• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ አባይ ግድብ “አድርባይ” እንሁን?

March 30, 2013 05:51 am by Editor Leave a Comment

ሰሞኑን ኢህአዴግ ጉባኤውን ሲጨርስ “አድርባይነት አሰጋኝ” ብሎናል። አባላቶቼ አድርባይ ሆነዋልና በዚህ ከቀጠልኩ እሰምጣለሁ የሚል ስጋት እንዳለበትም አስታውቆናል። ከፍርሃቻው ብዛት የተነሳ አድርባይነትን ለመዋጋትና “መድረክ ላይ ለመጥለፍ” በቁርጠኛነት እንታገላለን ብለው አቋማቸውን ነግረውናል። የሚገርመው ግን አድርባይነትን የፈጠረና ያነገሰው ራሱ ኢህአዴግ መሆኑን መዘንጋቱ ነው።

ኢህአዴግ አድርባይ ሚዲያዎች አሉት። አድርባይ ባለሃብቶች አሉት። ኢህአዴግ አድርባይ የኔቢጤዎች አሉት። ኢህአዴግ አድርባይና የማደናገሪያ ፕሮጀክቶች አሉት። ኢህአዴግ አድርባይ ድርጅቶች እንጂ ነጻ ድርጅቶች የሉትም። ኢህአዴግ አድርባይ ባለስልጣናት እንጂ ነጻ አመራሮች የሉትም። ሁሉም አድርባዮች ተጠሪነታቸው ለህወሃት ስለሆነ ተጠያቂውም ራሱ የኢህአዴግ ሾፌር ህወሃት እንጂ ሌሎች ሊሆኑ አይገባም። “ፈጣሪያቸው” የሚገመግማቸው፣ እነሱም አምነው የሚገመገሙት ታማኝ አድርባይ ስለሆኑ ብቻ ነው።

አሁን እየተለመደ የመጣው የመፈክርና የቀረርቶ ጉዳይ አጥወልውሎ የሚጥል ደረጃ ያደረሰንም ለዚህ ነው። ቃላት ማምረትና ማራባት የተካነበት ኢህአዴግ በየጊዜው የሚፈለፍላቸው ቃላቶች እያንገፈገፉን ነው። በተለይም ታላላቅ ዋጋ ባላቸው “ውድ” ቃላቶች ላይ አደጋ እየፈጠረም እንደሆነ ይሰማናል፤  ይጫወትባቸዋል። አድርባይ ሚዲያዎችና አድርባይ ጋዜጠኞች የማከፋፈሉን ስራ ይሰራሉ። ይህ በአገር ደረጃ የተንሰራፋው አድርባይነት ለኢህአዴግ ስጋቱ አይደለም፤ ኩራቱ እንጂ!!

ይህንን ያነሳነው ወድደን አይደለም። ባለፈው ሳምንት ባወጣነው የአባይ ግድብ ከግማሽ በላይ የኢትዮጵያ አይደለም የሚል ዜና አድርባይ እንድንሆን ያሳሰቡን በመኖራቸው ነው። ስለ አባይ ግድብ ያሰራጨነው ዜና ያስደነገጣቸው በርካቶች ናቸው። የአባይ ግድብ መገደብ እውን መሆን አለበት። አባይ ተገድቦ አገር መልማት አለበት። አባይን ለልማት ለመጠቀም ለሚገጥም ችግር ሁሉ ሁላችንም “ልዩነት” ሳይገድበን ዘብ እንቆማለን!! ግን የግልጽነት ጥያቄ ያሳስበናል። ያስጨንቀናል። “በልማትና ዕድገት” ስም የተድበሰበሱ ውሎችና ስምምነቶች እኛንም ሆነ መጪውን ትውልድ ዋጋ እንዳያስከፍሉን ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ እናምናለን። በዚህ ጉዳይ ላይ አድርባይነት የለም!!

በአባይ ላይ የሚሠራው ግድብ ከግማሽ በላይ የሆነው ድርሻ የኢትዮጵያ እንዳልሆነ የጻፍነው ለዜና ፍጆታ ወይም ለዝነኝነት ወይም “ዜና አገኘን” በሚል በኢህአዴግ ላይ ነቀፋ ለመሰንዘር በጎመጀ ስሜትና ኢህአዴግን ለማሳጣት በመፈለግ አይደለም፡፡ ከላይ በመነሻው እንዳልነው አውቆ የማሳወቅ ሃላፊነት ስላለብን ነው። ስለሚመለከተን ነው። “አያገባችሁም፣ ዝም በሉ፣ አትጠይቁ” የሚባሉ ወገኖች ሊኖሩ ስለማይገባ ነው፡፡ ኢህአዴግ በሚያስተዳራት ኢትዮጵያ ሁሉንም ዜጋ መስፈር በሚፈልግበት የአድርባይነት መስፈሪያ መሰፈር ስለሌለብን ነው፡፡

የአባይ መገደብ አስፈላጊነትና ለአገር ጥቅም መዋል ለክርክር መቅረብ የሚገባው ጉዳይ አይመስለንም፤ “አባይ ይገደብ” እየተባለ ከተፎከረና ከተዘመረ በርካታ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ የአባይ ጉዳይ ኢህአዴግ አጀንዳ ወይም በባለመብትነት የሚመራው ጉዳይም አይደለም፡፡ ነገር ግን ከአባይ ጋር የሚመጣው ዓ-ባ-ይ-ነት ያሳስበናል፡፡ እየተከሰተ ያለው የግልጽነት መታጣት ጉዳይ የሁሉም ዜጋ የቁጭት ጥያቄ ሊሆን እንደሚገባው በአጽዕኖት ስለምናምን ነው፡፡ ይልቅ ሊያሳስብ የሚገባው ዝምታው ነው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎችም በእንደዚህ ዓይነት አገራዊ ጉዳይ ላይ እስከጥግ በመሄድ ሕዝብን የማሳወቅ ኃላፊነት ሲወጡ አለመመልከት ጥያቄ ስለሚፈጥርብን ነው፡፡

ጉዳዩ የቦንድንና የባለድርሻነት “share” ልዩነት ካለማወቅ የመነጨም አይደለም፡፡ ያገኘነው መረጃ አስተማማኝነቱም ሆነ እርግጠኝነቱ የጸሐይ በምስራቅ የመውጣትና በምዕራብ የመጥለቅ እርግጠኝነት ያህል ለጥያቄ የማይቀርብ ነው፡፡ ሆኖም የኢህአዴግ ሰዎች ሥርዓቱ ከፈጠረው የራሱ የሆነ ዝግነትና የማስፈራሪያ ስልት አኳያ በዚህና መሰል ጉዳዮች ላይ ሲናገሩ ራሳቸውን ዓይኑን ካፈጠጠ መረጃ በማራቅ እንደሆነ በተደጋጋሚ የተስተዋለ ሁኔታ ነው፡፡ እየተቀለደ ግን ያለው ምትክ በሌላት አገር ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ታዲያ ይህ እየተከናወነ ነው ከሚባለው ልማት በላይ ካላሳሰበን ሌላ ምን ሊያሳስበን ይችላል?

ስለሆነም የአባይ ጉዳይ ግልጽ ይደረግ እንላለን! ኢህአዴግ አገር እያስተዳደርኩ ነው እንደሚለው ሁሉ ይህንንም በሕዝብና አገር ስም እየተዋዋለ ነውና ጉዳዩን ለሕዝብ ይፋ ያድርግ፡፡ በልማት ስም ተጠያቂነትን ወደ ጎን ማለትም ሆነ ከግልጽነት መራቅ ልማት ሳይሆን ጥፋት ነው! ውድመት ነው!

በጅቡቲ ላይ ኢትዮጵያ ሙሉውን ወጪ ሸፍና የምታስገነባውን ወደብ አስመልክቶ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሲናገሩ “የህዳሴውን ግድብ” ቦንድ ከገዙት አገሮች መካከል ጅቡቲን ጨምረው የተወሰኑ የአፍሪካ አገራት እንዳሉ ጠቅሰው ነበር፡፡ ቦንድ በመግዛት ብቻ ያልተወሰኑትን ሌሎች አገራት በነካ እጃቸው ማሳወቅ ይገባቸው ነበር፤ ወደፊትም ይጠበቅባቸዋል፡፡ ኢህአዴግ ይህንን ጉዳይ ይፋ ለማድረግ ያብቃው እንጂ እኛ በዚህ ጉዳይ ላይ ጥፋት ከሰራን ይቅርታ ለመጠየቅ ዝግጁ ነን፡፡ እርሳቸውም ሆኑ ኢህአዴግ ይህንን ባያደርጉም አገራቸውን የሚወድዱ በተገኘው መንገድ መረጃውን ሲሰጡ ግን ማዳመጥና መርምሮ ምላሽ መስጠት የግድ ነው፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን “ለምን መረጃው ይፋ ሆነ” በሚል ሳይገባን እስክስታ የምንወርድ ከሆነ “በአባይ ጉዳይ ላይ እኛም አድርባይ እንሁን?” ብለን እንድንጠይቅ እንገደዳለን፡፡

““የህዳሴው ግድብ” ከግማሽ በላይ የኢትዮጵያ አይደለም” በሚል ርዕስ የጻፍነውን ዜና ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule