• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ አባይ ግድብ “አድርባይ” እንሁን?

March 30, 2013 05:51 am by Editor Leave a Comment

ሰሞኑን ኢህአዴግ ጉባኤውን ሲጨርስ “አድርባይነት አሰጋኝ” ብሎናል። አባላቶቼ አድርባይ ሆነዋልና በዚህ ከቀጠልኩ እሰምጣለሁ የሚል ስጋት እንዳለበትም አስታውቆናል። ከፍርሃቻው ብዛት የተነሳ አድርባይነትን ለመዋጋትና “መድረክ ላይ ለመጥለፍ” በቁርጠኛነት እንታገላለን ብለው አቋማቸውን ነግረውናል። የሚገርመው ግን አድርባይነትን የፈጠረና ያነገሰው ራሱ ኢህአዴግ መሆኑን መዘንጋቱ ነው።

ኢህአዴግ አድርባይ ሚዲያዎች አሉት። አድርባይ ባለሃብቶች አሉት። ኢህአዴግ አድርባይ የኔቢጤዎች አሉት። ኢህአዴግ አድርባይና የማደናገሪያ ፕሮጀክቶች አሉት። ኢህአዴግ አድርባይ ድርጅቶች እንጂ ነጻ ድርጅቶች የሉትም። ኢህአዴግ አድርባይ ባለስልጣናት እንጂ ነጻ አመራሮች የሉትም። ሁሉም አድርባዮች ተጠሪነታቸው ለህወሃት ስለሆነ ተጠያቂውም ራሱ የኢህአዴግ ሾፌር ህወሃት እንጂ ሌሎች ሊሆኑ አይገባም። “ፈጣሪያቸው” የሚገመግማቸው፣ እነሱም አምነው የሚገመገሙት ታማኝ አድርባይ ስለሆኑ ብቻ ነው።

አሁን እየተለመደ የመጣው የመፈክርና የቀረርቶ ጉዳይ አጥወልውሎ የሚጥል ደረጃ ያደረሰንም ለዚህ ነው። ቃላት ማምረትና ማራባት የተካነበት ኢህአዴግ በየጊዜው የሚፈለፍላቸው ቃላቶች እያንገፈገፉን ነው። በተለይም ታላላቅ ዋጋ ባላቸው “ውድ” ቃላቶች ላይ አደጋ እየፈጠረም እንደሆነ ይሰማናል፤  ይጫወትባቸዋል። አድርባይ ሚዲያዎችና አድርባይ ጋዜጠኞች የማከፋፈሉን ስራ ይሰራሉ። ይህ በአገር ደረጃ የተንሰራፋው አድርባይነት ለኢህአዴግ ስጋቱ አይደለም፤ ኩራቱ እንጂ!!

ይህንን ያነሳነው ወድደን አይደለም። ባለፈው ሳምንት ባወጣነው የአባይ ግድብ ከግማሽ በላይ የኢትዮጵያ አይደለም የሚል ዜና አድርባይ እንድንሆን ያሳሰቡን በመኖራቸው ነው። ስለ አባይ ግድብ ያሰራጨነው ዜና ያስደነገጣቸው በርካቶች ናቸው። የአባይ ግድብ መገደብ እውን መሆን አለበት። አባይ ተገድቦ አገር መልማት አለበት። አባይን ለልማት ለመጠቀም ለሚገጥም ችግር ሁሉ ሁላችንም “ልዩነት” ሳይገድበን ዘብ እንቆማለን!! ግን የግልጽነት ጥያቄ ያሳስበናል። ያስጨንቀናል። “በልማትና ዕድገት” ስም የተድበሰበሱ ውሎችና ስምምነቶች እኛንም ሆነ መጪውን ትውልድ ዋጋ እንዳያስከፍሉን ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ እናምናለን። በዚህ ጉዳይ ላይ አድርባይነት የለም!!

በአባይ ላይ የሚሠራው ግድብ ከግማሽ በላይ የሆነው ድርሻ የኢትዮጵያ እንዳልሆነ የጻፍነው ለዜና ፍጆታ ወይም ለዝነኝነት ወይም “ዜና አገኘን” በሚል በኢህአዴግ ላይ ነቀፋ ለመሰንዘር በጎመጀ ስሜትና ኢህአዴግን ለማሳጣት በመፈለግ አይደለም፡፡ ከላይ በመነሻው እንዳልነው አውቆ የማሳወቅ ሃላፊነት ስላለብን ነው። ስለሚመለከተን ነው። “አያገባችሁም፣ ዝም በሉ፣ አትጠይቁ” የሚባሉ ወገኖች ሊኖሩ ስለማይገባ ነው፡፡ ኢህአዴግ በሚያስተዳራት ኢትዮጵያ ሁሉንም ዜጋ መስፈር በሚፈልግበት የአድርባይነት መስፈሪያ መሰፈር ስለሌለብን ነው፡፡

የአባይ መገደብ አስፈላጊነትና ለአገር ጥቅም መዋል ለክርክር መቅረብ የሚገባው ጉዳይ አይመስለንም፤ “አባይ ይገደብ” እየተባለ ከተፎከረና ከተዘመረ በርካታ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ የአባይ ጉዳይ ኢህአዴግ አጀንዳ ወይም በባለመብትነት የሚመራው ጉዳይም አይደለም፡፡ ነገር ግን ከአባይ ጋር የሚመጣው ዓ-ባ-ይ-ነት ያሳስበናል፡፡ እየተከሰተ ያለው የግልጽነት መታጣት ጉዳይ የሁሉም ዜጋ የቁጭት ጥያቄ ሊሆን እንደሚገባው በአጽዕኖት ስለምናምን ነው፡፡ ይልቅ ሊያሳስብ የሚገባው ዝምታው ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎችም በእንደዚህ ዓይነት አገራዊ ጉዳይ ላይ እስከጥግ በመሄድ ሕዝብን የማሳወቅ ኃላፊነት ሲወጡ አለመመልከት ጥያቄ ስለሚፈጥርብን ነው፡፡

ጉዳዩ የቦንድንና የባለድርሻነት “share” ልዩነት ካለማወቅ የመነጨም አይደለም፡፡ ያገኘነው መረጃ አስተማማኝነቱም ሆነ እርግጠኝነቱ የጸሐይ በምስራቅ የመውጣትና በምዕራብ የመጥለቅ እርግጠኝነት ያህል ለጥያቄ የማይቀርብ ነው፡፡ ሆኖም የኢህአዴግ ሰዎች ሥርዓቱ ከፈጠረው የራሱ የሆነ ዝግነትና የማስፈራሪያ ስልት አኳያ በዚህና መሰል ጉዳዮች ላይ ሲናገሩ ራሳቸውን ዓይኑን ካፈጠጠ መረጃ በማራቅ እንደሆነ በተደጋጋሚ የተስተዋለ ሁኔታ ነው፡፡ እየተቀለደ ግን ያለው ምትክ በሌላት አገር ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ታዲያ ይህ እየተከናወነ ነው ከሚባለው ልማት በላይ ካላሳሰበን ሌላ ምን ሊያሳስበን ይችላል?

ስለሆነም የአባይ ጉዳይ ግልጽ ይደረግ እንላለን! ኢህአዴግ አገር እያስተዳደርኩ ነው እንደሚለው ሁሉ ይህንንም በሕዝብና አገር ስም እየተዋዋለ ነውና ጉዳዩን ለሕዝብ ይፋ ያድርግ፡፡ በልማት ስም ተጠያቂነትን ወደ ጎን ማለትም ሆነ ከግልጽነት መራቅ ልማት ሳይሆን ጥፋት ነው! ውድመት ነው!

በጅቡቲ ላይ ኢትዮጵያ ሙሉውን ወጪ ሸፍና የምታስገነባውን ወደብ አስመልክቶ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሲናገሩ “የህዳሴውን ግድብ” ቦንድ ከገዙት አገሮች መካከል ጅቡቲን ጨምረው የተወሰኑ የአፍሪካ አገራት እንዳሉ ጠቅሰው ነበር፡፡ ቦንድ በመግዛት ብቻ ያልተወሰኑትን ሌሎች አገራት በነካ እጃቸው ማሳወቅ ይገባቸው ነበር፤ ወደፊትም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ኢህአዴግ ይህንን ጉዳይ ይፋ ለማድረግ ያብቃው እንጂ እኛ በዚህ ጉዳይ ላይ ጥፋት ከሰራን ይቅርታ ለመጠየቅ ዝግጁ ነን፡፡ እርሳቸውም ሆኑ ኢህአዴግ ይህንን ባያደርጉም አገራቸውን የሚወድዱ በተገኘው መንገድ መረጃውን ሲሰጡ ግን ማዳመጥና መርምሮ ምላሽ መስጠት የግድ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን “ለምን መረጃው ይፋ ሆነ” በሚል ሳይገባን እስክስታ የምንወርድ ከሆነ “በአባይ ጉዳይ ላይ እኛም አድርባይ እንሁን?” ብለን እንድንጠይቅ እንገደዳለን፡፡

““የህዳሴው ግድብ” ከግማሽ በላይ የኢትዮጵያ አይደለም” በሚል ርዕስ የጻፍነውን ዜና ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule