• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢህአዴግ ለባርነት የተሸጠችው ወገን ሰቆቃ

February 26, 2015 08:35 pm by Editor Leave a Comment

ገነት አበበ ሞላ ትባላለች፤ የልጅነት ጊዜዋን ሩጣ ያልጠገበች በአስራዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ ኮረዳ ነች። ከዛሬ 3 አመት በፊት ነበር በኑሮ ውድነት የተጎሳቆሉ ቤትሰቦችዋን ከድህነት ለመታደግ በወቅቱ እስከ ገጠር በዘለቀው የአሰሪና ሰራተኛ የደላሎች ዘመቻ ከአርሲ ኮሌ ወረዳ ኩዬ ከተማ ተመልምላ የማይጨበጠውን የአረቡን ዓለም መከራ ለመጋፈጥ ተስፋ ሰንቃ ወደ ሳውዲ አረቢያ ያቀናቸው።

በወቅቱ በሰው ልጆች ህይወት ዶላር ለማግበስበስ በየአካባቢው በተከፈቱ የአሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲ ደላሎች ከእናቶቻቸው ጉያ ተነጥቀው ለአቅመ ሄዋን ያልደረሰውን እድሜዎቻቸውን ቆልለው ፓስፖርት የወሰዱ ህጻናት ሳይቀሩ በቀን 1500 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የኮንትራት ሰራተኞች ያለህይወት ዋስትና ወደ ሳውዲ አረቢያ በጅምላ ይላኩ የነበረበት ወቅት በመሆኑ ወጣት ገነትም ሰው እንደሆነው እሆናለሁ ብላ በፌስታል የተሞሉ ልብሶቿን ይዛ የምትወዳቸውን ወላጆቿን በዕንባ የተሰናበተቸው። አንድም ቀን ከቤት ወጥታ የማታውቀውን ገነት አስረክበው ወደ ቀዬያቸው የተመለሱ ወላጆቿ የገነትን ድምጽ ቢናፍቁም ባህር አቋርጣ ሳውዲ ሄደች ከተባለ ወዲህ ወራት ተቆጥረው ዓመት ቢደፍንም ገነትን የበላ ጀብ አልጮህ አለ።

ወትሮስ ለማን አቤት ሊባል? “የገነትን ስቃይ ማን ይወቅላት?” ክፉ አጋጣሚ ሆኖ  በአሰሪዎቿ “ኃይል” ወደሚባል ገጠራማ የሳውዲ ግዛት ለስራ የተወሰደችው ገነት ወግ ባህሉ ቋንቋው ባዕድ በሆነባት ሃገር ሁሉም ነገር እንዳሰበቸው እና እንደተነገራት አልነበረም።  ታዲያ ገነት ከቤትሰቦቿ ጋር ስትለያይ ሲያነቡ የነበሩት አይኗቿ እንባ እንደቋጠሩ ነበር    ፍጹም ከባድ የሆነውን የአረቡን ዓለም የቤት ስራ የተጋፈጠቸው፡፡

genetበማለዳው ምናምን ቢጤ ቀማምሳ ለአመታት ተጠርጎ የማያውቀውን አቧራ የለበስና ቆሻሻ የተከመረበትን ግቢ ከአሰሪዎቿ በምልክት በተሰጣት ትዕዛዝ ስታፀዳና ከ4 ያላነሱ መኪኖችን ስታጥብ መዋል የዘወትር ተግባሯ ሆነ። በዚህ መልኩ ለወራት የተዋሃዳትን የአሰሪዎን የቤት ውስጥ ስራ ጨምሮ የማይመለክታትን ከባድ ስራዎች ሁሉ ካጠናቀቀች በኋላ ለሌላ አረብ ተላልፋ እየተሰጠች የቤት ሰራተኛ ለሌላቸው የሰፈሩ አረቦች ሁሉ አገልጋይ ሆናለች።

ገነት እረፍት የላትም እንደ ዘበኛ መኪና በመጣ ቁጠር የግቢ በር ትከፍታለች፤ የአሰሪዎቿን መኪናና ግቢ ታጥባለች፤ ከባድና ቀላል የሆኑ እቃዎችን እስከ 3ኛ ፎቅ ተሸክማ በመውጣት ከአቅም በላይ የሆነና የማይመለከታትን ስራ በግዳጅ እንድትሰራ ትደረጋለች። ከቤተሰቦቿ ከተለየች ወዲህ በስልክ ወላጆቿን አግኝታቸው የማታውቀው ገነት ከሥራው ክብደት ይልቅ በናፍቆት ከሰውነት ጎዳና የወጣው አካሏና የልጅነት ወዝ በቁም የተገነዘች ሬሳ አስመስሏታል፡፡

በአስሪዎቿ ታግት በደል የሚፈጸምባት ገነት አበበ ሞላ ከሚፈፀምባት ግፍ እና በደል  እግር ወደ መራት በመሄድ እርሷን ከባርነት ለመታደግ የሞከረችበትም አጋጣሚ እንደነበር ይነገራል። ከዚያ ወዲህ ገነትን ለማግባባት ብዙ ሞክረው እንዳልተሳካላቸው የተረዱት አሰሪዎቿ ገነት ላይ የሚያደርጉትን ክትትል በማጠናከር የስራ ግዳጅዋን ስትጨርስ ባዶ ቤት ይቆለፉባታል። የቤት ሰራተኛ እጥረት የገጠማት ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በአሰሪዎቿ የታገተቸው ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ገነት አበበ ለአሰሪዎቿ እያበረከተች ካለው ነጻ አገልግሎት ባሻገር በወር እስከ 3800 በሚደርስ ክፍያ ለሦስተኛ ወገን ተላልፋ በመሰጠት ጥሩ የገቢ ምንጭ እስከ መሆን መድረሷ ይነገራል። ከአንዱ የአረብ መኖሪያ ወደ ሌላው የአረብ መኖሪያ ቤት እየተቀባበሉ ያለ በቂ እረፍት የአረብ አገልጋይ ለመሆን የተገደደቸውን ኢትዮጵያዊት “የኮንትራት ሰራተኛ” ከማለት ይልቅ በኢህአዴግ ህጋዊ ፈቃድ አግኝቶ በሚንቀሳቀስ አሰሪና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ የተሸጠች ባሪያ ማለት ይቀላል።

አዲስ አበባ ውስጥ በተለምዶ ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ ሴብሪን “sebirn” እየተባለ በሚጠራ አንድ ኤጀንሲ አማካኝነት ተዋውላ “ህጋዊ” በሆነ መንገድ ለስራ ሳውዲ እንደገባች የሚነገርላት ገነት ዛሬም የድረሱልኝ የሰቆቃ ድምጽዋን ታሰማለች – የሚሰማት ካገኘች!

አሁን አሁን ለህይወቷ የምትሳሳው ገነት ይገሉኛል በሚል ስጋት በድብደባ ከተጎሳቆለው አካሏ ባሻገር ሌሎች ምስጢራዊ በደሎችን ለግዜው ከመግለጽ መቆጠቧን ለልጅቷ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ይገልጻሉ። እነዚህ ወገኖች አቤቱታቸውን በጅዳ ለኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ቢገልጹም እስክ አሁን የገነት የሰቆቃ ድምጽ ምላሽ አላገኘም፡፡

ሰሞኑን በደመወዝ ጥያቄ በጥይት የቆሰለችውን ኢትዮጵያዊት ከወራት ቆይታ በኋላም ቢሆን እውነታውን በአካል ሄደው ያረጋገጡት የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ሃላፊዎች የሰቆቃ ድምጽ ለምታሰማው ወጣት ገነት አበበ ሞላ አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ይጠበቅባቸዋል። ይህ በዚህ እንዳለ በዚህ መልኩ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በ10 ሺህ የሚቆጠሩ እንደ ጨው ተበትነው ያሉበት ሁኔታ በውል የማይታወቅ ግፍ እና በደል እያስተናገዱ የሚገኙ እህቶች መኖራቸው በተደጋጋሚ ተገልጾል። (Ethiopian Hagere Jed Bewadi)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule