• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዲና ሙፍቲ ይመችዎት – “በነጻው ፕሬስ” ስም

April 9, 2014 07:53 am by Editor 1 Comment

ለምሳሌ አንድ አናጢና ግንበኛ የነበረ ሰው ጊዜ ረድቶት ወይም ተምሮ ወይም እድገት አግኝቶ ወይም …. በቃ በሆነ ነገር የጦር ጄኔራል ቢሆንና ተመልሶ ግንበኛ ቢሆን ምን ተብሎ ሊሰየም ነው? ግራ ያጋባል። ግን ደግሞ ላያጋባም ይችላል። የዛሬዎቹ ጄኔራሎች ኢንቨስተር ስለሆኑ ነዋ!! ለምሳሌ አንድ አምባሳደር ተብሎ የ”ተመደበ” ሰው፣ በግምገማ በሉት በገገማ “በቃህ” ቢባልና ቀድሞ ወደነበረው ሙያ ወደ ነርስነቱ ቢመለስ ምን ተብሎ ሊጠራ ነው? “አምባሳደር፣ ነርስ፣ እገሌ …”?

ቀጭኑ ዘ-ቄራ ነኝ። በውል በማይገባችሁ ምክንያት ተሰውሬ ነበር። ዛሬ እግር ጣለኝና “ላሸብር” መጣሁ። ሰላምታዬ መሆኑ ነው። መለስ ድንጋዩ ይቅለላቸው፣ አርማታው ስፖንጅ ይሁንላቸውና ብዙ አይነት የሰላምታ ቋንቋና ስታይል “አውርሰውን” አልፈዋል። ታላቁና አርቆ አስተዋዩ መሪያችን!! ህወሃቶች በዚህም ይቀኑ ይሆናል እኮ። መለስዬን ማን የነሱ ብቻ አደረጋቸው? እስኪ አርፈው ይተኙ፣ ይሙቱበት… እኔ ወደ ጉዳዬ ላምራ። “ግን መቃብራቸው ልዩ ጥበቃ የማይደረግለት ለምንድነው?” ሳልል ማለፍ አልፈልግም። ዋ!! ድንገት ቢነሱ!! ዋ ብያለሁ …

ግን አሁን አምባሳደር የነበረ ሰው ጡረታ ወጥቶ ደላላ ቢሆን “አምባሳደር፣ ደላላው፣ እገሌ” እያልን ልንጠራ ነው? የአገራችን ሚዲያዎች ነጻ መውጣት ያቃታቸው ከስም ስያሜ ጀምሮ ነው። ካላይ ያነሳኋቸው የኢህአዴግ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ “አቶ” ይቅርታ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ስም ነው ሌላ ጉዳይ ውስጥ ቀርቅሮ ያስለፈለፈኝ። እሳቸው አሁን የተመደቡበት መደብ “አምባሳደር” በሚል ርዕስ ከሆነ ግድ የለኝም። ግን ለጌቶቻቸው ቀላጤ ሆነው በህዝብ ግንኙነትና አንደበትነት ተመድበው ከሆነ ለጊዜው “አቶ” በቂ ነው። የነጻው ፕሬስ ሰዎች ወይም የበርጫ ቤት ባልደረባዬ ሽመልስ ከማል እርማት ይስጡበት።

አንድ በርጫ የሚወድ ጋዜጠኛ፣ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን “ይከይፉኛል” በማለት አድንቆቱን ይቸራቸዋል። ዜና ሲጠፋ ሚስኮል ማድርግ ብቻ ነው። ምን ልታዘዝ በማለት የተመደቡበትን መደብ ሳይለቁ መግለጫ ይሰጣሉ። መብራት ሃይል ሰንደቁን አባሮ የመደባቸው ካድሬ መግለጫ መስጠት የጀመሩ ሰሞን ባህር ዳር እየደወሉ “ዛሬ ማታ ዜና ተመልከቱ፣ እኔ እታያለሁ” ይሉ ነበር። የመጀመሪያ ቀን ለዋንየው ሰውዬ ደውለውለት “ማን ጋር እንደደወልክ አውቀሃል” አላቸው። እሳቸውም ስማቸውን በመጥራት “እኔ እኮ ከፌዴራል መንግስት ነው የምደውለው” እንዳሉት እጎናቸው ያለ ሰው አጫውቶኛል። “ማን ይሙት” ካላችሁ፣ አንድ የምምልበትና የምገዘትበት ስም ነበረኝ “ተሰዋብኝ”። ስምም ይሰዋል። ዘንድሮ!! እኔን!! ለነገሩ የዘንድሮ መሐላ “ሰለሜ ሰለሜ” ሆኗል።

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለመለስ ሲያለቅሱ የሚያሳውን ፊልም እስኪ ዝም በሉና እዩት። እየተዝረበረቡ ሲነፈርቁ ጅል ነው የሚመስሉት። ለነገሩ ጅል መስለው ቁብ አሉበት። ከሳቸው ጋር አገራቸው ኮንፍራንስ የተካፈለ ሰው ሲናገር እንደሰማሁት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር እያሉ ከአጃቢዎቻቸው ጋር መጡ። ኮንፍራንሱ ላይ እድል ተሰጣቸውና ተናገሩ። “እኔ የኢየሱስን ስም መጥራት የማይገባኝ … ” በማለት አነቡ። ተንበርክከው ነፈረቁ። ሁለት ኣመት ሳይሞላ እስክስታ ጀመሩ። ሰለሜ ሰለሜ እያሉ እሬብ ለሬብ ተያይዘው ዘለሉ።

አራዳው መለስ ነብሳቸውን ገለባ ያድርገውና፣ ቀላል ለማለት ነው ገለባ ያልኩት “የኢትዮጵያ ሚሌኒየም” ሲከበር አላሙዲን ባስገነቡት የኮንቴነር ቤት ውስጥ ነው። ለመሆኑ እሱ ቦታ የማን እንደነበር ስማቸው በኖህ የሚጀምር አንድ ሃብታምና አዋቂ ሰው አፈላልጋችሁ ድረሱበት። ከሂልተን እስከ ሸራተን በተደረገ ግብዣ የተሰረቀ ፕሮጀክት ነው። በትክክልም ላሸብር እንደመጣሁ የገባኝ አሁን ነው። ኮንቴነርም ቢሆን ይሁን፣ ፕሮጀክቱ ድራማ ቢኖረውም ማን እንደሳቸው። በብድርም ቢሰራ ይሁን ከማለት ውጪ ምን ይባላል? አላሙዲ ግን ይገርማሉ እኮ። በሄክታር 0.20 ሳንቲም ግብር መክፈል አቅቷቸው ከሆለታ አበባ እርሻቸው እንዲነሱ የገበሬ ማህበር ደብዳቤ ጽፎላቸዋል ነበር። ብዙ ነገር አለ። ጥልዬ ምንድን ነበር ያለው “ሆድ ይፍጀው” ግን ለምን ሆድ ይፍጀው እኛን ራሳችንን ፍጅ-ት ያድርገን።

እናም አምባሳደር ዲና ሙፍቲ “ሙድ” አላቸው። ሚዲያውን ለባላንስ/ማመጣጠኛ ረድተውታል። አንድ ወዳጄ ሲተርባቸው ሳይደወልላቸው ከዋለ “ምነው ወዳጆቼ ጠፉ ብለው ይጨነቃሉ። ለመረጃ ነው፣ የታሰረ ጋዜጠኛ ወይም የተዘጋ ፕሬስ አለ?” ብለው የወዳጆቻቸውን ደህንነት ይጠይቃሉ። ግን እኮ ዝም ከማለት መናገር ይሻላል። ለተመደቡበት ቦታ ብቃት አላቸው። ኢህአዴግም በረከትም “ይመችህ” ያሏቸው ይመስላል። በተለይ ለሰነፍ ጋዜጠኞች መተዳደሪያ ሆነዋል። በነገራችን ላይ “ለመረጃ” በማለት የታሰሩ ጋዜጠኞችና የተዘጋ ፕሬስ እንዳለ ሲጠይቁ መልሱ “ምን ነጻ ፕሬስ አለና” የሚል ነው አሉ።

እዚህ ላይ ተመቸኝ። አዎ ነጻ ፕሬስ ወዴት ግድም ነው የሚገኘው? የት ነው ነጻ ሚዲያ ያለው። ከኢህአዴግን እየበላ የሚያመሰግን አለያም ሲመች እየተቸ ሲነቃነቅ ጥብቅና የሚቆም ወገንተኛ፣ ይህ አንዱ ነው። ሌላው ጭልጥ ብሎ መቃወም ነው። “ይህ ጥሩ ነው ግን” ብሎ የሚጀምር እንኳን የለም። ከጅምሩ ራሱ ኢህአዴግ በረከትን ልጓም የሌለው በትር ሰጥቶ ሊማርና ሊገራ የሚችለውን ጅምር አከሸፉት። ተወደደም ተጠላም ግን የተመጣጠነ ሚዲያ ግድ ነው። አለያ መጀመር እንጂ መጨረስ ይከብዳል።

ሃይለማርያም ሰለሜ ሰለሜ መጨፈር የሚችሉ አይመስለኝም ነበር። በነፈረቁበት ቤት እየተፍለቀለቁ ተምነሸነሹ – ደስ ይላል። ቤተ ክርስቲያናቸውና የሚያመልኩት መንፈስ ምን እንደሚላቸው ባለውቅም ሲጨፍሩ ደስ ብሎኛል። ቴድሮስ አድሃኖም እንደውም የቱሪዝምና ባህል ሚኒስትር ሁነው ኪነቱን ቢያነቃንቁ እመርጣለሁ። በነጻነት ፉት እያሉ እንዲሰሩ!! ሃይለ ማርያም ሲጨፍሩ በደስታ ስሜት ሆኜ መለስን ነፍስ ዘራሁባቸው። ህዝብ ፊት ቀርበው ዘፈን ምረጡ ሲባል “ሱዳንኛ” መርጠው ነው ከውዳቸው/ይቅርታ ውዳቸው የሌሎችም ውድ ነበሩ/ አብረው መስታዋት ቤት ውስጥ ሆነው በእጥርጥር የደነሱት!! የት? ሚሌኒየም አዳራሽ። አስቡት ኮንቴነር ቤት ውስጥ፣ በጋርዶች በተከበበ፣ በከባድ መሳሪያ በታጠረ፣ ጥይት በማይበሳው መስታዋት ውስጥ ሆኖ መዝናናት … ለትዝታ ያህል ነው። ታዲያ እሳቸው ሲሞቱ ያርማጮ ገበሬ ደረት መታ፣ ጸጉር ነጨ፣ የመንዲ እናት ደረቷን ደቃች። አዲስ አበባ በየቀበሌው ድንኳን ተጥሎ የቀበሌ የጸጥታ ሃላፊና ሊቀመንበርን “ነብስ ይማር፣ እግዜር ያጽናችሁ” እያለ ህዝብ ሲሰናበት … ጉድ እኮ ነው።

ቀጭኑ ዘ-ቄራ ኢህአዴግ “እንዲቀየር” የሚፈልገው እንዲህ ያሉ መለኪያ አልባ በሽታዎች ገሀድ ሲወጡ በዛው በጠንባራ ሚዲያ ለመመልከት በመጎምጅት ነው። እና መለስ በሱዳን ዘፈን ጨፈሩ!! ለምን? መሄድ የምትፈልጉ ሂዱና ጠይቋቸው። ቀጭኑ ሞትን ይፈራዋል። በድንገት ተስፈንጥሮ መሔድን አይወድም። አሁን የአራራ ሰዓት ነው!! ልሂድበት። እናንተም ተቀንጠሱ!! አምባሳደር ሙፍቲ ይመችዎት!!

ማሳሰቢያ፡- ከላይ ስለ አምባሳደርነት በምሳሌ ያነሳሁት የሙያ መጠሪያ ከአምባሳደር ዲናም ሙፍቲም ሆነ ከማውቃቸው አምባሳደሮች ጋር አንዳችም ግንኙነት የለውም። አምባሳደርነት የስራና የቦታው ሹመት እንጂ እንደ ሙያ ስም ለዘላለም ከሞት በኋላም የሚያገለግል አይደለም ለማለት ብቻ ነው!!

kechinu@goolgule.com

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Isak Amanuel says

    April 10, 2014 02:58 pm at 2:58 pm

    You are welcome Kechenu Z-Kera.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule