• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ማፈናቀሉ የሚካሄደው በመንግሥት ትዕዛዝ ነው፤ ወደ ክስ እናመራለን”

April 23, 2013 04:10 am by Editor 4 Comments

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ2000 ሺህ በላይ ትግሬዎች ባለይዞታ መሆናቸውንና ማንም ሳይነካቸው በሰላም እንደሚኖሩ፣ በቶጎ ወረዳ ከስልሳ በላይ ነባር የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ የእርሻ መሬት ወስደው በባለሃብት ደረጃ እንደሚገኙ የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አስታወቁ። ከሌሎች ብሔረሰቦች ተለይቶ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ያለውን የአማራ ብሔረሰብ በድጋሚ ለማስወጣት መታቀዱንም በመረጃ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።

በቦታው በመገኘት አስፈላጊውን መረጃ እንደሰበሰቡ ለአሜሪካ ሬዲዮ የገለጹት የመኢአድ ስራ አስፈጻሚ በክልሉ ከሚኖሩት የተለያዩ ብሔረሰቦች ተለይቶ የአማራ ብሔረሰብ እንዲፈናቀልና እንዲሰቃይ የሚደረገው በማዕከላዊ መንግስት ትዕዛዝ እንደሆነም አመልክተዋል።

መኢአድ ያሰራጨውን መግለጫ ተከትሎ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ማብራሪያ የሰጡት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ ድርጊቱ በበታች የቀበሌና ወረዳ አመራር አካላት ተፈጽሟል መባሉን ተቃውመዋል።”ሰዎቹ እንዲወጡ ሲታዘዝ ያ ሁሉ ወታደር ከየት መጣ?” በማለት የጠየቁት አቶ ሃይሉ ሻወል፣ በርካታ የወያኔ ሰዎች በቦታው እያሉ አማራው ተለይቶ እንዲፈናቀል የበታች ባለስልጣናት በራሳቸው ውሳኔ ይህን ሊያደርጉ እንደማይችሉ ተናግረዋል። በማያያዝም በርካታ ተጨባጭ ማስረጃ ስለተሰባሰበ ጉዳዩን ወደ ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

ባላቸው የተለያየ መስመር ፍርድ ቤቱ የሚቀበላቸውን ማስረጃዎች በማጣራት አስፈላጊ መረጃዎችን እንዳሰባሰቡ የገለጹት ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል፣ “የሰውና የቪዲዮ መረጃ አለን። የመንግስት ወታደሮች ህዝብ ሲደበድቡ፣ መኪና ተገልብጦ ሰዎች ሜዳ ላይ ሲሰቃዩ፣ በግድ ሲፈናቀሉ … የሚያሳይ ተጨባጭ ማስረጃ አሰባስበናል። ወደ ክስ እናመራለን” በማለት መናገራቸውን የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ (ቪኦኤ) አመልክቷል።

የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል በበኩላቸው የመንግስት ባለስልጣኖችና ካድሬዎች በኩምሩክ ሕዝብ በመሰብሰብ ማነጋገራቸውን ይጠቅሳሉ። እሳቸው እንዳሉት ህዝቡ “ለምን በዘራችን ሳቢያ ይህ ሁሉ ስቃይ ይደርስንባል?” በማለት ጠይቆ ነበር። የሰበሰቧቸው ባለስልጣናት “ክልሉ የናንተ አይደለም ውጡ” ሲሉ  እንደመለሱላቸው የጠቀሱት የስራ አስፈጻሚ አባል፣ በሌላ በኩል የተፈጸመው ህገ ወጥ የዘር ማጥፋት ተግባር የመንግስት እጅ ያለበት እንዳይመስል ለክልሉ ነዋሪዎች “አማራን አታስጠጉ፣ ከአማራ ጋር አትብሉ፣ ከአማራ ጋር አትጠጡ፣ ቤት አታከራዩ፣ ይህን ማድረግ ወንጀል ነው” በማለት መንገራቸውንና በዚሁ መነሻ ህዝቡ በክልሉ ያሉ አማሮች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ጥያቄ እንዲያቀርቡ መመሪያ መሰጠቱን አመልክተዋል። ይህ የሚሆነውም ጥያቄው ከህዝብ የመጣ እንደሆነ ለማሳየት እንደሆነም አስታውቀዋል።

ahmed
የቤኒሻንጉል ፕሬዚዳንት አህመድ ናስር

በዘር፣ በሐይማኖትና በአመለካከት አንድን ማህበረሰብ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት መሞከር፣ ማሸማቀቅ፣ ሴቶችን መድፈር በዘር ማጥፋት እንደሚያስጠይቅ ያመለከቱት የመኢአድ የስራ አስፈጻሚ አባል፣ “ይህ ሁሉ ተፈጽሟል” በማለት ድርጅታቸው በዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ ለመመስረት ከድምዳሜ መድረሱን ገልጸዋል።

የቤኒሻንጉል ክልል ፕሬዚዳንት ለሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ስህተት መሰራቱን ማመናቸውና ድርጊቱን የፈጸሙት ኪራይ ሰብሳቢ የወረዳና የበታች አመራሮች እንደሆኑ ማስታወቃቸው አይዘነጋም። በተመሳሳይ ለስራ ፈረንሳይ አገር በነበሩበት ወቅት ለጀርመን ሬዲዮ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ፕሬዚዳንቱ ተፈጸመ ስላሉት ስህተት “የማውቀው ነገር የለም። አልሰማሁም። እኔ የማውቀው ደን ጨፍጭፈው በሃይል መሬት የያዙ መፈናቀላቸውን ነው” ብለዋል። ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያም ቀደም ባሉት ሳምንታት ከቤኒሻንጉል የተፈናቀሉትን ዜጎች አስመልክተው በሰጡት አስተያየት ወንጀሉ የዘር ማጥፋት ስለሆነ ክስ መመስረት እንደሚቻል አመልክተው ነበር።

መኢአድ በበደኖ፣ በአርባ ጉጉ፣ አረካ ቀደም ሲል የተፈጸሙትን የዘር ማጥፋት ወንጀሎች አያይዞ ለክስ እንደሚጠቀምበት አመልክቷል። በጥያቄና መልሱ ወቅት ከነበሩት ጋዜጠኞች መካከል “የተፈናቀሉት ተመልሰዋል። ለምን አትተውትም” በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ጋዜጠኞች እንደነበሩ የቪኦኤው የአዲስ አበባ ዘጋቢ ጠቆም አድርጎ አልፏል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አልማዝ says

    April 23, 2013 06:15 am at 6:15 am

    ውድ ጎልጉል፣ ሰፋፊ እርሻ አላቸው ያልካቸውን የህወሃት ታጋዮችን ስም ዝርዝር ማውጣት ይኖርባችኋል። ሌላው ሕዝብ ወደ ሌላ ክልል እንዳይሄድ ተከልክሎ [በተለይም ወደ ትግራይ] የትግራይ ሕዝብ ግን ወደ ፈቀደው ሄዶ እንደ ፈቀደው ንግድ ማካሄድ መቻሉ አግባብ አይደለም።

    Reply
  2. Mario says

    April 24, 2013 08:04 pm at 8:04 pm

    Ethiopians have been subjected to killilism over shadowed by fake federalism. The fact is, it is woyanes and Al Almoudie and their beneficiaries who have the right to work, live and create wealth in any part of the country. Not because they are forced, but by their own free will and the exclusive right they they have. The rest of us are, “የበይ ተምልካች”. People are not even allowed to travel out of their killils. Over the years, killilism and fake federalism developed to a subtle and refined woyane style apartheid system. That is what it is.

    Our immediate job is to dismantle killilism, fake federalism and apartheid systems in Ethiopia. The earlier we do it, the better!!!

    Reply
  3. moged says

    April 24, 2013 09:29 pm at 9:29 pm

    Yizegiy enji hulum edawun yikefla! Ahun enkua bayhon, beliju hone belij liju yaleksal.
    Gid yelem bisot yitefaqem. Genzebim habitim halafi new, Tplf.eprdf yeethiopian tarikinina hizbuan aqoshishew ayqerum!!

    Reply
  4. በለው ! says

    April 25, 2013 05:54 pm at 5:54 pm

    “ማፈናቀሉ የሚካሄደው በመንግሥት ትዕዛዝ ነው፤ ወደ ክስ እናመራለን”በጠ/ሚ ኅይለመልስ የተሰጠው የፓርላማ መልስ በጣም ጠለቅ ያለ ሚስጥርን አውጥቷል መተርጎም ለሚችል ወንጀለኛን የሚከላከል ቃል ነው። ለማይገባው ግን ግለሰቡን ኃይለኛ የህዝብ ተቆርቋሪና ብስጩ የሆኑ ያስመስላል ግን ቤታቸው የበሰበሰና የበሸቀጠ እኛ የሞቱ ጠ/ሚ እንዳሉት ቆሻሻ ሌባ እደግመዋለሁ ቆሻሻ ሌባ በኢህአዴግ በዝቷል ሕገመንግስቱም ሆ ! ብለህ አስወጣ ይላል አቶ ኀይለመልስ በፓርላማ ንግግራቸውን “የአማራ ክልልና የአማራ ብሔር ተወላጆች? “ሲሉ ነበር የጀመሩት ግን እዚህ ጋ ነው የህገመንግስቱ ብሽቃጣምነት ማንነትህን በዘርህ እንጂ በኢትዮጵያዊ ዜግነትህ አያውቅህም ሀገሪቱም ሉዓላዊነት ሳይሆን ክልላዊ የግለሰብ ሉዓላዊነት ብሎ አስቀምጦታል አንድ በረት የታጎረ ከብት መለያው ቋንቋውና ዘሩ የሆነ !!… አፈናቃይ ተብዬዎች? ሕገምንግስቱ እንደተጻፈው “ለክልሉ መሰተዳደርና ለሕዝቡ ልማት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ማናቸውንም ሠፋሪ (ሞፈር ዘመት) ብሎ ማስለቀቅ መብቱ እንደሆነ ይደነግጋል”። አታጭበርብሩ!…የፌዴራል መንግስት ሥልጣንና ኀላፊነት ግን “የክልሉ መንግስት ማስተዳደር ያልቻለውንና ተከራይ ማፈላለግ ባልቻለበት ጊዜ ሙሉ ኀላፊነት ወስዶ ተከራይ ማፈላለግና መሬቱን ማከራየት መብት እንዳለው ይገልጻል”። ስለዚህ እጅና ጓንት ሆኖ የተሠራውን ውንብድና በጥቂት ግለሰቦች ላይ ለጥፎ ለህዝብ ተቆርቋሪነትን ለማሳየትና እራስን ከወንጀል ማፅዳት በሩሱ የማጭበርብር ወንጀል ነው። ለመሆኑ ችግሩ ከተፈጠረ ጀምሮ ጠ/ሚ ኅይሌ ጋዜጣዊ መግለጫ በቲቪ፣ በሬዲዮ፣ በጽሑፍም ይሁን ማስተካከያ ሠጥተዋልን? እንዴት በፓርላማ ለመፎከር በቁ? ? በራሳቸው አንደበት የሚያምኑት ግን በሁሉም ክልል “ኢህአዴግ በሌብነት የተጨማለቀ ኪራይ ሰብሳቢ ወሮባላ መሆኑን አስረግጠው ተናግረዋል!።” ለመሆኑ ይህ ደን የሚመነጥረው(ከሌላ አካባቢ የሚመጡ ሰዎች ያሏቸው!!?) የኦሮሞና የአማራ ገበሬዎች ወንጀል ነው። ሕንድና አረብ ሲያቃጥለው ልማት ነውን?
    ”ሰዎቹ እንዲወጡ ሲታዘዝ ያ ሁሉ ወታደር ከየት መጣ?”
    የአጭበርባሪ “ከቡድን” ወደ “ኀብረት አመራር” የተሸጋገረ የተወራረሰ የተተካካ ሌብነት…
    *የቤኒሻንጉል ክልል ፕሬዚዳንት አህመድ ናስር ለሪፖርተር በሰጡት መግለጫ ስህተት መሰራቱን ማመናቸውና ድርጊቱን የፈጸሙት ኪራይ ሰብሳቢ የወረዳና የበታች አመራሮች እንደሆኑ ማስታወቃቸው አይዘነጋም።
    **በተመሳሳይ ለስራ ፈረንሳይ አገር በነበሩበት ወቅት ለጀርመን ሬዲዮ ጉዳዩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ፕሬዚዳንቱ ተፈጸመ ስላሉት ስህተት “የማውቀው ነገር የለም። አልሰማሁም። እኔ የማውቀው ደን ጨፍጭፈው በሃይል መሬት የያዙ መፈናቀላቸውን ነው” ብለዋል።
    ***አቶ ኀይለመልስ ግን የማያውቁትን ህገመንግስት በማቆላመጥ ሕዝብ ከእነ ነፍሱ የሚሸጥ ኪራይ ሰብሳቢ በሁሉም ክልል ይዘው ሀገር እንደሚመሩ በድፍረት ይናገራሉ። ገንዘብ ያለው አማራና ኦሮሞ አይፈናቀልም ሲሉ… በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ2000 ሺህ በላይ ትግሬዎች ባለይዞታ መሆናቸውንና ማንም ሳይነካቸው በሰላም እንደሚኖሩ፣ በቶጎ ወረዳ ከስልሳ በላይ ነባር የህወሃት ታጋዮች ሰፋፊ የእርሻ መሬት ወስደው በባለሃብት ደረጃ እንደሚገኙ አልተናገሩም ምክንያቱም የእንጀራ ገመዳቸው ይበጠሳል።ለማስመሰል ጥቂት ማንበብና መፃፍ የማይችሉ ድሆች ሲታሠሩና ሲሰቃዩ በፍርድ ሲጉላሉ የሚያሳይ ተከታታይ ድራማ እራሳቸው የወያኔ ባለሀብቶች ፊልም ይሠሩበታል። የብላ ተባላ የኀብረት አመራር… “አመራር በደቦ” ሸዋ ተወቃህ በለው አላልኩም ነበር ?የኅይለመለስ ደስአላለኝም ይህንን ጉዳይ እልባት የሚሠጠው በዓለም መንግስታት ሕግ ፊት ቀርቦ ለተደጋጋሚው ጥፋት ዕርማት ባለመስጠቱ ቅጣትና ትምህርት ሲያገኝ አለዚያም የሕገመንግስቱ አተረጓጎም በሁሉም የሀገሪተ ቋንቋና የህግ ባለሙያዎች ከሌሎች መመሪያ ደንቦችና አዋጆች ጋር ሲናነብና ሲጠና ብቻ ነው!!። ለ፻፮ የሕገመንግስት አንቀፅ ፻፮ አዋጅና መመሪያ ማውጣት ከጥፋት አያድንም “ልዩነታችን ውበታችን ማለትም” ሀገሪቱን ከመበታተን አያድናትም ። ለነገሩ ብትኖር ኖሮ ሠው በዘር፣በድህነቱ፣በቋንቋው ተለይቶ ይፈናቀል ነበር ? ?የቀጣፊ ፣ሆድአደር ፣አድርባይ ፣ጥቅመኛ፣ወኔ ቢስ፣ ዘመንና ትውልድ የፈጠረ የተማረ የገደለው ህዝብ።
    ” ኢትዮጵያ እጆቿን ዘርግታ ቅን አሳቢ ልጆቿን ትሠበስባለች እንደገና አንድ ትሆናለች በለው! በቸር ይግጠመን ከሀገረ ካናዳ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule