• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዲና ሙፍቲ ይመችዎት – “በነጻው ፕሬስ” ስም

April 9, 2014 07:53 am by Editor 1 Comment

ለምሳሌ አንድ አናጢና ግንበኛ የነበረ ሰው ጊዜ ረድቶት ወይም ተምሮ ወይም እድገት አግኝቶ ወይም …. በቃ በሆነ ነገር የጦር ጄኔራል ቢሆንና ተመልሶ ግንበኛ ቢሆን ምን ተብሎ ሊሰየም ነው? ግራ ያጋባል። ግን ደግሞ ላያጋባም ይችላል። የዛሬዎቹ ጄኔራሎች ኢንቨስተር ስለሆኑ ነዋ!! ለምሳሌ አንድ አምባሳደር ተብሎ የ”ተመደበ” ሰው፣ በግምገማ በሉት በገገማ “በቃህ” ቢባልና ቀድሞ ወደነበረው ሙያ ወደ ነርስነቱ ቢመለስ ምን ተብሎ ሊጠራ ነው? “አምባሳደር፣ ነርስ፣ እገሌ …”?

ቀጭኑ ዘ-ቄራ ነኝ። በውል በማይገባችሁ ምክንያት ተሰውሬ ነበር። ዛሬ እግር ጣለኝና “ላሸብር” መጣሁ። ሰላምታዬ መሆኑ ነው። መለስ ድንጋዩ ይቅለላቸው፣ አርማታው ስፖንጅ ይሁንላቸውና ብዙ አይነት የሰላምታ ቋንቋና ስታይል “አውርሰውን” አልፈዋል። ታላቁና አርቆ አስተዋዩ መሪያችን!! ህወሃቶች በዚህም ይቀኑ ይሆናል እኮ። መለስዬን ማን የነሱ ብቻ አደረጋቸው? እስኪ አርፈው ይተኙ፣ ይሙቱበት… እኔ ወደ ጉዳዬ ላምራ። “ግን መቃብራቸው ልዩ ጥበቃ የማይደረግለት ለምንድነው?” ሳልል ማለፍ አልፈልግም። ዋ!! ድንገት ቢነሱ!! ዋ ብያለሁ …

ግን አሁን አምባሳደር የነበረ ሰው ጡረታ ወጥቶ ደላላ ቢሆን “አምባሳደር፣ ደላላው፣ እገሌ” እያልን ልንጠራ ነው? የአገራችን ሚዲያዎች ነጻ መውጣት ያቃታቸው ከስም ስያሜ ጀምሮ ነው። ካላይ ያነሳኋቸው የኢህአዴግ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ “አቶ” ይቅርታ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስም ነው ሌላ ጉዳይ ውስጥ ቀርቅሮ ያስለፈለፈኝ። እሳቸው አሁን የተመደቡበት መደብ “አምባሳደር” በሚል ርዕስ ከሆነ ግድ የለኝም። ግን ለጌቶቻቸው ቀላጤ ሆነው በህዝብ ግንኙነትና አንደበትነት ተመድበው ከሆነ ለጊዜው “አቶ” በቂ ነው። የነጻው ፕሬስ ሰዎች ወይም የበርጫ ቤት ባልደረባዬ ሽመልስ ከማል እርማት ይስጡበት።

አንድ በርጫ የሚወድ ጋዜጠኛ፣ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን “ይከይፉኛል” በማለት አድንቆቱን ይቸራቸዋል። ዜና ሲጠፋ ሚስኮል ማድርግ ብቻ ነው። ምን ልታዘዝ በማለት የተመደቡበትን መደብ ሳይለቁ መግለጫ ይሰጣሉ። መብራት ሃይል ሰንደቁን አባሮ የመደባቸው ካድሬ መግለጫ መስጠት የጀመሩ ሰሞን ባህር ዳር እየደወሉ “ዛሬ ማታ ዜና ተመልከቱ፣ እኔ እታያለሁ” ይሉ ነበር። የመጀመሪያ ቀን ለዋንየው ሰውዬ ደውለውለት “ማን ጋር እንደደወልክ አውቀሃል” አላቸው። እሳቸውም ስማቸውን በመጥራት “እኔ እኮ ከፌዴራል መንግስት ነው የምደውለው” እንዳሉት እጎናቸው ያለ ሰው አጫውቶኛል። “ማን ይሙት” ካላችሁ፣ አንድ የምምልበትና የምገዘትበት ስም ነበረኝ “ተሰዋብኝ”። ስምም ይሰዋል። ዘንድሮ!! እኔን!! ለነገሩ የዘንድሮ መሐላ “ሰለሜ ሰለሜ” ሆኗል።

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለመለስ ሲያለቅሱ የሚያሳውን ፊልም እስኪ ዝም በሉና እዩት። እየተዝረበረቡ ሲነፈርቁ ጅል ነው የሚመስሉት። ለነገሩ ጅል መስለው ቁብ አሉበት። ከሳቸው ጋር አገራቸው ኮንፍራንስ የተካፈለ ሰው ሲናገር እንደሰማሁት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እያሉ ከአጃቢዎቻቸው ጋር መጡ። ኮንፍራንሱ ላይ እድል ተሰጣቸውና ተናገሩ። “እኔ የኢየሱስን ስም መጥራት የማይገባኝ … ” በማለት አነቡ። ተንበርክከው ነፈረቁ። ሁለት ኣመት ሳይሞላ እስክስታ ጀመሩ። ሰለሜ ሰለሜ እያሉ እሬብ ለሬብ ተያይዘው ዘለሉ።

አራዳው መለስ ነብሳቸውን ገለባ ያድርገውና፣ ቀላል ለማለት ነው ገለባ ያልኩት “የኢትዮጵያ ሚሌኒየም” ሲከበር አላሙዲን ባስገነቡት የኮንቴነር ቤት ውስጥ ነው። ለመሆኑ እሱ ቦታ የማን እንደነበር ስማቸው በኖህ የሚጀምር አንድ ሃብታምና አዋቂ ሰው አፈላልጋችሁ ድረሱበት። ከሂልተን እስከ ሸራተን በተደረገ ግብዣ የተሰረቀ ፕሮጀክት ነው። በትክክልም ላሸብር እንደመጣሁ የገባኝ አሁን ነው። ኮንቴነርም ቢሆን ይሁን፣ ፕሮጀክቱ ድራማ ቢኖረውም ማን እንደሳቸው። በብድርም ቢሰራ ይሁን ከማለት ውጪ ምን ይባላል? አላሙዲ ግን ይገርማሉ እኮ። በሄክታር 0.20 ሳንቲም ግብር መክፈል አቅቷቸው ከሆለታ አበባ እርሻቸው እንዲነሱ የገበሬ ማህበር ደብዳቤ ጽፎላቸዋል ነበር። ብዙ ነገር አለ። ጥልዬ ምንድን ነበር ያለው “ሆድ ይፍጀው” ግን ለምን ሆድ ይፍጀው እኛን ራሳችንን ፍጅ-ት ያድርገን።

እናም አምባሳደር ዲና ሙፍቲ “ሙድ” አላቸው። ሚዲያውን ለባላንስ/ማመጣጠኛ ረድተውታል። አንድ ወዳጄ ሲተርባቸው ሳይደወልላቸው ከዋለ “ምነው ወዳጆቼ ጠፉ ብለው ይጨነቃሉ። ለመረጃ ነው፣ የታሰረ ጋዜጠኛ ወይም የተዘጋ ፕሬስ አለ?” ብለው የወዳጆቻቸውን ደህንነት ይጠይቃሉ። ግን እኮ ዝም ከማለት መናገር ይሻላል። ለተመደቡበት ቦታ ብቃት አላቸው። ኢህአዴግም በረከትም “ይመችህ” ያሏቸው ይመስላል። በተለይ ለሰነፍ ጋዜጠኞች መተዳደሪያ ሆነዋል። በነገራችን ላይ “ለመረጃ” በማለት የታሰሩ ጋዜጠኞችና የተዘጋ ፕሬስ እንዳለ ሲጠይቁ መልሱ “ምን ነጻ ፕሬስ አለና” የሚል ነው አሉ።

እዚህ ላይ ተመቸኝ። አዎ ነጻ ፕሬስ ወዴት ግድም ነው የሚገኘው? የት ነው ነጻ ሚዲያ ያለው። ከኢህአዴግን እየበላ የሚያመሰግን አለያም ሲመች እየተቸ ሲነቃነቅ ጥብቅና የሚቆም ወገንተኛ፣ ይህ አንዱ ነው። ሌላው ጭልጥ ብሎ መቃወም ነው። “ይህ ጥሩ ነው ግን” ብሎ የሚጀምር እንኳን የለም። ከጅምሩ ራሱ ኢህአዴግ በረከትን ልጓም የሌለው በትር ሰጥቶ ሊማርና ሊገራ የሚችለውን ጅምር አከሸፉት። ተወደደም ተጠላም ግን የተመጣጠነ ሚዲያ ግድ ነው። አለያ መጀመር እንጂ መጨረስ ይከብዳል።

ሃይለማርያም ሰለሜ ሰለሜ መጨፈር የሚችሉ አይመስለኝም ነበር። በነፈረቁበት ቤት እየተፍለቀለቁ ተምነሸነሹ – ደስ ይላል። ቤተ ክርስቲያናቸውና የሚያመልኩት መንፈስ ምን እንደሚላቸው ባለውቅም ሲጨፍሩ ደስ ብሎኛል። ቴድሮስ አድሃኖም እንደውም የቱሪዝምና ባህል ሚኒስትር ሁነው ኪነቱን ቢያነቃንቁ እመርጣለሁ። በነጻነት ፉት እያሉ እንዲሰሩ!! ሃይለ ማርያም ሲጨፍሩ በደስታ ስሜት ሆኜ መለስን ነፍስ ዘራሁባቸው። ህዝብ ፊት ቀርበው ዘፈን ምረጡ ሲባል “ሱዳንኛ” መርጠው ነው ከውዳቸው/ይቅርታ ውዳቸው የሌሎችም ውድ ነበሩ/ አብረው መስታዋት ቤት ውስጥ ሆነው በእጥርጥር የደነሱት!! የት? ሚሌኒየም አዳራሽ። አስቡት ኮንቴነር ቤት ውስጥ፣ በጋርዶች በተከበበ፣ በከባድ መሳሪያ በታጠረ፣ ጥይት በማይበሳው መስታዋት ውስጥ ሆኖ መዝናናት … ለትዝታ ያህል ነው። ታዲያ እሳቸው ሲሞቱ ያርማጮ ገበሬ ደረት መታ፣ ጸጉር ነጨ፣ የመንዲ እናት ደረቷን ደቃች። አዲስ አበባ በየቀበሌው ድንኳን ተጥሎ የቀበሌ የጸጥታ ሃላፊና ሊቀመንበርን “ነብስ ይማር፣ እግዜር ያጽናችሁ” እያለ ህዝብ ሲሰናበት … ጉድ እኮ ነው።

ቀጭኑ ዘ-ቄራ ኢህአዴግ “እንዲቀየር” የሚፈልገው እንዲህ ያሉ መለኪያ አልባ በሽታዎች ገሀድ ሲወጡ በዛው በጠንባራ ሚዲያ ለመመልከት በመጎምጅት ነው። እና መለስ በሱዳን ዘፈን ጨፈሩ!! ለምን? መሄድ የምትፈልጉ ሂዱና ጠይቋቸው። ቀጭኑ ሞትን ይፈራዋል። በድንገት ተስፈንጥሮ መሔድን አይወድም። አሁን የአራራ ሰዓት ነው!! ልሂድበት። እናንተም ተቀንጠሱ!! አምባሳደር ሙፍቲ ይመችዎት!!

ማሳሰቢያ፡- ከላይ ስለ አምባሳደርነት በምሳሌ ያነሳሁት የሙያ መጠሪያ ከአምባሳደር ዲናም ሙፍቲም ሆነ ከማውቃቸው አምባሳደሮች ጋር አንዳችም ግንኙነት የለውም። አምባሳደርነት የስራና የቦታው ሹመት እንጂ እንደ ሙያ ስም ለዘላለም ከሞት በኋላም የሚያገለግል አይደለም ለማለት ብቻ ነው!!

kechinu@goolgule.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Isak Amanuel says

    April 10, 2014 02:58 pm at 2:58 pm

    You are welcome Kechenu Z-Kera.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule