• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ

August 19, 2016 09:15 am by Editor 1 Comment

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ

የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር

የአቋም መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን።

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ዙሪያ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት መነሻ በማድረግ ያወጣውን መግለጫ በመደገፍ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር የተሰባሰብን ተወካዮች ባካሄድነው አስቸኳይ ጉባኤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በሰፊው ተመልክተን የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ምዕ. ፪ ከቁ. ፲፰ ጀምሮ “ልጆቼ ሆይ ይህቺ የመጨረሻዋ ሰዓት ናት እኛም የመጨረሻዋ ሰዓት እንደሆነች አውቀን በአንድነት እንቁም” ብሎ ባስተማረን መንፈሳዊ መሪ ቃል መሠረት የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ እንዳሻው እየዘረፍ እና እየገደለ ያለው በደም የተጨማለቀውን ወያኔን በአንድነት ሆነን በቃ ልንለው ይገባል።

የእናት ሀገሩ ፍቅር እንደ እግር እሳት የሚያቃጥለው ወጣት ትውልድ እምቢ ለሀገሬ! እምቢ ለነፃነቴ! ብሎ ግንፍሎ ወጥቷል። በአንፃሩ ሥልጣን ያሰከረውና ገንዘብ ያሳበደው ወያኔ ያገኘውን ሁሉ መግደልና መጨፍጨፉን ቀጥሏል። ሁሉም እንደሚያውቀው ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት የተጣሰባት፣ የዲሞክራሲ ጭላንጭል የጠፋባት፣ የዘር መድልኦ አገዛዝ የሰፈነባት የአምባ ገነኖች መፈንጫ ሆናለች። የወያኔ የግፍ አገዛዝ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለድህነት ለርሃብ ለዕርዛት ለስደትና ለመሐይምነት ዳርጎታል።

ውድ ኢትዮጵያዊ ወገን!

“ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንደሚባለው የኢትዮጵያ ውድ ልጆች በየቀኑ በወያኔ ጥይት መቀላት ብቻ ሳይሆን በወያኔ ቆመጥ ተደብድበው እየተገደሉ ደማቸው እንደ ጅረት ውሃ እየፈሰሰ ከሞት የተረፉትም ለቀጣይ ግድያ እንዲጠባበቁ በጅምላ እየታሰሩ ናቸው። የዘረኛው ወያኔ የግፍ አገዛዝ ፅዋው ሞልቶ ከፈሰሰ ቆዬ። በመሆኑም እኛ በሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ-ቤተክርስቲያን መዋቅር በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሥር የተሰባሰብነው የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማኅበር አባላት ይህን የአቋም መግለጫ በጋራ አውጥተናል።

፩ኛ/ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሕ.ወ.ሓ.ት የባርነት ቀንበር ተላቆ የሰላምና የነፃነት አየር እንዲተነፍስ ትግሉን በየአቅጣጫው እንዲያፋፍም ጥሪ እናቀርባለን። እኛም በማንኛውም ረገድ አስተዋጸኦ ለማበርከት ቃል እንገባለን።

፪ኛ/ አረመኔውንና ዘረኛውን የወያኔ ቡድን ለማንበርከክ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በተደራጀና በተቃናጀ መልኩ በየቦታው ዘብ ይቁም።

፫ኛ/ የሀገር አለኝታ የወገን መከታ የሆነው ወጣቱ ትውልድ እንደ ጽጌረዳ አበባ በየቦታው እየረገፈ ነው። እናት ልጇን ተነጥቃ ግንባሩ በአጋዚ ጥይት ተበርቅሶ ሲወድቅ እያየች የወላድ አንጀቷ አልችል ብሏት የሀገር ያለህ፤ የወገን ያለህ፤ ድረሱልኝ እያለች ትጮሃለች። ከዚህ የበለጠ ምድራዊ ገሀነም ምን ሊኖር ይችላል? በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሰን ይህንን ዘረኛና ገዳይ ቡድን ልናስወግደው ይገባል በማለት ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

፬ኛ/ ሀገር በቀል የሆነው ከሀዲ ወራሪ ኃይል ቀደም ብሎ በነደፈው የከፋፍለህ ግዛ ያረጀና ያፈጀ ሥልት ሊሠራለት አልቻለም። ሕዝቡም ነቅቶበታል። አንድ ለአምስት በሚል አደረጃጀት ያዋቅረውን የሰሜን ኮሪያ ኮምኒስታዊ የአፈና አገዛዝ ሰንሰለት  ኢትዮጵያዊ ወገናችን በጣጥሶ ጥሎት በአንድነት ፀንቶ ቆሟል። ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ እስከሚሆን ድረስ የነፃነት ትግሉ ይቀጥላል። እኛም ድጋፋችንን እንቀጥላለን።

፭ኛ/ ወቅቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች የፍልሰታ ፆምን ምክንያት በማድረግ በየቤተክርስቲያኑ በጸሎትና በሱባኤ ላይ ናቸው። በስቃይና በመከራ ላይ ያሉትን ወገኖቻቸውንም ዕለት በዕለት በጸሎት ያስባሉ።በአንፃሩ ግን ወያኔ በሃይማኖትና በእምነት ውስጥ ገብቶ ታጋይ ካድሬዎቹን በካሕናት ስም እያሰማራ ቤተክርስቲያናችንን እያመሰ ይገኛል። እውነተኛ የሃይማኖት አባቶች የሆናችሁ የወያኔን አፀያፊና ዘግናኝ ድርጊት ልታወግዙ ይገባል። በኢትዮጵያም ሆነ በየትኛውም የዓለም ክፍል የምትገኙ አባቶች ሕዝባዊ ወገናዊነታችሁን የምትገልጹበት ጊዜ አሁን ነው እንላለን።

እግዚአብሔ አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቅ ሕዝቧንም ይባርክ። አሜን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Abebe says

    August 22, 2016 02:52 pm at 2:52 pm

    አባቶች ካስተማሩኝ እንጅ መፅሀፍ ቅዱሳዊ እውቀት የለኝም። መቼም “ህገ-ወጦቹ አባቶች ስላስተማሩህ ነው፤ ህጋዊዎቹ አባቶች እኛ ነን” እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ለመሆኑ የሀይማኖት አባቶች መንግስትን ለመጣል የአቋም መግለጫ እንዲያወጡ ኢየሱስ ክርስቶስ አስምሯቸዋልን? የቀደሙት አባቶቻችንስ በፅናት አንገታቸውን ለሰይፍ ሰጡ እንጂ እነሱ ሸሽተው ልጆቻቸውን ሙቱ ብለው ነበርን? እናንተ ታዲያ…

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule