• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣል

July 8, 2014 12:01 am by Editor Leave a Comment

የአቶ ጌታቸው ረዳን የአማራ ነገድ ጋዜጠኞች እና ልሂቃኖች አማራውን በማዳከም የወያኔ መጋዝ ይዘው በግዝገዛው ሴራ ላይ እየተሳተፉ ናቸው። “ኢሳት” ጭምር። ጌታቸው ረዳ የሚለውን ጽሁፍ ሳነብ፣ ምንም እንኳ ከስብሰባው አዘጋጅ ከሞረሽ ወገኔ መግለጫ ይወጣል ብዬ ስጠብቅ እስካሁን ባላይም፣ በኢሳት ሴራ በጣም ማዘኔንና፣ የሞረሽ ወገኔን ደግሞ “እሰጥ – አገባ” ውስጥ አለመግባት የድርጅቱን በራስ መተማመን ያሳየኝ ክስተት መሆኑን መግለጽ እወዳለሁ።

ሞረሽ ስብሰባውን ሲጠራ በማስታወቂያው፡-

በኢትዮጵያና በአማራው ነገድ ላይ እየተፈጸመ ስላለው ጥፋት እና ጥፋቱን ለመከላከል አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ማድረግ ስላለበት ተግባር ለመመካከር የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል።

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥልቅ እውቀት ያላቸውን ሶስት ምሁራንን ፕሮፌሰር ጌታቸው ሓይሌን፣ ዶክተር ሃይሌ ላሬቦ እና አቶ ጌታቸው ረዳን በአስረጅነት ጋብዘናል። ይልና በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲገኝ ይጋብዛል።

በሞረሽ ወገኔ የግብዣ ጥሪ ላይ እንደምናየው፣ ኢትዮጵያዊውን ሁሉ ለውይይት ሲጋብዝ ቅሬታም ካለ ቅሬታን በመድረኩ ላይ ተገኝቶ እንደማሰማት፣ ለምን ሰው ወደ ስብሰባው እንዳይሄድ ኢሳት በዚያው ሰዓት እና በዚያው ቀን ስብሰባ መጥራት መረጠ? ብሎ መጠየቅ ከጀሌነት ራስን ነጻ ማውጣት ብቻ ሳይሆን፤ ሰው ለኢሳት ለሚያደርገው የገንዘብ አስተዋጽኦ የመጠየቅ መብቱም ነው ብዬ አምናለሁ።

ሞረሽ ወገኔ በጁላይ 27 “ቅሬታን ስለማሳወቅ” ብሎ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቦርድ በጻፈው ደብዳቤ እንዲህ ይላል።

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በ፴፩ኛው የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርት ዝግጅት ለሰኔ ፳፮ ቀን ፪ሺህ፮ ዓ.ም. (July 3, 2014) ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራቱን ኢሣት እያወቀ፣ ማስታወቂያውንም በራሱ ዝግጅት ከሦስት ጊዜ በላይ ለሕዝብ አሰምቶ እያለ፣ የኢሣትን ዓመታዊ የገንዘብ ማሰባሰቢ ዝግጅት ድሮ ያደርግ የነበረበትን ቀን ትቶ፣ ሞረሽ-ወገኔ ሕዝባዊ ስብሰባ በሚያዘጋጅበት ቀን እና ሰዓት ለማድረግ መወሰኑ፣ “ጠብያለሽ በዳቦ” ሆኖ ተሰምቶናል። ይህም የኢትዮጵያውያን ተቋሞች እንዲጠናከሩ እንጂ፣ እንዳለፉት ሁሉ ተቋሞች እንዳይፈርሱ ዓላማቸው አድርገው የተነሱትን እንደሞረሽ ያሉ ድርጅቶችን የጠነከረ አቋም የሚፈታተን ሆኖ ተሰምቶናል።

ስለሆነም፦

1. ኢሣት በሣንሆዜ ሊያደርገው ያሰበውን ዝግጅት ቀኑን ለሌላ ቀን እንዲደርግ አጥብቀን አበክረን እንጠይቃለን።

2. በዐማራው ላይ የሚፈጸሙ ግፎች እና በደሎችን ኢሣት ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ባላነስ መልኩ የዜና ሽፋን እንዲሰጠው ከማክበር ጋር እናሳስባለን።

ይህ አቤቱታ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቦርድ ይድረስ እንጂ ቦርዱ ለቅሬታ ማሳወቂያው መልስ ከመስጠት ይልቅ የሞረሽን ስብሰባ ለማደናቀፍ ካቀደው ሴራው አልተቆጠበም። ለምን?

ኢሳት በኢትዮጵያኖች የገንዘብ እርዳታና ተሳትፎ የተቋቋመ እስከሆነ ድረስ ኢትዮጵያኖችን በጋራና በእኩልነት የሚያሳትፍ ከመሆን አልፎ ወገን በመለየት ለአንዱ አቀንቃኝ ለሌላው እንቅፋት መሆን አልነበረበትም። ኢሳት የራሱ ባለቤትነት የሌለው፤ ግንቦት 7 እና የአክራሪ ብሄረተኞች በውስጥ ሆነው በበላይነት የሚያሽከረክሩት ነው እየተባለ ለሚታማው ማስተማመኛ ካልሆነ በቀር በሞረሽ ስብሰባ ላይ ያሳየው ተንኮልና ሴራ ሌላ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም።

ኢሳት ከአማራው ህዝብ የሚፈልገው ገንዘቡን እንጂ የአማራውን ህዝብ አይደለም የሚባለውን ወሬ ከዚህ በፊት እንዳልታመነ ወሬ ሰምተን ከማለፍ ይልቅ ቆመን ኢሳትን ከመጠየቅና ከመጠራጠር አልፈን የሳንሆዜው የኢሳት ድርጊት ለወሬው ማስተማመኛ ከመሆን ያለፈ ለኢሳት የፈየደለት ነገር ያለ አይመስለኝም። በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ኢትዮጵያዊነት በአንድ መድረክ ተገናኝቶ እንዳይነጋገር  እንቅፋት እየሆኑ ከኢትዮጵያኖች በተለይም ከአማሮች የገንዘብ እርዳታ መጠየቅ “ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል” እንደሚሉት፣ አይን ያወጣ የሰው ንቀት ይሆናል። የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ደግሞ አማራው ኢሳትን በገንዘብ እስከረዳ ድረስ፣ በኢሳት ቴሌቪዥን ጣቢያ በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን መፈናቀል፣ መገደልና መታሰር ወዘተ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ እኩል ትኩረት ሰጦ ማስተናገድ ይገባል። “ከአማራው ህዝብ ገንዘቡን ብቻ ነው የምንፈልገው” የሚለው ፈሊጥ በሂደት የኢሳትን ማንነት መፈታተኑ እንደማይቀር ኢሳትና ደጋፊዎቹ ሊያስቡበት ይገባል። “እዩኝ! እዩኝ! ያለች ደብቁኝ! ደብቁኝ ትላለች” እንደሚባለው፣ ዛሬ መድረኩን ይዘናል ተብሎ የአንድን ህዝብ መፈናቀል፣ መገደልና መታሰር ህዝብ እንዳያውቅ የሚደረግ ተንኮልና ሴራ ነገ ያስጠይቃል።

tasewanete@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule