• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከአሜን ባሻገር በበዕውቀቱ ስዩም

February 21, 2016 10:54 pm by Editor 6 Comments

ከአሜን ባሻገር በ19 ምዕራፎች የተቀነበበች246 ገጽ የሆነች ተነባቢ መፅሃፍ ነች። የዞን ዘጠኙ በፍቃዱ እንደነገረን ከሆነ አብዛኛዎቹ ምእራፎች በመጽሄትም በጋዜጣም የወጡ ስለነበሩ አዲስ አይደሉም ብሏል። በመጽሄትና በጋዜጣ የሚወጡ መጣጥፎች ማጣቀሻ ዋቢ ስለማያክሉ ከጊዜ ብዛትም ጸሀፊውም ስለሚረሳቸው የይድረስ ይድረስ ነገር ሻጥ ሻጥ ይደረጋሉ። የበዕውቀቱ ከአሜን ባሻገር በዚህ ረገድ ጉልህ ጎደሎነት አሳይቷል። ከቤተ አማራ ፖለቲካ አቀንቃኞችንም ጋር እሰጥ አገባ ያስገባው ይሄ የመጽሃፉ ደካማ ጎን ለምንጭ ለዋቢ የሚሰጠው ግምትና ቦታ። በሁለተኛው እትም ይስተካከላሉ የሚል ግምት አለኝ።

ስለ 19ኞቹ መጣጥፎች በዕውቀቱ በ13 ቃላት በሁለት አረፍተ ነገር ሲገልጽ “መጣጥፎቼ የእንጉርጉሮና የልግጫ ድብልቅ ናቸው። የሐሳብ አርአያዎቼ አንጎራጓሪ ሴቶች እንጂ ፕሮፌሽናል ፖለቲከኞች አይደሉም።”

ከአሜን ባሻገር ተስፋ መቁረጥና ንዴት ይታይበታል። ለዚህ ተስፋ መቁረጥና ንዴት የመፅሃፉ ጀርባ ጽሁፍ ጥሩ ገላጭ ይመስለኛል። ከአሜን ባሻገር በዚህ ስሜት ቢነበብ ለመረዳት አያስቸግርም።

በዕውቀቱ ሲጀምር እንዲህ ይላል። “የዘመኔ ጀግና እንዲህ የሚል ይመስለኛል”

“በኔ ዘመንና በጥንት አቴናውያን የቸነፈር ዘመን መካከል መሰረታዊ መመሳሰል አለ።”

“በሁለቱም ዘመኖች ውስጥ ለነገ ተስፋ ማድረግ የሚባል ነገር የለም።”

“ለፍቼ የሰራሁት ቤቴን ባቡር ይሁን ሰርጓጅ መርከብ በውል ያልታወቀ ነገር ጥሶት የሚያልፍ ከሆነ ቤት ለመስራት እንዴት ላቅድ እችላለሁ?

“ሰባት መቶ ሺህ ብር የገዛሁትን ቤቴን በክረምት አፍርሶ ደርዘን ጃንጥላ የማይገዛ ፍራንክ ሸጎጥ አድርጎ፣ ቤተ መቅደስ እንደገባች ውሻ አካልቦ የሚያባርረኝ ባለስልጣን ባለበት ሀገር ውስጥ ጎጆ ለምን እቀልሳለሁ።”

“ጌቶች ለችግር ቀኔ ያጠራቀምኩትን ብር በጥጋብ ዘመናቸው የሚወርሱብኝ ከሆነ የባንክ ደብተር የማወጣው ለምንድነው?”

“ልጄ በሕይወት እያለሁ እጓለማውታ ሊሆን እንደሚችል እያወቅሁ፣ “የዛሬ ዓመት የማሙሽ ልደት” እያልሁ የምዘፍንበት ምክንያት ምንድነው?”

“ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር” ከሚለው መፈክር በስተቀር ኢትዮጵያን ለዘላለም የሚያኖራት መሰረት መፍረሱን እያወቅሁ ለሚቀጥለው አመት እንዴት ላቅድ እችላለሁ?”

“ተው ባክህ! እኔም እንደጥንቱ አቴናውያን የሞት ፍርድ እንደተፈረደበት ሰው እኖራለሁ። የመሰቀያው ገመድ አንገቴ ውስጥ እንደተፈረደበት ሰው እኖራለሁ። የመሰቀያው ገመድ አንገቴ ውሰጥ እስቲገባ ድረስ የጥንቱ ባላገር ግጥም በቃሌ እወጣለሁ።”

ይህን ይመስላል የበዕውቀቱ ስዩም ከአሜን ባሻገር የተጻፈበት መንፈስ። አብዛኞቹ የመፅሃፉ ምእራፋት ባንድም ሆነ በሌላው በኩል የኦሮሞዎችን ላገር ግንባታ ያደረጉት አስተዋፆ ተንታኝ ነው። የኦሮሞ ታሪክ ሲነሳ ምኒልክም መነሳታቸው ስለማይቀር አንድ ሁለት ምእራፍ ምኒልክም ተችሯቸዋል። ዳያስፖራውም አንድ ምዕራፍ ደርሶታል። የኦሮሞ ታሪክ ሲነሳ ራስ ጎበናም ስለተነሱ አንድ ማስተካከያና አንድ ሀሳብ ልጨምር።

1) “ይታመሳል አሉ ከፋና ቦረና

አማን አይደሉም ወይ እነ ራስ ጎበና” (ገፅ 70)

በዕውቀቱ ይህንን ግጥም አንተርሶ ጎበና አማን (ሰሜን ሸዋ) በተባለ ቦታ ተወልዷል ይለናል። የግጥሙ አማን ሚዛን ቴጲ የሚገኘው ሲሆን ጎበና ደቡብ ሄደው የጎበና መልክተኛ ድምፅ በመጥፋቱ የተገጠመ ነው።

2) በዕውቀቱ “የጎበናን ቅኝት” ምዕራፍ የጀመረው በዮፍታሄ ግጥም ነው

አጥንቱን ልልቀመው መቃብር ቆፍሬ

ጎበናን ተሸዋ፤ አሉላን ተትግሬ

አሉላን ለጥይት፤ ጎበናን ለጭሬ

አሉላ ሴት ልጁን፤ ጥይት ሲያስተኩስ

ጎበና ሴት ልጁን፤ ሲያስተምር ፈረስ

አገሬ ተባብራ፤ ካረገጠች እርካብ

ነገራችን ሁሉ፤ የእምቧይ ካብ የእምቧይ ካብ…

መነሳት የነበረበት ግን በዕውቀቱ ያላነሳው የጎበና ሴት ልጅ ማናት ነው (በዕውቀቱ ያነሳው የጎበናን ወንድ ልጅ ወዳጆን ስለሆነ) ግን ደግሞ በዕውቀቱ ላነሳው ትርክት አጋዥ እሷ ትሆነው ነበር። አስካለ ማርያም ትባላለች የራስ አበበ አረጋይ እናትም ነች። እንዲህም ተብሎላቸዋል።

“በለው በዱባይ በለው በዱባይ

የአስካለ ማርያም ልጅ አበበ አረጋይ”

በዕውቀቱ ስለ ውጫሌው ውል በሌላው ምዕራፉ ሲያትት ገብርኤል ጎበና የተባለ አስተርጓሚ እንደነበር ያትታል። በዚህ ትርክቱ ግራዝማች ዮሴፍ ሲካተቱ አፅመ ጊዮርጊስ ተዘለዋል። በሁለተኛው ከአሜን ባሻገር እትም የሶስቱን ሚና ይልይልናል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

በዕውቀቱ ስለ ሀሰን አንጃሞ ሲፅፍ ሀሰን ወንጃቦ ብሎታል አስተካክላችሁ አንብቡለት።

በሌላው ገፅ (224) እንዲሁ የኦሮሞዎችን ላገር ግንባታ አስተዋፅኦ ሲያጎላ በስህተት የዳውሮውን ተወላጅ የኦሮሞ ተወላጅ ብሎታል።

እራሮት ቢበዛበትም ከአሜን ባሻገር ተነባቢ ፅሁፍ ነው። እንድታነቡት እጋብዛለሁ።

መልካም ንባብ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mus'ab says

    February 24, 2016 05:23 pm at 5:23 pm

    ውድ ወንድሜ: በውቀቱ ማለት ለእኔ በዘመኔ እንድኮራ በስነ-ፅሁፍ በታሪክ እንዲሁም በቁም ነገር ጭውውቱ አንቱ ከምላቸውና ልክ እንደ ስሙ የተፈጠረ መሆኑን እወቀው::

    Reply
  2. Alex says

    February 24, 2016 05:53 pm at 5:53 pm

    Dear Daniel,

    I didn’t get you at all.

    Reply
  3. አማረ መኮን ን says

    February 28, 2016 05:06 am at 5:06 am

    የበዕውቀቱ መጽሐፍ፤አሁን ለምንገኝበት የፖለቲካ ምስቅልቅል አንድ አግጣጫ ሊያሲዘን ይችላል የሚል እምነት አለኝ።
    ኢትዮጲያችንን ያጋጠማት ችግር ምንድነው መፍትሔው ወደ ሚል መንገድ ይወስደና።

    አማረ

    Reply
  4. bufta says

    March 1, 2016 03:26 pm at 3:26 pm

    losers are always blaming and criticizing genius peoples and preachers of peace and love for their greedy short period benefit as well, to defame others for their good will. i have seen this critics as a loser!

    Reply
  5. satenaw says

    April 27, 2016 08:27 pm at 8:27 pm

    ከአሜን ባሻገር ተስፋ መቁረጥና ንዴት ይታይበታል። ለዚህ ተስፋ መቁረጥና ንዴት የመፅሃፉ ጀርባ ጽሁፍ ጥሩ ገላጭ ይመስለኛል። ከአሜን ባሻገር በዚህ ስሜት ቢነበብ ለመረዳት አያስቸግርም።በዕውቀቱ ሲጀምር እንዲህ ይላል። “የዘመኔ ጀግና እንዲህ የሚል ይመስለኛል”“በኔ ዘመንና በጥንት አቴናውያን የቸነፈር ዘመን መካከል መሰረታዊ መመሳሰል አለ።”“በሁለቱም ዘመኖች ውስጥ ለነገ ተስፋ ማድረግ የሚባል ነገር የለም።”“ለፍቼ የሰራሁት ቤቴን ባቡር ይሁን ሰርጓጅ መርከብ በውል ያልታወቀ ነገር ጥሶት የሚያልፍ ከሆነ ቤት ለመስራት እንዴት ላቅድ እችላለሁ?“ሰባት መቶ ሺህ ብር የገዛሁትን ቤቴን በክረምት አፍርሶ ደርዘን ጃንጥላ የማይገዛ ፍራንክ ሸጎጥ አድርጎ፣ ቤተ መቅደስ እንደገባች ውሻ አካልቦ የሚያባርረኝ ባለስልጣን ባለበት ሀገር ውስጥ ጎጆ ለምን እቀልሳለሁ።”“ጌቶች ለችግር ቀኔ ያጠራቀምኩትን ብር በጥጋብ ዘመናቸው የሚወርሱብኝ ከሆነ የባንክ ደብተር የማወጣው ለምንድነው?”“ልጄ በሕይወት እያለሁ እጓለማውታ ሊሆን እንደሚችል እያወቅሁ፣ “የዛሬ ዓመት የማሙሽ ልደት” እያልሁ የምዘፍንበት ምክንያት ምንድነው?”“ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር” ከሚለው መፈክር በስተቀር ኢትዮጵያን ለዘላለም የሚያኖራት መሰረት መፍረሱን እያወቅሁ ለሚቀጥለው አመት እንዴት ላቅድ እችላለሁ?”“ተው ባክህ! እኔም እንደጥንቱ አቴናውያን የሞት ፍርድ እንደተፈረደበት ሰው እኖራለሁ። የመሰቀያው ገመድ አንገቴ ውስጥ እንደተፈረደበት ሰው እኖራለሁ። የመሰቀያው ገመድ አንገቴ ውሰጥ እስቲገባ ድረስ የጥንቱ ባላገር ግጥም በቃሌ እወጣለሁ።”ይህን ይመስላል የበዕውቀቱ ስዩም ከአሜን ባሻገር የተጻፈበት መንፈስ። አብዛኞቹ የመፅሃፉ ምእራፋት ባንድም ሆነ በሌላው በኩል የኦሮሞዎችን ላገር ግንባታ ያደረጉት አስተዋፆ ተንታኝ ነው። የኦሮሞ ታሪክ ሲነሳ ምኒልክም መነሳታቸው ስለማይቀር አንድ ሁለት ምእራፍ ምኒልክም ተችሯቸዋል። ዳያስፖራውም አንድ ምዕራፍ ደርሶታል

    Reply
  6. Yared says

    June 11, 2016 11:51 pm at 11:51 pm

    Golgul, wanted to share article i came across. Thanks.
    http://ethiopianchurch.org/en/books_reviews/268-%E2%80%9C%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B4%E1%89%B5-%E1%89%A5%E1%88%B5%E1%8A%AD%E1%88%8C%E1%89%B3%E1%8B%8D%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%88%B0%E1%89%A5%E1%8A%A8%E1%8B%8D%E2%80%9D.html

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule