9, 2015 07:21 am by Editor Leave a Comment

ከአንድ አመት በፊት የሳውዲ አረቢያ መንግስት በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ ሃገር ዜጎች  ግዛቱን  ለቀው እንዲወጡ ያስቀመጠው የግዜ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጅዳ እና ሪያድ ከተማ ወደሚገኙ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ መጉረፋቸው ይታወሳል።

eth emb saudi
የቆንስላው ጽ/ቤት ዲፕሎማቶችና ሠራተኞች

በወቅቱ ከነበረው ስርዓት አልበኝነት ህይወታቸውን ለመታደግ አቅሙ የቻለ ጎረምሳ ልብሶቹን በሻንጣ አጭቆ እግር አውጭኝ ሲል አይን ያልገለጹ ህጻናት ልጆቻቸውን በወጉ መሰብሰብ ያልቻሉ እናቶች ለክፉ ቀን ትሆነኛለች ብለው ገዝተው ያስቀመጡጥን ወርቅ እና የተለያዩ ጌጣጌጦቻቸውን የያዘች አነስተኛ ሻንጣ አንጠልጥለው ከቀማኞች ይታደገናል ወዳሉት በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ቅጠር ግቢ በማቅናት ለተውሰኑ ቀናቶች በመጠለል ሻንጣዎቻቸው በካርጎ ጭነት እንደሚላክ ቃል ተገብቶላቸው ብጣሽ  ጨርቅ እንኳን ሳይዙ  ባዶ እጃቸውን ወደ ሃገር ቤት  ማቅናታቸው ይነገራል።

በወቅቱ  በዚህ መልክ ወደ ቆንስላ ጽ/ቤት ቅጠር ግቢ የሚመጣውን  ወገን  ሃብትና ንበት በሃላፊነት ተረክቦ ወደ ሃገር መላክ የሚችል አካል ባለመኖሩ በጅዳ እና አካባቢው የሚኖሩ ታዋቂ ግለሰቦች  ከዲፕሎማቱ ጋር በመተባበር “ወገን ለወገን” የሚል አንድ ኮሚቴ በማዋቀር ኢትዮጵያኑ በሰላም ሃገር እንዲገቡ ሰፊ የማስተባበር ዘመቻ ይካሄድ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ይገልጻሉ። ይህ ኮሚቴ ወደ ሀገር ተመላሽ ወገኖችን ስምና አድራሻ እየመዝገበ በአደራ ተቀብሎ ከሚሰበስበው ንብረት ባሻገር በተለያዩ ግዜያት በአሰሪዎቻቸው ተደብድበው ተድፍረውና ደሞዛቸው ተነጥቆ ወደ ቆንስላው ቅጠር ግቢ የሚመጡ እህቶች ጉዳይ ተድበስብሶና በደልን ተሸክመው ወደ ሃገር መሸኝት እንደሌለባቸው በማመን የቆንስላው ባለስልጣናት በዚህ ዙሪያ አንድ አይነት ሚና መጫወት እንደሚገባቸው ያደርግ በነበረው ግፊት ኮሚቴው ከተሰጠው ሃላፊነትና ተግባር አፈንግጦል በሚል ቅሬታ በኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎችና የአሰሪ እና ሰራተኛ ኤጀንሲ ደላሎች በተፈጠረው አለመግባባት  የማህበሩ መስራቾች  በቆንስላው ዲፕሎማቶች ትዕዛዝ ወደ ቆንስላው ግቢ እንዳይገቡ በመታገዳቸው የወገን ለወገን  ህልውና ገና ከጅምሩ በአደራ የተረከበውን ንብረት ሜዳ ላይ በትኖ ከስመ።

በዛኔው መንገደኛ እና ሻንጣ በተለያዩበት የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት  የጎዞ መስተንግዶ አሳዛኝ ድራማ በተፈጠረው ስርአት አልበኝነት የተጠቀሱትን ሻንጣዎች ከአደጋ ለመከላከል ባሉበት ሁኔታ ሸራ ለብሰው ቀሩ።  እህቶች ለአመታት ይደርስባቸው የነበረውን  እንደወላፈን የሚፋጅ የአረብ ወይዛዝርት ቁጣ እና ግልምጫ ተቋቁመው ባገኙት ደሞዝ  የሸመቱት ወርቅና የተለያየ ጌጣጌጦችን የያዙ ሻንጣዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎ አገልግሎት አቆመ በሚል ሰንካላ ምክንያት ወደ ሃገር እንዳይልኩ በቆንስላው ዲፕሎማቶች እገዳ ተጣለበት። የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ቅጠር ግቢ ተቆልሎ የሚታየው ይህ  ሻንጣ ለወራት  ዝናብ እና ፀሃይ እይተፈራረቀበት ባለቤት አልባ ሆኖ ድፍን አመት ካስቆጠረ በኋላ  ሰሞኑን  በሻንጣዎቹ ላይ አስነዋሪና አሳዛኝ ተግባር መፈፀሙ ተስማ። በተለይ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ግቢ ውስጥ ከተደረደሩ ሻንጣዎች ውስጥ የአባዛኛው ቁልፍ መሰበሩን የሚናገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ሻንጣዎቹ ላይ የተፈፀመው ዘረፋ የዲፕሎማቱ እጅ እንዳለበት በመረጃ አስደገፈው ይናገራሉ። ድርጅታዊ ጉባኤ የምትለዋን ቃል እንደ  መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ማታ ማታ ያለወትሯቸው ቆንስላው ግቢ  የሚያድሩ  ከዲፕሎማቱ ጋር የቀርብ ግንኙነት ያላቸው የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ አባላት ግንባር ቀደም የዚህ ወንጀል ተዋናይ ሳይሆኑ እንደማይቀር ይጠረጠራል። እስክሁን ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ የተለያዩ ሻንጣዎች ቆልፍ እየተሰበረ በጥንቃቄ ብርበራ እንደተካሄደበት በተጨባጭ፡ ማረጋገጥ ተችሏል።

ይህ በዚህ እንዳለ  ሰሞኑን የሰማያዊ  “ማንዋል” ፓስፖርት የአገልግሎት ዘመን ማብቃቱን ተከትሎ ፓስፖርት ለማስለወጥና ለማሳደስ  የጅዳ ቆንስላ  ጽ/ቤት በተከስተው የባለጉዳዩች መጨናነቅ ዲፕሎማቱ  ህጋዊ በሆነ መንገድ ወደ ቆንስላ ጽ/ቤት ለሚገባው ተስተናጋጅ የ3 ወር እና ከዚያ በላይ ቀጠሮ እየተሰጠው ሲሸኝ  በሌላ አቅጣጫ ለሚስተናገድ  ባለጉዳይ ከ5 ቀን ባልበለጠ ግዜ ውስጥ ሁሉም ነገር እንዲሚያልቅለት የሚናገሩ ባለጉዳዩች ዲፕሎማቱ  እየሰጡ ባለው  በሙስና የነቀዘ አገልግሎት ክፉኛ መማረራቸውን ይናገራሉ፡፡

በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልጋዩች በሚል ሽፋን ከዲፕሎማቱ ጋር ጥብቅ ቁረኝት ያላቸው የዚህ ወንጀል ተባባሪ ደላሎች እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል።  በዚህ ዙሪያ ለማነጋገር በቅርቡ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ሃላፊ ሆነው የተሾሙትን አምባሳደር ውበሸትንም  ሆነ ዲፕሎማት ሼሪፍ ኬሬን በአካል  ለማገኘት ያደረኩት ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።

(Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የላኩት – ፎቶ በቆንስላ ቅጠር ግቢ የተቆለለው ሻንጣ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule