• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያ ሀገራችን የሰብአዊ መብት ተሟጋች ልጇን አጣች

February 28, 2016 12:08 am by Editor 1 Comment

በሰብአዊ መብት ተሟጋችነታቸው፣ ለሰላምና ለዲሞክራሲ መስፈን ታጋይነታቸው የሚታወቁት ዶ/ር ማይገነት ሽፈራው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ዶ/ር ማይገነት ሽፈራው ስለ ሰላም የሰበኩ ያስተማሩና የጻፉ ቀንዲል ኢትዮጵያዊ ነበሩ። ድህነትና በሽታ፣ ርሐብና ስደት፣ አምባገነንትና ጦርነት እያለ የኢትዮጵያ ሴቶች መብት መከበር፣ የሰብአዊ መብት መረጋገጥ፣ ዲሞክራሲና ሰላምን ማስፈን አይቻልም በሚል እምነታቸው በጽናት ታግለው ያታገሉ የዘመናችን ጣይቱ ነበሩ። የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ የመናገር የመጻፍ የመሰብሰብ የመደራጀትና በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞን የማሰማት መሠረታዊ መብቶች እውን እንዲሆኑ እንዲሁም ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብአዊ መብት መከበር፣ ለሃገራችን ሰላም፣ የሃገራችን የፖለቲካ ችግር በዲሞክራሲ፣ በመቻቻልና በሰከነ ውይይት እንዲፈታ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እድሜያቸውን ሙሉ ታግለው ያታገሉ እናት፣ እህትና ወገን ነበሩ።

ዶ/ር ማይገነትሽፈራው (Ethiopian Women for peace and development (EWPD)) እ.ኤ.አ. በ1991 ዓም ከመሥራቾቹ አንዷ በመሆን ለ21 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን በ2012 ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ ባደረገውም ተከታታይ ስብሰባ የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከልን (Center for Rights of Ethiopian Women (CREW)) ሲመሠረት ሀሳቡን ከመጠንሰስ ጀምሮ በምሥረታው ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካደረጉትና ከመሥራቾቹ አንዷ ናቸው።ከተመሠረተም በኋላበ ተደጋጋሚ በመመረጥ ድርጅቱን በብቃት የመሩ የመሪነት ችሎታቸውን በተግባር ያስመሰከሩ ናቸው።

ይህ አዲስ የተወለደው የሴቶች ማዕከል የተነሳበት ዓላማና የሚታገልላቸው ጥያቄዎች የኢትዮጵያ ሴቶች የሰላምና የልማት ድርጅት (EWPD) ለ21 ዓመታት ሲታገሉላቸው ከነበሩት ዓላማዎች ጋር አንድ በመሆናቸው ተመሳሳይ ድርጅት ለየብቻ ሆኖ ኃይልና ጉልበትን ከመከፋፈል በአንድ ላይ ሆኖ ያለውን ጉልበት አሰባስቦ ጠንክሮ ለውጤት በመሥራት የተሻለና ጠንካራ የሴቶች ድርጅት በመሆን ለኢትዮጵያ ሴቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማህበራዊ ፍትህ፣ለሰብአዊ መብት መከበር፣ ለዲሞክራሲ መብት መስፈን እየታገሉ የሴቶችን በራስ የመተማመን አቅም ለማጎልበት እጅለ እጅ ተያይዞ መሥራት የወቅቱ ቁልፍ መፍትሔ መሆኑን በማመን ለ21 ዓመት በጽናት የቆዬውን የኢትዮጵያ ሴቶች የሰላምና የልማት ድርጅት የሠራቸውን ሕዝባዊ ሥራዎችንና ያካበተውን የትግል ልምድ ይዞ ኢትዮጵያ ሀገራችን የሰብአዊ መብት የሚከበርባት፣ የሕግ የበላይነት የሚያብባት፣ ሰላም የሰፈነባትና የሴቶች ስብእናቸው የሚከበርባት አገር እንድትሆን በጋራ ቆሞ ለመሥራት ከኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማዕከል ጋር አንድ በመሆን ሲዋሃድ ዶ/ር ማይገነት ሽፈራው ውህደቱን እውን እንዲሆን ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል::

ዶ/ር ማይገነት ሽፈራው የኢትዮጵያ ሴቶች ጠንካራ ተቋም እንዲኖራቸውና በሃገራቸው የፖለቲካ፣ የኤኮኖሚና የማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲኖራቸው በነበራቸው ከፍተኛ አላማና ምኞት ንቃተ ህሊናቸውን ለማሳደግ የመጀመሪያው እርምጃ ሴቶች ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄዱ እንዲማሩ የሚያበረታቱና የሚያስተምሩ ኃላፊነት የሚሰማቸው አብነታቸው ብዙዎችን የሚያነሳሳ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሴቶችን ለመሪነት ማብቃት ለነገ የማይባል ግዴታችንና ኃላፊነታችን ነው ብለው የሚያምኑ ለዚህም ሳያሰልሱ ያስተማሩ ምርጥ መምህር ነበሩ።

የኢትዮጵያ ሴቶች የመብት ማእዕከል (CREW) መሪውን በማጣቱ የተሰማውን ከፍተኛ ኃዘን እየገለጸ ዶ/ር ማይገነት በተውሉንን መልካም ሥራዎቻቸውንና በጎ ሀሳባቸው እየተጽናናን የደከሙበትንና የታገሉለትን አላማና አርማ ቀጣዩ ትውልድ በማንሳት የነገይቱ ኢትዮጵያ የሃገራችን የፖለቲካ ችግር በዲሞክራሲና በሰከነ ውይይት ተፈትቶ የሴቶች መብት የሚሰፍንባት፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብአዊ መብት የሚከበርበት፣ የመልካም አስተዳደር መሠረት የሚጥልበት እንደሚሆን ጥርጥር አይኖረንም።

“ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከመሬት” የማይቀርበት የህይወት ጉዞ ነውና ለዶ/ር ማይገነት የሰላም እረፍት እንዲሆንላቸው እየጸለይን፤ እንዲሁም ለባለቤታቸው፣ለልጆቻቸው፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብርታትና መጽናናትን እንመኛለን።

የኢትዮጵያሴቶችየመብትማእዕከል (CREW)

የዶ/ር ማይገነት ሽፈራው የቀብር ስነስርአት ፕሮግራም የሚካሄደው ሰኞ ፌብሩዋሪ 29, 2016 ነው፡፡ የቤተክርስትያን ስነስርአት የሚፈዐመው፡ ከ 10፡00 ኤ.ም – 1፡00 ፒ.ኤም
ቦታው፡ ቅዱስ ገብርኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን
አድራሻ፡ 2601 Evarts St. N.E Washington DC 20018

የቀብር አገልግሎት የሚከናወነው፡ 2፡00ፒ.ኤም

የቀብር ቦታ አድራሻ፡ 9500 Riggs RD Adelphi, MD,20783

ከቀብር ስነስርአቱ ፍፃሜ በኋላ የምሳ ፕሮግራም በቅዱስ ገብርኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ተዘጋጅቷል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Yikir says

    March 29, 2016 10:51 pm at 10:51 pm

    Toomoosgen ale weyane.Bekaliti biretabiret dimitsu. Lekas Kaliti yeweyane “oshutiz” oshutiz magoriyaw new. BEKALITI ANEGAGER LESEW MEBIT YEMITAGELU SEWOCH SIMOTU GINBOT 19 new.BENEGATAW GINBOT 20 malet new.”

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule