• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጉቦ በመቀበል እስረኞችን የለቀቁ ታሰሩ!

December 16, 2013 06:24 am by Editor 2 Comments

ከ300 እስከ 500 ሺህ ብር እየተቀበሉ በሀሰተኛ ሰነድ ታራሚዎችን ከማረሚያ እንዲወጡ አስደርገዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሶስት የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት የስራ ሀላፊዎችና አምስት ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ተጠርጣሪዎቹ ኦፊሰር ገብረመድህን አረጋ፣ ረዳት ኦፊሰር ኢሳያስ ከበደና ዋርደር ኢብራሂም መሀመድ ሲሆኑ፥ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት የእስረኞች አስተዳደር የስራ ሃላፊዎችና ሰራተኞች ሆነው ሲሰሩ የነበሩ ናቸው።

ከእነዚህ የስራ ሃላፊዎች ጋር የጥቅም ትስስር በመፍጠር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የተቀሩት ግለሰቦች ደግሞ ፥ በንግድ ስራ ይተዳደር የነበረው አቶ ሰለሞን ገለታ፣ አቶ ብሩክ ሀይሌ፣ ወይዘሪት ሳባ ገብረሚካኤል፣ አቶ ናታን ዘላለምና አቶ ቴዎድሮስ ግደይ ናቸው።

የፌደራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን  መርማሪ ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ የወንጀል ችሎት ባቀረበው የጊዜ ቀጠሮ ማመልከቻ ላይ እንደተመለከተው፥ ከሳባ ገብረሚካኤል ውጪ እነዚህ በንግድ ስራ ይተዳደሩ የነበሩ ግለሰቦች ቀደም ሲል በተለያዩ ወንጀሎች ተፈርዶባቸውና በማረሚያ ቤት የእስራት ጊዜያቸውን ጨርሰው የወጡ ናቸው።

እንደ መርማሪው ማመልከቻ ሳባ ገብረሚካኤል በኮምፒውተር ፅሁፍ እያገዘቻቸው፥ በንግድ ስራ የሚተዳደሩት ግለሰቦችም ከፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ታራሚዎች ከእስር የሚፈቱበትን ትዕዛዝ በሀሰተኛ መንገድ በማዘጋጀት እንዲሁም በሀሰተኛ ፊርማ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ማህተም በማስመሰል አዘጋጅተዋል።

በማረሚያ ቤት የሚገኙና ቅጣታቸው ከአምስት ዓመት በታች ለሆነ 300 ሺህ ብር ከዚያ በላይ ከሆነ ደግሞ 500 ሺህ ብር እየተቀበሉ ፥ ከ11 በላይ ታራሚዎችን በዚህ ሀሰተኛ ሰነድ ከእስር እንዲለቀቁ አድርገዋል ይላል።

የሚያገኙትንም ገንዘብ ለኦፊሰር ገብረመድህን አረጋ፣ ረዳት ኦፊሰር ኢሳያስ ከበደና ዋርደር ኢብራሂም መሀመድ ለተባሉት የማረሚያ ቤቱ የስራ ሀላፊዎች በመስጠታቸው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

በመርማሪው ማመልከቻ መሰረት እነዚህ የስራ ሃላፊዎች የነበሩ ተጠርጣሪዎች የእስር መፍቻ ደብዳቤው በሀሰተኛ መንገድ የተዘጋጀ እንደሆነ እያወቁ ታራሚዎች እንዲፈቱ በማድረጋቸው ስልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ከሶስቱ የስራ ሀላፊዎች ውስጥ ኦፊሰር ገብረመድህን አረጋ ሀሰተኛ የእስር መፍቻ ካቀረበ አንድ ታራሚ 40 ሺህ ብር መቀበሉ ተመልክቷል።

የጊዜ ቀጠሮ ማመልከቻውን የተቀበለው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ የወንጀል ችሎት ተጠርጣሪዎቹ ያቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ ቢለቀቁ መረጃ ያጠፋሉ የሚለውን የመርማሪውን ተቃውሞ በመቀበል ፥ ጉዳያቸውን ማረሚያ ሆነው ይከታተሉ ብሏል። (ኤፍ.ቢ.ሲ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    December 17, 2013 09:31 pm at 9:31 pm

    << በአድሃሪውና ባላባቱ ሥርዓት ፩ ጆንያ ከሰል፣ ፩ስልቻ ጥሬ እህልና ፭ ክንድ ጋቢ አጅ መንሻ ፩ ቀይ አወራዶሮን ጨምሮ ፤ በደረግ ዘመነ መንግስት ግን ተሻሽሎ በወጣው ስም የማዛወር ሥልጣንና ኀላፊነት ማናቸውም ከ፳ሺህ ብር የሚደርሱ ጉዳይ ማስፈጸሚያ ሁሉ " ጉቦ "ተብለው እንዲጠሩ ከዚያ በላይ የሚቀበሉና የሚያቀባብሉ ግን የፓርቲ አባላትና ከፍተኛ ጋዶች የሚነጋገሩበት ተብሎ ይጠቀስ ነበር።

    *አሁንማ 'በአብዮታዊ ዴሞክራሲ' 'ልማታዊ መንገስት' ማናቸውም ከ፩ሚሊየን ብር በታች የሆኑ የጉዳይ ማስፈፀሚያ ድጎማዎች ሁሉ የቀድሞ ሥማቸውን 'ጉቦ' ሆኖ እንዲቀጥሉ። ከ፩ሚሊየንና ከዚያም በላይ የማይንቀሳቀስ ንበረትን ጨምሮ የሚሰጡ የአጅም የእግርም ማንሻዎች ሁሉ "ሙስና" ተብለው እንዲንቆለጳጰሱ በመወጣው መመሪያ መሠረት… የቀድሞውን ሥርዓት ናቀፈቂዎች በሚያደርጉት ሴራ ሙስናን በጉቦ በማሸበርና ህገ መንግስቱንና(የህወአት ማኒፌስቶ) ህገመንግሰታዊ የሙና ሥርዓቱን ለመናድ፣ የሚያደርጉትን ጥረት ከምንጩ ለማድረቅ በተደረገው የሙሰኞች ያላሰለሰ ትብብርና እርዳታ ከ፫፻እስከ ፭፻ሺህ ብር የተቀበሉ ፫ አሸባሪ ጉቦኞች የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት የስራ ሀላፊዎችና ፭ ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር ውለው ፍርድ ቤት ቀረቡ።ከእነዚህ የስራ ሃላፊዎች ጋር የጥቅም ትስስር በመፍጠር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የተቀሩት ግለሰቦች ደግሞ ፥ በንግድ ስራ ይተዳደር የነበረው አቶ ሰለሞን ገለታ፣ አቶ ብሩክ ሀይሌ፣ ወይዘሪት ሳባ ገብረሚካኤል፣ አቶ ናታን ዘላለምና አቶ ቴዎድሮስ ግደይ ናቸው።

    * ከሳባ ገብረሚካኤል ውጪ እነዚህ በንግድ ስራ ይተዳደሩ የነበሩ ግለሰቦች ቀደም ሲል በተለያዩ ወንጀሎች ተፈርዶባቸውና በማረሚያ ቤት የእስራት ጊዜያቸውን ጨርሰው የወጡ ናቸው። ታላቅ የሥራ ልምድ ያካበቱ…ድሮስ ድልድይ አፍረሽ ልማታዊ መንግስት ሲል ምን ማለት ነበር በለው!
    *ሳባ ገብረሚካኤል በኮምፒውተር ፅሁፍ እያገዘቻቸው፥ በንግድ ስራ የሚተዳደሩት ግለሰቦችም ከፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ታራሚዎች ከእስር የሚፈቱበትን ትዕዛዝ በሀሰተኛ መንገድ በማዘጋጀት እንዲሁም በሀሰተኛ ፊርማ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ማህተም በማስመሰል አዘጋጅተዋል።(ሥራ ክፈቱ ብለዋቸ አፋቸውን ይክፈቱ? ከሶስቱ የስራ ሀላፊዎች ውስጥ ኦፊሰር ገብረመድህን አረጋ ሀሰተኛ የእስር መፍቻ ካቀረበ አንድ ታራሚ ፵ ሺህ ብር መቀበሉ! ምን አላት?ይህ የወ/ሮ ታጋይ አዜብ በአሜሪካ የተሰራላቸው ቤት ውሃና መበራት ክፍያ ናት። በሕግ አመላክ የእስር መፍቻ ደብዳቤ ይዘጋጅለትና በነፃ ይፈታ! ! ለነገሩ ፵ሺህ በ፷፻፪፻ ሲሰላ የአቶ መለስ የ፮ ወር ያልተጣራ ገቢ ማለት አደለምን!
    **፪፱፻፲፭ እንዲሁ ከአደጉ ሀገሮች ጎን መሰለፍ አለን? ምነው ሸዋ ተስካር ነው ሠረግ? እራሱ ህወአተሻቢያ ቀበሮ ጉድጋድ ሆኖ ሲሰራበት የኖረው አደለምን እነዚህስ ሥልጠና ወስደው የለምን?ባንክ መዝረፍ ፣ጎተራ መገልበጥ፣ የገበሬ ሚስት መድፈር በህወአጠሻቢያ የተጀመረ በፋውንዴሽኑ ከተውልድ ተውልድ እንዲተላላፍ ለምርምርና ጥናት ተቀብሮ የለምን!? ሀገር፣ ዳርድንበር፣ ወደብ፣ ሰንደቅ፣ መስደብና ማዋረድ መሸጥ የተጀመረው " በሰጥቶ መቀበል ማኒፌስቶ" ለም መሬት ለጎረቤት ሀገራት የሚቸረው "በታላቁ የሙስና ራዕይ" አደለምን!?
    "አልተናገርኩም ወይ እዚሁ ብቅ ብዬ
    የሙስና ሥርዓት ሻቢያህወአት ወሮ በላዬ !?
    ኢትዮጵያ ፡ ነጋዴው ፣ፖለቲከኛው፣ አድርባይ ምሁር፣ ካድሬ፣መከላከያው፣ብሄርተኛው፣ ኢንቨስተርና ዲያስፖራ በመኖፖል የጠረነፋት ክልል ነች።!እናንት በመጠላላፍ በመፈቃቀርና በመቻቻል ተጠርንፋችሁ የድሃ ደም የምትመጠምጡ፣ ጣታችሁን ወደ ሻቢያህወአት ቀስረችሁ እጃችሁ ድሃው ሕዝብ ንብረትና ገንዘብ ላይ የተጫነ፣እዳይጽፍ፣ እንዳይናገር፣ እንዳይሰባሰብ ለገቢ ምንጫችሁ ያዘናችሁ፣ ከመሀል ሆናችሁ የምትበትኑ ሹምባሾች፣ የቁራ ጩኸት የአዞ እንባ እያነባችሁ ዘረኝነትን ጎጠኝነትን የምትሰብኩ፣ ስንጨቆንና ተረስተን ነበር እያላችሁ… አሁን የራሳችሁን ብሔራችሁን የረሳችሁ አድርባዮች ሁሉ እባካችሁ አታወናብዱ ተነሱ!!የሙሰኞች ወታቦ(ሞኖፖሊው) ይፍረስ! ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ ከህዝቦቿ ጋር ለዘለዓለም ትኑር!!

    Reply
  2. Shaleka Kebede says

    December 19, 2013 06:37 am at 6:37 am

    ኦፊሰር ገብረመድህን አረጋ፣ ረዳት ኦፊሰር ኢሳያስ ከበደና ዋርደር ኢብራሂም መሀመድ ; አቶ ብሩክ ሀይሌ፣ ወይዘሪት ሳባ ገብረሚካኤል፣ አቶ ናታን ዘላለምና አቶ ቴዎድሮስ ግደይ
    Anything in commen here … Or is it just me ? Weyne Wegen , Weyne Ager, both have ended up being a playgroung for the ” ድልድይ አፍረሽ ልማታዊ መንግስት ” . !!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule