• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣል

July 8, 2014 12:01 am by Editor Leave a Comment

የአቶ ጌታቸው ረዳን የአማራ ነገድ ጋዜጠኞች እና ልሂቃኖች አማራውን በማዳከም የወያኔ መጋዝ ይዘው በግዝገዛው ሴራ ላይ እየተሳተፉ ናቸው። “ኢሳት” ጭምር። ጌታቸው ረዳ የሚለውን ጽሁፍ ሳነብ፣ ምንም እንኳ ከስብሰባው አዘጋጅ ከሞረሽ ወገኔ መግለጫ ይወጣል ብዬ ስጠብቅ እስካሁን ባላይም፣ በኢሳት ሴራ በጣም ማዘኔንና፣ የሞረሽ ወገኔን ደግሞ “እሰጥ – አገባ” ውስጥ አለመግባት የድርጅቱን በራስ መተማመን ያሳየኝ ክስተት መሆኑን መግለጽ እወዳለሁ።

ሞረሽ ስብሰባውን ሲጠራ በማስታወቂያው፡-

በኢትዮጵያና በአማራው ነገድ ላይ እየተፈጸመ ስላለው ጥፋት እና ጥፋቱን ለመከላከል አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ማድረግ ስላለበት ተግባር ለመመካከር የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል።

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥልቅ እውቀት ያላቸውን ሶስት ምሁራንን ፕሮፌሰር ጌታቸው ሓይሌን፣ ዶክተር ሃይሌ ላሬቦ እና አቶ ጌታቸው ረዳን በአስረጅነት ጋብዘናል። ይልና በኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ እንዲገኝ ይጋብዛል።

በሞረሽ ወገኔ የግብዣ ጥሪ ላይ እንደምናየው፣ ኢትዮጵያዊውን ሁሉ ለውይይት ሲጋብዝ ቅሬታም ካለ ቅሬታን በመድረኩ ላይ ተገኝቶ እንደማሰማት፣ ለምን ሰው ወደ ስብሰባው እንዳይሄድ ኢሳት በዚያው ሰዓት እና በዚያው ቀን ስብሰባ መጥራት መረጠ? ብሎ መጠየቅ ከጀሌነት ራስን ነጻ ማውጣት ብቻ ሳይሆን፤ ሰው ለኢሳት ለሚያደርገው የገንዘብ አስተዋጽኦ የመጠየቅ መብቱም ነው ብዬ አምናለሁ።

ሞረሽ ወገኔ በጁላይ 27 “ቅሬታን ስለማሳወቅ” ብሎ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቦርድ በጻፈው ደብዳቤ እንዲህ ይላል።

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በ፴፩ኛው የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርት ዝግጅት ለሰኔ ፳፮ ቀን ፪ሺህ፮ ዓ.ም. (July 3, 2014) ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራቱን ኢሣት እያወቀ፣ ማስታወቂያውንም በራሱ ዝግጅት ከሦስት ጊዜ በላይ ለሕዝብ አሰምቶ እያለ፣ የኢሣትን ዓመታዊ የገንዘብ ማሰባሰቢ ዝግጅት ድሮ ያደርግ የነበረበትን ቀን ትቶ፣ ሞረሽ-ወገኔ ሕዝባዊ ስብሰባ በሚያዘጋጅበት ቀን እና ሰዓት ለማድረግ መወሰኑ፣ “ጠብያለሽ በዳቦ” ሆኖ ተሰምቶናል። ይህም የኢትዮጵያውያን ተቋሞች እንዲጠናከሩ እንጂ፣ እንዳለፉት ሁሉ ተቋሞች እንዳይፈርሱ ዓላማቸው አድርገው የተነሱትን እንደሞረሽ ያሉ ድርጅቶችን የጠነከረ አቋም የሚፈታተን ሆኖ ተሰምቶናል።

ስለሆነም፦

1. ኢሣት በሣንሆዜ ሊያደርገው ያሰበውን ዝግጅት ቀኑን ለሌላ ቀን እንዲደርግ አጥብቀን አበክረን እንጠይቃለን።

2. በዐማራው ላይ የሚፈጸሙ ግፎች እና በደሎችን ኢሣት ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ባላነስ መልኩ የዜና ሽፋን እንዲሰጠው ከማክበር ጋር እናሳስባለን።

ይህ አቤቱታ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቦርድ ይድረስ እንጂ ቦርዱ ለቅሬታ ማሳወቂያው መልስ ከመስጠት ይልቅ የሞረሽን ስብሰባ ለማደናቀፍ ካቀደው ሴራው አልተቆጠበም። ለምን?

ኢሳት በኢትዮጵያኖች የገንዘብ እርዳታና ተሳትፎ የተቋቋመ እስከሆነ ድረስ ኢትዮጵያኖችን በጋራና በእኩልነት የሚያሳትፍ ከመሆን አልፎ ወገን በመለየት ለአንዱ አቀንቃኝ ለሌላው እንቅፋት መሆን አልነበረበትም። ኢሳት የራሱ ባለቤትነት የሌለው፤ ግንቦት 7 እና የአክራሪ ብሄረተኞች በውስጥ ሆነው በበላይነት የሚያሽከረክሩት ነው እየተባለ ለሚታማው ማስተማመኛ ካልሆነ በቀር በሞረሽ ስብሰባ ላይ ያሳየው ተንኮልና ሴራ ሌላ ትርጉም ሊሰጠው አይችልም።

ኢሳት ከአማራው ህዝብ የሚፈልገው ገንዘቡን እንጂ የአማራውን ህዝብ አይደለም የሚባለውን ወሬ ከዚህ በፊት እንዳልታመነ ወሬ ሰምተን ከማለፍ ይልቅ ቆመን ኢሳትን ከመጠየቅና ከመጠራጠር አልፈን የሳንሆዜው የኢሳት ድርጊት ለወሬው ማስተማመኛ ከመሆን ያለፈ ለኢሳት የፈየደለት ነገር ያለ አይመስለኝም። በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን የዘር ማጥፋትና ማጽዳት ወንጀል የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ኢትዮጵያዊነት በአንድ መድረክ ተገናኝቶ እንዳይነጋገር  እንቅፋት እየሆኑ ከኢትዮጵያኖች በተለይም ከአማሮች የገንዘብ እርዳታ መጠየቅ “ከሞኝ ደጃፍ ሞፈር ይቆረጣል” እንደሚሉት፣ አይን ያወጣ የሰው ንቀት ይሆናል። የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ደግሞ አማራው ኢሳትን በገንዘብ እስከረዳ ድረስ፣ በኢሳት ቴሌቪዥን ጣቢያ በአማራው ህዝብ ላይ የሚፈጸመውን መፈናቀል፣ መገደልና መታሰር ወዘተ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ እኩል ትኩረት ሰጦ ማስተናገድ ይገባል። “ከአማራው ህዝብ ገንዘቡን ብቻ ነው የምንፈልገው” የሚለው ፈሊጥ በሂደት የኢሳትን ማንነት መፈታተኑ እንደማይቀር ኢሳትና ደጋፊዎቹ ሊያስቡበት ይገባል። “እዩኝ! እዩኝ! ያለች ደብቁኝ! ደብቁኝ ትላለች” እንደሚባለው፣ ዛሬ መድረኩን ይዘናል ተብሎ የአንድን ህዝብ መፈናቀል፣ መገደልና መታሰር ህዝብ እንዳያውቅ የሚደረግ ተንኮልና ሴራ ነገ ያስጠይቃል።

tasewanete@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule