• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ እንደ ናቡከደነፆር

April 13, 2014 07:29 pm by Editor 2 Comments

በአንድ ወቅት የዓለም ገናና ንጉስ የነበረው የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነፆር ለ43 ዓመታት ባቢሎንን ገዝቷል፤ በስተሰሜን ሶሪያ በምዕራብ በፍልስጤም እስከ ግብፅ ግዛቱን አስፋፍቷል፡፡ ይህ ንጉስ ህጎችን ከመቀፅበት ይደነግጋል፣ ይለውጣል፡፡ ለእሱ ስርዓት ተገዥ ያልሆኑትን ያስራል፣ ይገርፋል፡፡ ንጉስ ናቡከድነፆር በጣም የሚፈራ እና ኃይለኛ ንጉስ ቢሆንም ከመውደቅ ግን አልዳነም፡፡ ለማንኛውም የዚህ ንጉስ ታሪክና የሀገራችን መንግስት ስርዓት ብዙ የሚያመሳስላቸው ነገሮች ስላሉ እንዲህ አቅርቤዋለሁ፡፡

ንጉስ ናቡከድነፆር በዘመኑ በጣም የሚፈራ እና የማይደፈር እንደመሆኑ መጠን የፈለገውን የማድረግ መብት ነበረው፡፡ በዚህም መሰረት ነው የሌለባቸውንና መልክ መልከኞችን ጥበብና ዕውቀት የሞላባቸውን በብልሀት ዳኞችንና አስተዋዮች የሆኑትን በንጉሱም ቤት መቆም የሚችሉ ብላቴናዎችን በእስራኤል ልጆች ከነገስታቱ እና ከመሳፍንቱ ዘር ይመጣ ዘንድ ለጃንደራቦቹ አለቃ ለአስፋኔዝ ነገድ ዳንኤል 1,3,4፤ የተመረጡትም ወጣቶች ዳንኤል፣ አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ ነበሩ፡፡ በእርግጥም እነዚህ ወጣቶች ጤናማ አዕምሮና አካል እንዲሁም ጥልቅ ማስተዋል ጥበብና ዕውቀት ነበራቸው::

ንጉስ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች ከባቢሎናውያን ስርዓት ጋር እንዲስማሙ ለማድረግ ንጉስ የከላዳውያንንም ትምህርት ቋንቋ ያስተምራቸው ዘንድ ጃንደረቦቹን አዘዘ፡ ፡ ንጉሱም በእርሱ ዘንድ እንዲቆሙ ስለሚፈልግ ከንጉስ መጠጥና መብል በየዕለቱ እንዲወስድላቸው አዘዘ፡፡ ስማቸውንም ቀየረ፡፡ ንጉስ የእነዚህን ወጣቶች ስም የቀየረው በራሱ መስመር ለሱ እንዲስማማው እና የእሱ ተገዥ እንዲሆኑ ለማሳወቅ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ ስማቸውንም ቢቀይረው የዓላማ ፅናታቸውን ግን መቀየር አልቻለም ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ናቡከደነፆር የግዛቱን አንድነት ለማጠናከር በማሰብ በዱር ሜዳ አንድ የወርቅ ምስል አቆመ፡፡ የምስሉ ርዝመት 60 ክንድ (27 ሜትር) ወርዱ 6 ክንድ (2.7 ሜትር) ነበር፡፡ ንጉስ በዚሁ ምስል የምረቃ ሰነ ስርዓት አዘጋጅቶ መሳፍንቱንና ሽማምንቶቹን፣ አገር ገዥዎቹን፣ አማካሪዎቹን፣ የህግ አዋቂዎችን ሰብስቦ ላሰራው የወርቅ ምስል የእምቢልታና የዘፈን ድምፅ በሰሙ ጊዜ ተደፍተው እንዲሰግዱ፣ ካልሰገዱ ደግሞ በሚነደው የእቶን እሳት ውስጥ እንደሚጣሉ ተነገራቸው፡ ፡ ሙዚቃው መሰማት ሲጀምር ያ ሁሉ ባለስልጣን ተደፍቶ ሲሰግድ እነዚያ አስተዋይና ጥበበኞች ወጣቶች ግን ቀጥ ብለው ቆሙ፤ የወጣቶችን አለመስገድ ያዩ የንጉሱ ታማኞች ንጉሱ ዘንድ ሄደው ወጣቶቹን ታማኝነት በማጉደልና ሀገርን በመክዳት ወንጀል እንዲያቃጥላቻ ጠየቁ፤ ንጉሱም ላሰራው ምስል እንዲሰግዱ፣ እምቢ ካሉ ግን እቶን እሳት ውስጥ እንደሚጥሏቸው ቢያስጠነቅቃቸውም አንሰግድም ብለው ከአቋማቸው ሳይነቃነቁ ቀሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ይህ አምባገነን የነበረ ንጉስ የፈቀደውን የሚገድል፣ የሚያስር፣ የሚመታ እና የሚያዋርድ እንዲሁም ለእሱ ተገዥ የሆኑትን ደግሞ ከፍከፍ የሚያደርግ ነበርና እነዚህን ሶስት ወጣቶች ከዚያ ከሚቀለቀል እቶን እሳት ውስጥ ከተቷቸው፡፡

ኢህአዴግ እንደ ናቡከደነፆር

በአሁኑ ሰዓት ኢህአዴግ እየሰራ ያለው ይህንኑ የንጉስ የናቡከደነፆር አይነት ስራ ነው፡፡ በፈለገው ሰዓትና ቀን ህገ መንግስቱን ይሽራል፣ ይለውጣል፡ ፡ ማሰር መምታትና መግደል ካሰኘው ያደርገዋል፡፡ እሱ በሚጠራው ሰልፍና ስብሰባ ላይ በግዳጅ እያስወጣ ፓርቲው ህብረትና አንድነት እንዲሁም ሙሉ ኃይል ያለው ያስመስላል፡፡ በትምህርት ውጤታቸው የላቁ ልጆችን በየትምህርት ቤቱ እየዞረ አባል እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡ የ‹‹ኢህአዴግዝም››ንም እምነት ይከተሉ ዘንድ በወጣት ሊግና ፎርም አደረጃጀት ይጠይቋቸዋል፡፡ ከዚያም በየስብሰባው ሚሪንዳና ቦንቦሊኖ እያደለ በብሔር ብሔረሰቦች ዘፈን እያስጨፈረ ስለ ደርግ ጭፍጨፊነት እና ስለ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጭራቅነት እየሰበካቸው እሱን እሱን ብቻ እንዲያመልኩ ያደርጋቸዋል፡፡ ለዚሁ የኢህአዴግዝም እምነት ጠንካራ አምላኪ ከሆንክ ደግሞ ያለ ውድድር ስራ መግባቱ፣ ሹመትና እድገቱ፣ ቤትና መኪናው፣ 10ኛ ክፍልን ሳትጨርስ አመራር ቦታ ላይ መቆሙ፣ በቃ ምን አለፋህ… ሁሉ በእጅህ ነው፡፡

ኢህአዴግ ከድሮው ንጉስ ናቡከደነፆር የሚለየው ሳይሰራ ሊያሰግድ የሚጥር ግትር መሆኑ ነው፡፡ ማሰገዱ በጎ ባይሆንም የድሮው ንጉስ ያሰግድ የነበረው ለህዝብ የሚታይ ነገርን ሰርቶ ነበር፡፡ ኢህአዴግ ግን እንዲሰገድለት የሚፈልገው በማይታየው፣ በሌለውና ባልተሰራው ስራው ነው፡፡ በአጭሩ ያላዩት እንዲያምኑት የሚፈልግ የዘመኑ ነብይ ለመሆን ይሞክራል፡ ፡ ትራንስፎርሜሽን፣ አብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ ልማታዊ መንግስትና ሌሎችም…. የሚጨበጡ የሚያዙ አይደሉም፡፡ እነዚህ የማይጨበጡ ነገሮችን ግን ከምንም በላይ አጋንኖ ያቀርባቸዋል፡፡ በእነዚህ ስራዎች፣ ለእነዚህ ‹‹መሃንዲስ›› ለተባሉት ካድሬና መሪዎቹ እንድንሰግድለት ይጠብቃል፡፡

በአጠቃላይ ልክ በድሮ ዘመን የነበረው ናቡከደነፆር ያደርግ እንደነበረው ለኢህአዴግና ለመሪዎቹ ለሰገደ ሁሉ ከሚገባው በላይ ከአገርና ከህዝብ ጥቅም ይሰጠዋል፡፡ ይዘርፋል ማለት ይቀላል፡፡ ኢህአዴግ ሳይቀር ያወጣውን ህግ ጠቅሶ ‹‹መብቴ ነው!›› እያለ፣ ለመስገድ አሻፈረኝ ያለ ግን እንደ ሶስቱ ወጣቶች የዘመኑን የእሳት ነበልባል ይቀምሳል፡፡ ወደ እስር ቤት ይወረወራል፡፡ ይደበደባል፡፡ ከስራ ይባረራል፡፡

ወይንሸት ንጉሴ
ወይንሸት ንጉሴ

ነገር ግን አንተ እውነተኛው የኢትዮጵያ ልጅ ከራስህ ጥቅም ይልቅ የሀገርህን ጥቅም የምታስቀድም ከሆነ እና ከምግብ ይልቅ ነፃነት፣ ከብሔር ይልቅ ኢትዮጵያዊነትን፣ ከውሸት ይልቅ እውነትን መርጠህ ይህን መንግስት ከተቃወምክ ወይም ከተቸህ የኢህአዴግ አምላኪዎች በገባህበት እየገቡ ዛቻና ማስፈራሪያ፣ ስድብና ዱላ መለያህ ያደርጉልሀል፡፡ ይህ ነገር ግን አቋምህን ሊያስቀይረው አለመቻሉን ሲያውቁ ደግሞ ደስ የምትል ውሸት አቀናብረው ፊልም ይሰሩ እና አሸባሪ፣ ከዳተኛ፣ የሀገር ጠላት ብለው ንጉስ ናቡከደነፆር እሳት ውስጥ እንደከተታቸው ሶስቱ ወጣቶች ሁሉ ኢህአዴግም ይወረውርሃል፡፡ ከደበርከውም ያስወግድሃል፡፡ ነገር ግን ኢህአዴግ ዛሬም አናንያ፣ አዛርያ እና ሚሳኤልን የመሳሰሉ ወጣቶች እንዳሉ ያወቀ አልመሰለኝም፡፡

በእርግጥ ከ97ቱ ምርጫ በኋላ ወጣቱ ሀገራዊ ጉዳይ አያገባኝም ብሎ እርፍ ብሎ ቢታየውም ዛሬ ደግሞ እንደ አዲስ መታሰርም መደብደብም ሆነ መሞት የማይፈሩ፣ ባመኑበት እንጂ ለማያምኑበት ነገር የማይገዙና የማይንበረከኩ፣ ጥቅማ ጥቅም የማያታልላቸው፣ ለመብታቸው የሚታገሉ ለሀገራቸው ክብር የሚቆረቆሩ እና ከራሳቸው ጥቅም ይልቅ የሀገራቸውን ጥቅም የሚያስቀድሙ ወጣቶች ማቆጥቆጥ ጀምረዋል፤ በቅለዋል፡፡ እናም ኢህአዴግ ሆይ! እንደ ንጉስ ናቡከደነፆር ከመሆንህ በፊት መንገድህን አስተካክል! (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. asdf says

    April 15, 2014 02:22 pm at 2:22 pm

    I like your thoughts!!!

    Reply
  2. Netsanet says

    April 16, 2014 06:49 pm at 6:49 pm

    Well said; better to stay poor than being woyane’s servant. Trading country for money/personal advantage is morally wrong; Historical mistake especially for young people. Woyane will be gone; country and people always live forever. Lemialf Ken, Cadre Mehon, Tizibt New Tirfu. Better to die with dignity.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule