• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አበሻና ጽሕፈት

August 4, 2014 08:54 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ ከአንድ ወዳጄ ጋር ስለኢየሩሳሌም ማኅበር ስናወራ መሥራቹ አቶ መኮንን ዘውዴ ትዝ አሉኝና ስለሳቸው ውለታ ሳወራ ነበር፤ ከሳቸው ጋር ተያይዞም ከዚህ በፊት አይ አበሻ! በሚል አጠቃላይ ርእስ አበሻና ልመና ወዘተ. እያልሁ መጻፍ ጀምሬ የነበረው ትዝ አለኝ፤ አንዳንድ ስላልገባቸው ነገር ሁሉ መጻፍ የሚወዱ ሰዎች አቅጣጫውን ሊለውጡት ሙከራ ሲጀምሩ ትቼው ነበር፤ አሁን የመክሸፍን ጉዳይ ደግሜ ለመጻፍ ስጀምር አንዳንድ በጣም መሠረታዊ የሆኑ የመክሸፍ መገለጫዎችን ስጽፍ በመጽሐፍ መልክ እስኪወጣ አላስችል አለኝና አንዱን ሀሳብ አደባባይ ለማውጣት ወሰንሁ፤ በዚያውም አቶ መኮንን ዘውዴን ማስታወሻ ይሆነኛል።

ወደ 1935-36 ግድም በአዲስ አበባ ውስጥ ክፉ ችግር ቸጋርን አስከትሎ ነበር፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ ገና ከስደት ከተመለሱ ሁለትና ሦስት ዓመት መሆኑ ነው፤ አገር አልተረጋጋም፤ የኢጣልያኑ አገዛዝ ቅሪት፣ የእንግሊዞች ዘረፋ፣ የሱዳን፣ የኬንያና የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች እንደልባቸው የሚፈነጩበት ጊዜ ነበር፤ በአንድ በኩል በአርበኞቹ ላይ የነበረው ኩራት፣ በሌላ በኩል በኢጣልያኖች፣ በእንግሊዞችና በሌሎች የውጭ አገር ሰዎች የበላይነት ኩራቱ የሚደፈጠጥበት ጊዜ ነበር።

በቤት ውስጥ እናቴና የእናቴ ረዳት ሆና ያሳደገችኝ ሴት ሲቸገሩ በየዕለቱ አያለሁ፤ አብዛኛውን ጊዜ የሁለቱም ችግር ለእኔ ነበር፤ ስለዚህ ኃላፊነት ተሰማኝና የበኩሌን አስተዋጽኦ ለማድረግ ሥራ ያዝሁ፤ የነበረኝ ችሎታ የእጅ ጽሕፈት ብቻ ነበር፤ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት በር ላይ ራፖር ጸሐፊ ሆንሁ፤ የእጅ ጽሑፌ በጣም ጥሩ ስለነበረ አብዛኛዎቹ ሰዎች ወደእኔ በመምጣታቸው ደህና ገንዘብ አገኝ ጀመረ፤ እናቴን ከመርዳት አልፌ ሌላ ሌላ ነገርም ለመልመድ እየዳዳኝ ነበረ፤ ቁልቁለቱን ለመውረድ የሚረዱኝ ነበሩ፤ አንድ ዘመድ ትምህርቴን ብቀጥል እንደሚሻለኝ ነገረኝና ለትምህርት ሚኒስቴር ማመልከቻ ጽፌ አቶ መኮንን ዘውዴ ለሚባሉት አንድሰጥ መከረኝ፤ እኔም እንደተመከርሁት አደረግሁና አቶ መኮንን ማመልከቻዬን ገና ተቀብለው ሲያዩት ማን ነው ይህን ማመልከቻ የጻፈልህ? ብለው ጠየቁኝና እኔ መሆኔን ስነግራቸው ወረቀትና ብዕር ሰጡኝና እስቲ ጻፍ አሉኝ፤ በጣም አስደሰታቸውና ከተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ዲሬክተር የምስክር ደብዳቤ እንዳመጣላቸው ጠየቁኝ፤ በበነጋታው ይዤላቸው ስሄድ እሳቸውም ወዲያው ማዘዣ ሰጡኝና በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት አዳሪ ሆንሁ፤ የእናቴንና የአሳዳጊዬን ችግር ቀነስሁ።

ከላይ የተዘረዘረው ታሪክ ዓላማ ራሴን ለማስተዋወቅ አይደለም፤ ጽሕፈትን ለማስተዋወቅ ነው፤ በኢትዮጵያ የጽሕፈትን መክሸፍ፣ የእውቀትን መክሸፍ ለማሳየት ነው፤ አቶ መኮንን ዋጋ የሰጡት በኢትዮጵያ ባህላዊ ትምህርት ዋጋ የሚያወጣውን የእጅ ጽሑፍ ውበት ነው፤ በኢትዮጵያ የጽሕፈት ዋና ተግባር ለቤተ ክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍትን ለመጻፍና ለቤተ መንግሥት ማዘዣዎችን ዜና መዋዕሎችን ለመጻፍ ነበር።

በሌሎች አገሮች የጽሕፈት ዋና ተግባር እውቀትን ለማሰራጨት፣ እውቀትን ለማስተላለፍና እውቀትን ለመለዋወጥ ነበር፤ ነገር ግን የራሳችን ፊደል ቢኖረንም፣ የጽሕፈት ባህል ጅምሩ ቢኖረንም የጽሕፈት ተጠቃሚዎች ነበርን ለማለት የሚያስደፍር ምንም ነገር የለም፤ እንዲያውም የኢትዮጵያ ታሪክ መክሸፍ ዋናው ቁልፍ አንደነበረ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤ በመጀመሪያ ሁለት መሠረታዊ እውነቶችን ላንጥፍ፡— አንደኛ የፊደሎችና የጽሕፈት ጉዳይ የተጀመረው በምሥራቁ የዓለም ክፍል ዛሬ መሀከለኛ ምሥራቅ በሚባለውና በሩቅ ምሥራቅ አገሮች ነው፤ ሁለተኛ መጻሕፍትን ማሳተሚያ መኪና የተፈጠረው በምዕራባውያን ነው፤ እንደሚባለው በአሥራ አምስተኛው ምዕተ-ዓመት መዝጊያ ላይ ነው፤ ጽሕፈት በምሥራቃውያን ከተፈጠረ ከብዙ ምዕተ-ዓመታት በኋላ ማተሚያ መኪና ተሠራ፤ በጽሕፈት መፈጠርና በጽሕፈት ማተሚያ መፈጠር መሀከል ያለውን የዓመታት ልዩነት በአንድ በኩል፣ በጽሕፈት ፈጣሪዎችና በጽሕፈት ማተሚያ መኪና ፈጣሪዎች መሀከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ፤ ከተቻላችሁም ተወያዩበት።

ነገሩን ወደኢትዮጵያ ስናመጣው የፊደላችን ዕድሜ በሺህ ዓመታት የሚቆጠር ለመሆኑ ድንጋይ ይመሰክራል፤ የጽሕፈት መኪና ከገባ ግን ከመቶ ሃምሳ ዓመት የሚበልጥ አይመስለኝም፤ ዛሬ የመለስ ዜናዊ አገልጋዮች እንደሚሉት የኢትዮጵያ ታሪክ ከመቶ ዓመት አይበልጥም ሲሉ፣ በወግ በሥርዓት የተመዘገበ ታሪክ የለም ማለታቸው ይመስለኛል፤ በዚህም ምክንያት እኛ ባለቤቶች እንሆንበታለን ማለታቸው ነው፤ እንግዲህ መክሸፍ መክሸፍን እንዴት እንደሚወልድ በገሀድ ይታያል፤ ፊደል ከሸፈ፤ ጽሕፈት ከሸፈ፤ እውቀት ከሸፈ፤ ኅትመት ከሸፈ፤ በመክሸፍ መሰላል ወንበሩ ላይ የወጡት የመክሸፍ ልጆች ናቸው፤ እነዚህ የመክሸፍ ልጆች የመክሸፍን ዕድሜ ለማራዘም ቢሞክሩ ምን ያስደንቃል? አፈናውን ቢያጠናክሩት፣ የዜና ማሰራጫዎችን ሁሉ በቁጥጥራቸው ስር አድርገው ውሸታቸውን የሚያጋልጡባቸው ጋዜጦች እንዳይኖሩ ማድረግ የባህርያቸው ነው፤ ደንቁሮ ማደንቆር የባሕርይ ነው።

በመገናኛ ብዙኃን ዛሬ ዓለም የሁሉም ሆናለች፤ ለአፈና አገዛዝ አትመችም፤ ኢትዮጵያውያን ፊደልን ሲንቁ እውነትንና እውቀትን ናቁ፤ እውነትንና እውቀትን ሲንቁ ዳገቱን እየተዉ ቁልቁለቱን ወረዱ! ቀላል ነው፤ መክሸፍ ማለት አንዲህ ነው።

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ሰኔ 2006

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule