• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጅዳ ሽሜሲ በር ላይ ወድቃለች የተባለችው እህት ጉዳይ!

November 24, 2016 01:33 am by Editor Leave a Comment

ከትናንት ጅዳ ውስጥ በጠና ታማ እሷና ልጇ አደጋ ላይ አሉ ስለተባ ለችው እህት እየተሰራጨ ያለው መረጃ ደርሶኛል። መረጃውን በዝርዝር ያገኘሁት ከሊያ ሾው ነበር፣ ታመመች የተባለችውን እህት በቪዲዮ የተደገፈ መረጃ እንደደረሰኝ ወደ ጅዳ ቆንስል ደውዬ ለማጣራት ሞክሬ ነበር! በጅዳ ቆንስላ መረጃ ለማግኘት ከባድ እየሆነ መጥቷ ል፣ አንዳንዶች ኃላፊዎች ከዚህ ቀደም በማቀርባቸው ተጨባጭ ሂሶች አኩርፈው መረጃ ላለመስጠት ስልካቸውን ይዘጉብኛል፣ አንዳንዶች ደግሞ መረጃም ሆነ ጥያቄ ለመመለስ ፈቃደኛ አይደሉም! እጅ አዙር በሆነ መንገድ የጅዳ ቆንስል መረጃው እንዳልደረሰው ተነግሮኛል!

ይህች እህት በሽሜሲ ጊዜያዊ እስር ቤት በር ላይ ተጥለላች መባሉን ሰምቸ ወደ ቦታው የሚያጣራልኝ የስራ ባልደረባዬን ልኬም ነበር፣ ዛሬ ረፋድ ላይ በር ላይ ተዟዙሮ የወደቀ ሰው አለመኖሩን አረጋግጦልኛል! ይህን ካደረግ ኩ በኋላ ምናልባት ይህች እህት በእስር ቤት ትገኝ እንደሁ ቢረዷት ለማሳሰብ ወደ ቆንስላው የሺሜሲ ተወካዮች ወደ አቶ ቡሩና አቶ አብርሃ ደወልኩ፣ ሁለቱም ስልክ አያነሱም። መልሸ ወደ ቆንስል ያለለት ደወልኩ ስለኬ ብሎክ የመደረጉ ምልክት ሰጠኝ። በዚህ ሁኔታ እስካሁን ከቆንስሉ ያገኘሁት መረጃ የለምና ወደ ሺሜሲ አመራሁ!jeddah-sister-eth

ሽሜሲ በር ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግበት ቦታ በመሆኑ በአካል ሄጅ በአካባቢው ወድቃለች የተባለቸውን እህት ዘወር ዘወር ብዬ ፈለግኳት፣ የለችም፣ ይሁን እንጅ ከዚህ ቀደም በአካባቢው ወድቃ የነበረች እህት ስለመኖርዋና ልጇንም እሷንም ለመርዳት ሞክረው አቅሙ ስለሌላቸው መረጃ የሚቻሉትን አደርገውላት የሄዱትን እህቶች ምስልና ምስክርነት ደርሶኝ ተመልክቸዋለሁ! ዛሬ እኔ ባላገኛትም ትናንትና ከትናንት በፊት ያገኟት እንዳሉ ማረጋገጥ ችያለሁ! እንግዲህ ሊሆን ስለሚችለው ብቻ በግምት ልናገር … በትክክል ቪዲዮው የተቀረጸው ጅዳ ሽሚሲ ስለመሆኑ መረጃው ደርሶኛል፣ ልጅቱ በእስር ላይ የምትገኝ ይመስለኛል፣ የቆንስሉ ተወካዮች ለምን ወደ ህክምና እንዳልወሰዷት አልገባ ኝም። አንድ በቦታው የነበረ ች እማኝ ይህች እህት ከእነ ልጇ ለቀናት ስትሰቃይ ማንም እንዳልደረሰላት ተናግራለች። አሁንም በእርግጠኝነት መናገር የምችለው ወይ በጠና ታማ ሀኪም ቤት ተወስዳለች አለያም ወደ ማረፊያ ወስደዋት ይሆናል፣ በመጠለያ ካለችም  ተከ ታትለው ህክምና እንድታገኝ የእኛ ተወካዮች ሰራ አልሰሩ ይሆናል ፣ በቅርብ ሰአታት በደረሰኝ መረጃ መሰረት “ይህች እህት ከእስር ቤት አስወጥተው የጣሏት የሳውዲ ፖሊሶች ናቸው!” የሚለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን በሊያ በኩል ተስተካክሎ ሰምቻለሁ!

በትክክል የሆነው በጠና በመታመሟ ወደ ሀገር ለመላክ አንቻልም መባሏን ነው፣  ይህ በመሆኑ ያለ ማንም ረዳት በበር ብርድና ጸሀይ እየተፈራረቀባት መሰንበቷ ልብን በሀዘን ይሰብራል 🙁 አሁንም አልመሸም፣ ያለችበት ቦታ ተጣርቶ ከተገኘች በጅዳ ቆንስል ተወካዮች ጎትጓችነት ወደ ህክምና ሊወስዷት ይችላሉ! ይህን በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ! ሀገሩ ሳውዲ ነውና በጠና በታመመና እስር ቤት ያለን የወገን ጉዳይ ተከታትሎ ህክምና እንዲያገኙና ወደ ሀገር ለመላክ  ከኢንባሲና ከቆንስላ ውጭ አማራጭ የለም! ጌቱና ሊያ ሾው የወገን ጉዳይ ያገባኛል ብላችሁ የወገናችሁን ድምጽ በማሰማት ላደረሳችሁን መረጃ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ!

እንዲህ አይነት የወገን ጉዳት ሲደርስ፣ በተለይ ሰው በጠና ሲታመምና ወደ ሀገር ቤት ልግባ ብሎ እጁን የሰጠ ዜጋ በማቆያ እስር ቤት ሰማቅቅ ተራው ነዋሪ ሰው ለመደገፍ አቅሙ የለውም፣ ብቸማው ደራሽ እውቅና ያለው የመንግስት ተወካዮች ብቻ ናቸው! ለማጠቃለል ያህል ይህ መረጃ የሚደርሳችሁ የቆንስሉ ሹማምንትና ሰራተኞች ለፈጣሪ ብላችሁ ከነልጇ የምትከላተመው እህት ዜጋ ናትና  እርዷት፣ መረጃ ስጡን ተለመኑን!

ቸር ያሰማን!

ነቢዩ ሲራክ
ህዳር 14 ቀን 2009 ዓም
(ከዚህ ጋር ያያዝኩትን ፎቶ ያገመሁት ከሊያ ሾው ነው)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule