• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የደብሪቱ ወተት

September 27, 2013 09:28 pm by Editor Leave a Comment

ሰፈራችንን መሀል ለመሀል ሰንጥቆ ከሚያልፈው መንገድ በስተቀኝ ሃያ አንድ መኖሪያ ቤቶች ይገኛሉ። ከነዚህ ቤቶች ነዋሪዎች ውስጥ ከአብዛኛዎቹ ጋር የስጋ ዝምድና አለን። በተለይ በአንድ ግቢ ውስጥ የምንኖረው ስምንት ቤተሰቦች ደግሞ የቅርብ – በጣም የቅርብ ዘመዳሞች ነን።

በነዚህ ቤቶች ውስጥ አያቶች፣ እናቶች፣ አባቶች፣ አክስቶች፣ አጎቶች፣ አማትና አማቾች ሲኖሩ ከሁሉም የተውጣጣን የልጅ ልጆችም እንገኛለን። ከአጎቶቻችንና ከአክስቶታችን መካከል ሁለቱ ከኛ ዕድሜ ብዙ ስለማይርቁ ቀረቤታችን የጎላ ነው።

አሰግድ ገ/እግዚአብሔርና …

አሰግድ ቀልደኛ ነው። በማንኛውም ጊዜ በትንሹም በትልቁም ነገር እራሱን አዝናንቶ ሌላንም ለማስደሰት ይጥራል። የወጣለት ፀሐፊም ነው። እንደዛሬው የትያትር ጥበብ ሳይስፋፋ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ከሚሉ ጥቂት ተዋናዮች መካከልም አንዱ ነበር። አሰግድ አጎቴ ብቻ ሳይሆን ከጉርምስናዬ ማግስት ጀምሮ ምርጥ ጓደኛዬም ሆኖ ቆይቷል። ስለ አሰግድ ይቺን ካልኩ ይበቃኛል ወደቤታችን ድራማ ላምራ።

በቤታችን ውስጥ ቀንና ሰዓታቸው ያልተወሰነ፤ አጫጭር ድራማዎች በየጊዜው ይቀርባሉ። እነዚህ ድራማዎች አይጠኑም፤ ተዋናይ ተመርጦ አይመደብባቸውም፤ ፀሐፊና አዘጋጅ የላቸውም። አንዱ ባሻው መንገድ ይጀምረዋል፤ ሌላው አውቆም ሆነ ሳያውቅም ያግዘዋል፤ በቅብብሎሽ ወይም በግል ድራማው ተሠርቶ ይፈጸማል። ድራማው አስቂኝ ቢሆንም የማያቄሙ ተበዳዮችም ይኖሩታል። ብዙ ግዜ ድራማው በልጅ ልጆች የሚቀርብ ሲሆን፤ አሰግድ ድምቀት ሰጭ ሆኖ ያገለግላል።

አንድ ቀን እንዲህ ተሠራ። አንዷ አክስታችን ከመንደሩ ጠዋት ጠዋት የሚመጣላት ወተት በኪራይ ይዛለች። አከራይዋ ወ/ሮ ደብሪቱ ይባላሉ። ደብሪቱ ዝቅአድርጌ። ኃይለኛነታቸው በሰፊው ስለሚወራ ሰው ሁሉ በጥንቃቄ ነው የሚይዛቸው። የወተት ሂሳብ በወቅቱ ያልከፈለ የጭቃ ጅራፋቸውን ስለሚያወርዱበት ከቀኗ ውልፍች አይልም።

አክስቴ ዘንግታው ይሁን በሌላ አጋጣሚ የዛን ወር የወተት ሂሳብ ሳትከፍል ሦስት ቀን አልፏታል። በአራተኛው ቀን ጠዋት ወፍ ሳይንጫጫ የወ/ሮ ደብሪቱ ድምፅ በግቢያችን ውስጥ ተሰማ።

“ወ/ሮ አሰገደች እንደምን አደሩ? ምነው ምነው ትልቅ ስው አይደሉም እንዴ!? ከልጆቼ ጉሮሮ ነጥቄ ያከራየኽዎትን የወተት ሂሳብ ሊበሉኝ ነው? ወይስ ምን ሆነው ነው ሦስት ቀን ሙሉ ያላኩልኝ? ከኔ ከደሃይቱ ይሄን በልተው ምን ሊጠቀሙ ነው? ምነው ጡር አይሆንብዎትም ወይ? ነግሬዎታለሁ! ማንንም የምፈራ እንዳይመስልዎት፤ እንቢ ካሉ ሕግ ፊት ነው የምገትርዎት እከነሽና ደብሪቱ! ‘ግዛኝ ግዣኝ ብለው፣ ሊሸጠኝ አሰበኝ’ አለ ያገሬ ሰው! ዛሬ ባይልኩልኝ ወርድ ከራሴ …” የደብሪቱ ንግግር ማለቂያም የለው …

አክስቴ መግቢያ ቀዳዳ ጠፍቷታል፤ በሹክሹክታ ታወራ ጀመር “ይቺ ሴትዮ ጤናም የላት እንዴ?”

“ምን ጤናም የላት ትያለሽ? ለምንድነው! በወቅቱ ያልከፈልሽው?” ባለቤቷ ደነፋ።

“አንተ ደግሞ ዝም በል። ቢረሳ እንኳን ላኩልኝ ይባላል እንጂ፤ በጠዋት መጥቶ ምን ያስለፈልፋል።” አክስቴ ይበልጥ ጮኸች። የግቢው ቤተሰብ በሙሉ የሴትየዋን እሮሮ እየሰማ ነው። ማንም መልስ ሊመልስ አልፈለገም። ሁሉም አድፍጦ ዝም!

ደብሪቱ ብለው ብለው ድምጻቸው ሲጠፋ መሄዳቸው ስለታወቀ ከየቤቱ ብቅ ብቅ ማለት ተጀመረ። አክስቴ ከሁሉም ቀድማ ነበር ውጪውን የረገጠችው። የወንድሟ ልጅ በራፏ ላይ ቆሟል። “ውይ ሽመልስዬ እዚህ ምን ትሠራለህ? ይቺ እብድ በጠዋት ቀሰቀሰችህ አይደል?” አክስቴ ጥፋተኛነት ተሰምቷታል።

“ምን እኔን ብቻ የሰፈሩ ህዝብ በሙሉ እኮ ነው የተረበሸው! አዋጅ የሚናገሩ ነበር የሚመስሉት። ማን ያልሰማ አለ ብለሽ ነው” ሽመልስ ነገሩን ይበልጥ አደመቀው።

“ጉድ! ጉድ! ጉድ! አዋረደችን እኮ! እስቲ በለሊት መጥቶ አፍ መክፈት ምን አመጣው የሷን ብር ይዤ እንዳልጠፋ ነው? ወይስ ገንዘብ ሆነና እንዳልክድ …?”

“ኧረ! ሕግ ፊት እገትርሻለሁም ብለዋል!”

“ሂድ! አንተ ደግሞ ነገር አታንፏቅ፤ ለሃያ ብር ነው ሕግ ፊት የምትገትረኝ!?”

“እኔ ምን አውቃለሁ፤ ሲሉ የሰማሁትን ነው”

“እሷማ ምን ያላለችው አለ! ቆይ! ግድ የለም! እማደርገውን፤ እኔ ነኝ የማውቅ።” አክስቴ ወደ በሩ አመራች።

“እንዴ አሁን ልትሄጂ ነው እንዴ?” ሸመልስ ነገሩ አላማረውም።

“አሁንማ ምን ይሁን ብዬ እሄዳለሁ። እንደሷ አላበድኩ። እንደው እንዴት እንደገባች በሩን ለማየት እንጂ ቡናዬን ጠጥቼ ቀስ ብዬ እደርሳለሁ። የማደርገውን እኔ ነኝ የማውቅ። ሁለተኛ ግን የሷን ወተት … መርዝ ያስጠጣኝ።”

* * * * * * * * * * *

የአክስቴ ቡና ደርሶ ዘመድ ተሰብስቧል፤ ሁለት ሌሎች አክስቶቼና አንድ አጎቴ እስከሚስቱ ቦታቸውን ይዘዋል። አሰግድ አለ፤ ዙሪያውን በልጅ ልጆች ተከቧል። አያታችን በምርኩዛቸው መሬቱን እያንኳኩ ቀኝ እግራቸውን እየጎተቱ ገቡ። ሁሉም ብድግ ብሎ ተቀበላቸው። ማዕከላዊውን ቦታ ይዘው ከተቀመጡ በኋላ፤ “ጠዋት እንደዛ ትለፈልፍ የነበረችው ማናት?” ጥያቄ አቀረቡ።

“ወ/ሮ ደብሪቱ ናታ” አክስቴ ወ/ሮን ጠበቅ አደረገቻት።

“ምን ይሁን ብላ?” አባባ ነገሩ ገርሟቸዋል።

“አልሰሙም እንዴ ወተት አከራይዋ …

“እኮ ምን ይሁን ብላ መጣች?” አላስጨረሷትም።

“የወተት ኪራይ ሳትከፍይ ዘገየሽ ብላ፤ ልትሳደብ ነዋ! ጨፈረችብኝ እኮ! …”

“ለመሆኑ! በሩን ማን ከፈተላት?”

“እንጃላት! እጇን አስገብታ ከፍታ ወይም አንዱ ወጥቶ ይሆናላ”

“ገብቶ ማለትሽ ነው?” አባባ ወደ አሰግድ ተመለከቱ።

አሰግድ ሽሙጡ ቢገባውም መልስ ሊሰጥ አልፈለገም። “ደግሞ እኮ ስትናገር አንገቷን የታነቀች ነው የምትመስል” አለ አሰግድ፤ የሴትዬዋ ነገር እንዲሰፋ ፈልጓል፤ ሁሉም በጅምላ ሳቀ።

“ኧረ! የሚያንቅ ይነቃትና፤ ስትታይም የታነቀች ነው የምትመስል” የእህቷ መሰደብ ያንገበገባት ትንሿ አክስታችን ነበረች። የአሰግድ ሳቅ ጎልቶ ወጣ።

“አዎን ሳቅ አንተ! ጅብም ሲጎትተኝ ብታይ ሳትስቅ አትቀር። አይ! የኛ ወንድም!” አክስቴ ተናደደችበት።

“አንችስ ለምን ሳትከፍይ ቆየሽ?” አያታችን ሌላ ጥያቄ ወረወሩ።

“እርስት አደረኩት አባብዬ”

“እርስት አደረኩት! አንቺ የረሳሽ እንደሆን እሷም መርሳት አለባት?” ሁሉም ሳቁን ለቀቀው። አባባም በራሳቸው ንግግር ይስቁ ጀመር። ወርቅ ጥርሳቸው ከግራና ከቀኝ እንደ አንፖል ያበራል።

“እናስ! የሆነ እንደሆን ሀገር ጥዬ አልኮበልል፤ በጠዋት መጥቶ መለፍለፍን ምን አመጣው? ቆይ! ግድየለም! የማደርገውን እኔ ነኝ የማውቅ …”

“አክስቴ ገንዘባቸውን ወደዚያ ወርውሪላቸው እንጂ ምንም እንዳትናገሪ” ሽመልስ ጣልቃ ገባ።

“ለምንድነው የማልናገር? አንተን ደግሞ የሷ ጠበቃ ያደረገህ ማነው? ፎቃቃ”

“አይ! ወንድማቸው የአብዮት ጥበቃ ሊቀመንበር ናቸው ሲባል ስለሰማሁ …”

“ታድያ! የሆነስ እንደሆን በጠዋት እየተነሳሽ ሰው ስደቢ ብሎ ፈቅዶላታል ማለት ነው? ማነው ከዘሯ የነገሠ?” ትንሿ አክስት ተንጣጣች። አክስቴ እየተናገረች ሥራዋን አላቋረጠችም። ቁርስ አቅርባ ተበላ። አቦል ቡና ተዳረሰ፤ አሁን ሁሉም ጎኑ ካለው ሰው ጋር ጨዋታ ጀምሯል። አሰግድ ከኛ ጋር እየቀለደ ነው፤ አባባ ጣቶቻቸውን አቆላልፈው ሁለት አውራ ጣቶቻቸውን ማገለባበጥ ይዘዋል።

ሽመልስ ገባ ወጣ ይላል። አክስቴ አልወደደችለትም። “መቀመጫህ ላይ መርፌ የተሰካ ይመስል፤ ምን ያንቆራጥጥሃል? ቡና እያፈላሁ የሚክለፈለፍብኝ አልወድም … ትቀመጥ እንደሆን ተቀመጥ!” ሸመልስ ውጭውን መርጦ ወጣ።

ሁለተኛውና ሦስተኛው ቡና ተፈልቶ ተጠጣ። አክስቴ ስኒውን አነሳስታ፣ እቃውን አጣጥባ ልብሷን ለባብሳ ተነሳች። መሃረቧ ላይ ብር ቋጥራ ያዘች። ወ/ሮ ደብሬ ዛሬ ጉዷ ፈልቷል። ሁለቱ ሌሎቹ አክስቶቼ በዛው የምንደርስበት አለ ብለው ከአክስቴ ጋር ለመሄድ እየጠበቋት ነው። አሰግድ ሥራው ሊሄድ ተዘጋጅቷል። እግረ መንገዱን ግን የደብሬን ጉዳይ ለማየት ፈልጓል። አብዛኛው የልጅ ልጅ በር ላይ እንደዘብ ቆሞ ይሳሳቃል።

በዚህ መሀል ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ። የደብሬ ልጅ እንደወትሮዋ ወተቱን በነጭ ጨርቅ ሸፍና በራፋችን ላይ ቆማ ታየች። አክስቴ እንደዛ ተናግረው ካሁን ወዲያ ወ/ሮ ደብሬ ወተት ይልካሉ የሚል ግምት አልነበራትም፤ አብዛኛውም የሚያስበው ይሄንኑ ነው።

አክስቴ ልጅቷን እንደጉድ እያየቻት “አንቺ! …” ብላ ልትናገር ስትጀምር ሸመልስ አንዳች የሚያህል ድንጋይ ይዞ እግሯ ላይ ተከመረ።

“ምንድንነው ነገሩ?” አክስቴ አንባረቀች። ሁሉም ገርሞት ሽመልስ ላይ ዓይኑን ተክሏል።

“አክስቴ ይቅር በይኝ፤ ይቅር በይኝ” ድንጋዩን አስቀምጦ እግሯን አንቆ ያዘ።

“ምንድነው ነገሩ? ጤናም አልያዘኽ? ምኑን ነው ይቅር የምልህ? ኧረ! ይሄ ልጅ አንድ በሉልኝ …” አክስቴ ቆጣ ማለት ጀመረች።

ሁሉም በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር፤ ምንድነው? ምን አድርገሃል? አባባ ተነስተው ጎኑን በምርኩዛቸው ጎንተል አደረጉት። ተናደዋል። “ምንድንነው ያደረግኸው? አትናገርም?”

ሽመልስ ይሄን ጊዜ ተነስቶ ቆመ። ፊቱ ፀሐይ ወጥቶ የሚዘንብ ቀን መስሏል። ሳቅም ድንጋጤም ይዞታል።

“ምንድነው ምን አድርገኻል?” የአክስቴ የግንባር ቆዳ ተሰበሰበ።

“ጠዋት …”

“እ … ጠዋት”

“እማማ ደብሬ”

“እ … እማማ ደብሬ ትናገር እንደሆን ተናገር” አክስቴ ይበልጥ ተናደደች።

“እማማ ደብሬ አልመጡም።”

“ታድያ! ማነው እንደዛ ይለፈልፍ የነበረው? እኔ ነኝ እንዳትለኝ ብቻ” አክስቴ አፏን ይዛ ዓይኗን አፈጠጠች።

“አዎን! እኔ ነኝ አክስትዬ ይቅርታ አድርጊልኝ” እንደገና እግሯን አንቆ ያዘ። ሁሉም ሳቁን ለቀቀው አክስቴ እንደመሳቅ እያለች ከእግሯ ላይ ካነሳችው በኋላ እጁን ቀጨም አድርጋ ይዛ “እስቲ እንደጠዋቱ ተናገር” አለችው።

ሽመልስ በአንድ እጁ ጉሮሮውን ይዞ ድምፁን አስተካክሎ መናገር ጀመረ፤ “ወ/ሮ እጅጋየሁ እንደምን አደሩ? ወር ሙሉ ወተቴን ጠጥተው ገንዘቤን ያላኩልኝ ምን ሆነው ነው? ምነው ነውር እማይደል …?”

ጠዋት የተሰማው የደብሪቱ ድምፅ በድጋሚ ግቢውን ሞላው።

(Photo: ILRI – ወ/ሮ ደብሪቱ አይደሉም)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule