• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣል

July 8, 2014 12:01 am by Editor Leave a Comment

የአቶ ጌታቸው ረዳን የአማራ ነገድ ጋዜጠኞች እና ልሂቃኖች አማራውን በማዳከም የወያኔ መጋዝ ይዘው በግዝገዛው ሴራ ላይ እየተሳተፉ ናቸው። “ኢሳት” ጭምር። ጌታቸው ረዳ የሚለውን ጽሁፍ ሳነብ፣ ምንም እንኳ ከስብሰባው አዘጋጅ ከሞረሽ ወገኔ መግለጫ ይወጣል ብዬ ስጠብቅ እስካሁን ባላይም፣ በኢሳት ሴራ በጣም ማዘኔንና፣ የሞረሽ ወገኔን ደግሞ “እሰጥ – አገባ” ውስጥ አለመግባት የድርጅቱን በራስ መተማመን ያሳየኝ ክስተት መሆኑን መግለጽ እወዳለሁ።

ሞረሽ ስብሰባውን ሲጠራ በማስታወቂያው፡-

በኢትዮጵያና በአማራው ነገድ ላይ እየተፈጸመ ስላለው ጥፋት እና ጥፋቱን ለመከላከል አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ማድረግ ስላለበት ተግባር ለመመካከር የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል።

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥልቅ እውቀት ያላቸውን ሶስት ምሁራንን ፕሮፌሰር ጌታቸው ሓይሌን፣ ዶክተር ሃይሌ ላሬቦ እና አቶ ጌታቸው ረዳን በአስረጅነት ጋብዘናል። ይልና በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲገኝ ይጋብዛል።

በሞረሽ ወገኔ የግብዣ ጥሪ ላይ እንደምናየው፣ ኢትዮጵያዊውን ሁሉ ለውይይት ሲጋብዝ ቅሬታም ካለ ቅሬታን በመድረኩ ላይ ተገኝቶ እንደማሰማት፣ ለምን ሰው ወደ ስብሰባው እንዳይሄድ ኢሳት በዚያው ሰዓት እና በዚያው ቀን ስብሰባ መጥራት መረጠ? ብሎ መጠየቅ ከጀሌነት ራስን ነጻ ማውጣት ብቻ ሳይሆን፤ ሰው ለኢሳት ለሚያደርገው የገንዘብ አስተዋጽኦ የመጠየቅ መብቱም ነው ብዬ አምናለሁ።

ሞረሽ ወገኔ በጁላይ 27 “ቅሬታን ስለማሳወቅ” ብሎ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቦርድ በጻፈው ደብዳቤ እንዲህ ይላል።

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በ፴፩ኛው የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርት ዝግጅት ለሰኔ ፳፮ ቀን ፪ሺህ፮ ዓ.ም. (July 3, 2014) ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራቱን ኢሣት እያወቀ፣ ማስታወቂያውንም በራሱ ዝግጅት ከሦስት ጊዜ በላይ ለሕዝብ አሰምቶ እያለ፣ የኢሣትን ዓመታዊ የገንዘብ ማሰባሰቢ ዝግጅት ድሮ ያደርግ የነበረበትን ቀን ትቶ፣ ሞረሽ-ወገኔ ሕዝባዊ ስብሰባ በሚያዘጋጅበት ቀን እና ሰዓት ለማድረግ መወሰኑ፣ “ጠብያለሽ በዳቦ” ሆኖ ተሰምቶናል። ይህም የኢትዮጵያውያን ተቋሞች እንዲጠናከሩ እንጂ፣ እንዳለፉት ሁሉ ተቋሞች እንዳይፈርሱ ዓላማቸው አድርገው የተነሱትን እንደሞረሽ ያሉ ድርጅቶችን የጠነከረ አቋም የሚፈታተን ሆኖ ተሰምቶናል።

ስለሆነም፦

1. ኢሣት በሣንሆዜ ሊያደርገው ያሰበውን ዝግጅት ቀኑን ለሌላ ቀን እንዲደርግ አጥብቀን አበክረን እንጠይቃለን።

2. በዐማራው ላይ የሚፈጸሙ ግፎች እና በደሎችን ኢሣት ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ባላነስ መልኩ የዜና ሽፋን እንዲሰጠው ከማክበር ጋር እናሳስባለን።

ይህ አቤቱታ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቦርድ ይድረስ እንጂ ቦርዱ ለቅሬታ ማሳወቂያው መልስ ከመስጠት ይልቅ የሞረሽን ስብሰባ ለማደናቀፍ ካቀደው ሴራው አልተቆጠበም። ለምን?

ኢሳት በኢትዮጵያኖች የገንዘብ እርዳታና ተሳትፎ የተቋቋመ እስከሆነ ድረስ ኢትዮጵያኖችን በጋራና በእኩልነት የሚያሳትፍ ከመሆን አልፎ ወገን በመለየት ለአንዱ አቀንቃኝ ለሌላው እንቅፋት መሆን አልነበረበትም። ኢሳት የራሱ ባለቤትነት የሌለው፤ ግንቦት 7 እና የአክራሪ ብሄረተኞች በውስጥ ሆነው በበላይነት የሚያሽከረክሩት ነው እየተባለ ለሚታማው ማስተማመኛ ካልሆነ በቀር በሞረሽ ስብሰባ ላይ ያሳየው ተንኮልና ሴራ ሌላ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም።

ኢሳት ከአማራው ህዝብ የሚፈልገው ገንዘቡን እንጂ የአማራውን ህዝብ አይደለም የሚባለውን ወሬ ከዚህ በፊት እንዳልታመነ ወሬ ሰምተን ከማለፍ ይልቅ ቆመን ኢሳትን ከመጠየቅና ከመጠራጠር አልፈን የሳንሆዜው የኢሳት ድርጊት ለወሬው ማስተማመኛ ከመሆን ያለፈ ለኢሳት የፈየደለት ነገር ያለ አይመስለኝም። በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ኢትዮጵያዊነት በአንድ መድረክ ተገናኝቶ እንዳይነጋገር  እንቅፋት እየሆኑ ከኢትዮጵያኖች በተለይም ከአማሮች የገንዘብ እርዳታ መጠየቅ “ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል” እንደሚሉት፣ አይን ያወጣ የሰው ንቀት ይሆናል። የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ደግሞ አማራው ኢሳትን በገንዘብ እስከረዳ ድረስ፣ በኢሳት ቴሌቪዥን ጣቢያ በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን መፈናቀል፣ መገደልና መታሰር ወዘተ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ እኩል ትኩረት ሰጦ ማስተናገድ ይገባል። “ከአማራው ህዝብ ገንዘቡን ብቻ ነው የምንፈልገው” የሚለው ፈሊጥ በሂደት የኢሳትን ማንነት መፈታተኑ እንደማይቀር ኢሳትና ደጋፊዎቹ ሊያስቡበት ይገባል። “እዩኝ! እዩኝ! ያለች ደብቁኝ! ደብቁኝ ትላለች” እንደሚባለው፣ ዛሬ መድረኩን ይዘናል ተብሎ የአንድን ህዝብ መፈናቀል፣ መገደልና መታሰር ህዝብ እንዳያውቅ የሚደረግ ተንኮልና ሴራ ነገ ያስጠይቃል።

tasewanete@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule