• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ

August 19, 2016 09:15 am by Editor 1 Comment

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ

የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር

የአቋም መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን።

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ዙሪያ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት መነሻ በማድረግ ያወጣውን መግለጫ በመደገፍ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር የተሰባሰብን ተወካዮች ባካሄድነው አስቸኳይ ጉባኤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በሰፊው ተመልክተን የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ምዕ. ፪ ከቁ. ፲፰ ጀምሮ “ልጆቼ ሆይ ይህቺ የመጨረሻዋ ሰዓት ናት እኛም የመጨረሻዋ ሰዓት እንደሆነች አውቀን በአንድነት እንቁም” ብሎ ባስተማረን መንፈሳዊ መሪ ቃል መሠረት የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ እንዳሻው እየዘረፍ እና እየገደለ ያለው በደም የተጨማለቀውን ወያኔን በአንድነት ሆነን በቃ ልንለው ይገባል።

የእናት ሀገሩ ፍቅር እንደ እግር እሳት የሚያቃጥለው ወጣት ትውልድ እምቢ ለሀገሬ! እምቢ ለነፃነቴ! ብሎ ግንፍሎ ወጥቷል። በአንፃሩ ሥልጣን ያሰከረውና ገንዘብ ያሳበደው ወያኔ ያገኘውን ሁሉ መግደልና መጨፍጨፉን ቀጥሏል። ሁሉም እንደሚያውቀው ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት የተጣሰባት፣ የዲሞክራሲ ጭላንጭል የጠፋባት፣ የዘር መድልኦ አገዛዝ የሰፈነባት የአምባ ገነኖች መፈንጫ ሆናለች። የወያኔ የግፍ አገዛዝ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለድህነት ለርሃብ ለዕርዛት ለስደትና ለመሐይምነት ዳርጎታል።

ውድ ኢትዮጵያዊ ወገን!

“ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንደሚባለው የኢትዮጵያ ውድ ልጆች በየቀኑ በወያኔ ጥይት መቀላት ብቻ ሳይሆን በወያኔ ቆመጥ ተደብድበው እየተገደሉ ደማቸው እንደ ጅረት ውሃ እየፈሰሰ ከሞት የተረፉትም ለቀጣይ ግድያ እንዲጠባበቁ በጅምላ እየታሰሩ ናቸው። የዘረኛው ወያኔ የግፍ አገዛዝ ፅዋው ሞልቶ ከፈሰሰ ቆዬ። በመሆኑም እኛ በሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ-ቤተክርስቲያን መዋቅር በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሥር የተሰባሰብነው የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማኅበር አባላት ይህን የአቋም መግለጫ በጋራ አውጥተናል።

፩ኛ/ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሕ.ወ.ሓ.ት የባርነት ቀንበር ተላቆ የሰላምና የነፃነት አየር እንዲተነፍስ ትግሉን በየአቅጣጫው እንዲያፋፍም ጥሪ እናቀርባለን። እኛም በማንኛውም ረገድ አስተዋጸኦ ለማበርከት ቃል እንገባለን።

፪ኛ/ አረመኔውንና ዘረኛውን የወያኔ ቡድን ለማንበርከክ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በተደራጀና በተቃናጀ መልኩ በየቦታው ዘብ ይቁም።

፫ኛ/ የሀገር አለኝታ የወገን መከታ የሆነው ወጣቱ ትውልድ እንደ ጽጌረዳ አበባ በየቦታው እየረገፈ ነው። እናት ልጇን ተነጥቃ ግንባሩ በአጋዚ ጥይት ተበርቅሶ ሲወድቅ እያየች የወላድ አንጀቷ አልችል ብሏት የሀገር ያለህ፤ የወገን ያለህ፤ ድረሱልኝ እያለች ትጮሃለች። ከዚህ የበለጠ ምድራዊ ገሀነም ምን ሊኖር ይችላል? በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሰን ይህንን ዘረኛና ገዳይ ቡድን ልናስወግደው ይገባል በማለት ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

፬ኛ/ ሀገር በቀል የሆነው ከሀዲ ወራሪ ኃይል ቀደም ብሎ በነደፈው የከፋፍለህ ግዛ ያረጀና ያፈጀ ሥልት ሊሠራለት አልቻለም። ሕዝቡም ነቅቶበታል። አንድ ለአምስት በሚል አደረጃጀት ያዋቅረውን የሰሜን ኮሪያ ኮምኒስታዊ የአፈና አገዛዝ ሰንሰለት  ኢትዮጵያዊ ወገናችን በጣጥሶ ጥሎት በአንድነት ፀንቶ ቆሟል። ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ እስከሚሆን ድረስ የነፃነት ትግሉ ይቀጥላል። እኛም ድጋፋችንን እንቀጥላለን።

፭ኛ/ ወቅቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች የፍልሰታ ፆምን ምክንያት በማድረግ በየቤተክርስቲያኑ በጸሎትና በሱባኤ ላይ ናቸው። በስቃይና በመከራ ላይ ያሉትን ወገኖቻቸውንም ዕለት በዕለት በጸሎት ያስባሉ።በአንፃሩ ግን ወያኔ በሃይማኖትና በእምነት ውስጥ ገብቶ ታጋይ ካድሬዎቹን በካሕናት ስም እያሰማራ ቤተክርስቲያናችንን እያመሰ ይገኛል። እውነተኛ የሃይማኖት አባቶች የሆናችሁ የወያኔን አፀያፊና ዘግናኝ ድርጊት ልታወግዙ ይገባል። በኢትዮጵያም ሆነ በየትኛውም የዓለም ክፍል የምትገኙ አባቶች ሕዝባዊ ወገናዊነታችሁን የምትገልጹበት ጊዜ አሁን ነው እንላለን።

እግዚአብሔ አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቅ ሕዝቧንም ይባርክ። አሜን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Abebe says

    August 22, 2016 02:52 pm at 2:52 pm

    አባቶች ካስተማሩኝ እንጅ መፅሀፍ ቅዱሳዊ እውቀት የለኝም። መቼም “ህገ-ወጦቹ አባቶች ስላስተማሩህ ነው፤ ህጋዊዎቹ አባቶች እኛ ነን” እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ለመሆኑ የሀይማኖት አባቶች መንግስትን ለመጣል የአቋም መግለጫ እንዲያወጡ ኢየሱስ ክርስቶስ አስምሯቸዋልን? የቀደሙት አባቶቻችንስ በፅናት አንገታቸውን ለሰይፍ ሰጡ እንጂ እነሱ ሸሽተው ልጆቻቸውን ሙቱ ብለው ነበርን? እናንተ ታዲያ…

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule