• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አበሻና ጽሕፈት

August 4, 2014 08:54 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ ከአንድ ወዳጄ ጋር ስለኢየሩሳሌም ማኅበር ስናወራ መሥራቹ አቶ መኮንን ዘውዴ ትዝ አሉኝና ስለሳቸው ውለታ ሳወራ ነበር፤ ከሳቸው ጋር ተያይዞም ከዚህ በፊት አይ አበሻ! በሚል አጠቃላይ ርእስ አበሻና ልመና ወዘተ. እያልሁ መጻፍ ጀምሬ የነበረው ትዝ አለኝ፤ አንዳንድ ስላልገባቸው ነገር ሁሉ መጻፍ የሚወዱ ሰዎች አቅጣጫውን ሊለውጡት ሙከራ ሲጀምሩ ትቼው ነበር፤ አሁን የመክሸፍን ጉዳይ ደግሜ ለመጻፍ ስጀምር አንዳንድ በጣም መሠረታዊ የሆኑ የመክሸፍ መገለጫዎችን ስጽፍ በመጽሐፍ መልክ እስኪወጣ አላስችል አለኝና አንዱን ሀሳብ አደባባይ ለማውጣት ወሰንሁ፤ በዚያውም አቶ መኮንን ዘውዴን ማስታወሻ ይሆነኛል።

ወደ 1935-36 ግድም በአዲስ አበባ ውስጥ ክፉ ችግር ቸጋርን አስከትሎ ነበር፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ ገና ከስደት ከተመለሱ ሁለትና ሦስት ዓመት መሆኑ ነው፤ አገር አልተረጋጋም፤ የኢጣልያኑ አገዛዝ ቅሪት፣ የእንግሊዞች ዘረፋ፣ የሱዳን፣ የኬንያና የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች እንደልባቸው የሚፈነጩበት ጊዜ ነበር፤ በአንድ በኩል በአርበኞቹ ላይ የነበረው ኩራት፣ በሌላ በኩል በኢጣልያኖች፣ በእንግሊዞችና በሌሎች የውጭ አገር ሰዎች የበላይነት ኩራቱ የሚደፈጠጥበት ጊዜ ነበር።

በቤት ውስጥ እናቴና የእናቴ ረዳት ሆና ያሳደገችኝ ሴት ሲቸገሩ በየዕለቱ አያለሁ፤ አብዛኛውን ጊዜ የሁለቱም ችግር ለእኔ ነበር፤ ስለዚህ ኃላፊነት ተሰማኝና የበኩሌን አስተዋጽኦ ለማድረግ ሥራ ያዝሁ፤ የነበረኝ ችሎታ የእጅ ጽሕፈት ብቻ ነበር፤ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት በር ላይ ራፖር ጸሐፊ ሆንሁ፤ የእጅ ጽሑፌ በጣም ጥሩ ስለነበረ አብዛኛዎቹ ሰዎች ወደእኔ በመምጣታቸው ደህና ገንዘብ አገኝ ጀመረ፤ እናቴን ከመርዳት አልፌ ሌላ ሌላ ነገርም ለመልመድ እየዳዳኝ ነበረ፤ ቁልቁለቱን ለመውረድ የሚረዱኝ ነበሩ፤ አንድ ዘመድ ትምህርቴን ብቀጥል እንደሚሻለኝ ነገረኝና ለትምህርት ሚኒስቴር ማመልከቻ ጽፌ አቶ መኮንን ዘውዴ ለሚባሉት አንድሰጥ መከረኝ፤ እኔም እንደተመከርሁት አደረግሁና አቶ መኮንን ማመልከቻዬን ገና ተቀብለው ሲያዩት ማን ነው ይህን ማመልከቻ የጻፈልህ? ብለው ጠየቁኝና እኔ መሆኔን ስነግራቸው ወረቀትና ብዕር ሰጡኝና እስቲ ጻፍ አሉኝ፤ በጣም አስደሰታቸውና ከተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ዲሬክተር የምስክር ደብዳቤ እንዳመጣላቸው ጠየቁኝ፤ በበነጋታው ይዤላቸው ስሄድ እሳቸውም ወዲያው ማዘዣ ሰጡኝና በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት አዳሪ ሆንሁ፤ የእናቴንና የአሳዳጊዬን ችግር ቀነስሁ።

ከላይ የተዘረዘረው ታሪክ ዓላማ ራሴን ለማስተዋወቅ አይደለም፤ ጽሕፈትን ለማስተዋወቅ ነው፤ በኢትዮጵያ የጽሕፈትን መክሸፍ፣ የእውቀትን መክሸፍ ለማሳየት ነው፤ አቶ መኮንን ዋጋ የሰጡት በኢትዮጵያ ባህላዊ ትምህርት ዋጋ የሚያወጣውን የእጅ ጽሑፍ ውበት ነው፤ በኢትዮጵያ የጽሕፈት ዋና ተግባር ለቤተ ክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍትን ለመጻፍና ለቤተ መንግሥት ማዘዣዎችን ዜና መዋዕሎችን ለመጻፍ ነበር።

በሌሎች አገሮች የጽሕፈት ዋና ተግባር እውቀትን ለማሰራጨት፣ እውቀትን ለማስተላለፍና እውቀትን ለመለዋወጥ ነበር፤ ነገር ግን የራሳችን ፊደል ቢኖረንም፣ የጽሕፈት ባህል ጅምሩ ቢኖረንም የጽሕፈት ተጠቃሚዎች ነበርን ለማለት የሚያስደፍር ምንም ነገር የለም፤ እንዲያውም የኢትዮጵያ ታሪክ መክሸፍ ዋናው ቁልፍ አንደነበረ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤ በመጀመሪያ ሁለት መሠረታዊ እውነቶችን ላንጥፍ፡— አንደኛ የፊደሎችና የጽሕፈት ጉዳይ የተጀመረው በምሥራቁ የዓለም ክፍል ዛሬ መሀከለኛ ምሥራቅ በሚባለውና በሩቅ ምሥራቅ አገሮች ነው፤ ሁለተኛ መጻሕፍትን ማሳተሚያ መኪና የተፈጠረው በምዕራባውያን ነው፤ እንደሚባለው በአሥራ አምስተኛው ምዕተ-ዓመት መዝጊያ ላይ ነው፤ ጽሕፈት በምሥራቃውያን ከተፈጠረ ከብዙ ምዕተ-ዓመታት በኋላ ማተሚያ መኪና ተሠራ፤ በጽሕፈት መፈጠርና በጽሕፈት ማተሚያ መፈጠር መሀከል ያለውን የዓመታት ልዩነት በአንድ በኩል፣ በጽሕፈት ፈጣሪዎችና በጽሕፈት ማተሚያ መኪና ፈጣሪዎች መሀከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ፤ ከተቻላችሁም ተወያዩበት።

ነገሩን ወደኢትዮጵያ ስናመጣው የፊደላችን ዕድሜ በሺህ ዓመታት የሚቆጠር ለመሆኑ ድንጋይ ይመሰክራል፤ የጽሕፈት መኪና ከገባ ግን ከመቶ ሃምሳ ዓመት የሚበልጥ አይመስለኝም፤ ዛሬ የመለስ ዜናዊ አገልጋዮች እንደሚሉት የኢትዮጵያ ታሪክ ከመቶ ዓመት አይበልጥም ሲሉ፣ በወግ በሥርዓት የተመዘገበ ታሪክ የለም ማለታቸው ይመስለኛል፤ በዚህም ምክንያት እኛ ባለቤቶች እንሆንበታለን ማለታቸው ነው፤ እንግዲህ መክሸፍ መክሸፍን እንዴት እንደሚወልድ በገሀድ ይታያል፤ ፊደል ከሸፈ፤ ጽሕፈት ከሸፈ፤ እውቀት ከሸፈ፤ ኅትመት ከሸፈ፤ በመክሸፍ መሰላል ወንበሩ ላይ የወጡት የመክሸፍ ልጆች ናቸው፤ እነዚህ የመክሸፍ ልጆች የመክሸፍን ዕድሜ ለማራዘም ቢሞክሩ ምን ያስደንቃል? አፈናውን ቢያጠናክሩት፣ የዜና ማሰራጫዎችን ሁሉ በቁጥጥራቸው ስር አድርገው ውሸታቸውን የሚያጋልጡባቸው ጋዜጦች እንዳይኖሩ ማድረግ የባህርያቸው ነው፤ ደንቁሮ ማደንቆር የባሕርይ ነው።

በመገናኛ ብዙኃን ዛሬ ዓለም የሁሉም ሆናለች፤ ለአፈና አገዛዝ አትመችም፤ ኢትዮጵያውያን ፊደልን ሲንቁ እውነትንና እውቀትን ናቁ፤ እውነትንና እውቀትን ሲንቁ ዳገቱን እየተዉ ቁልቁለቱን ወረዱ! ቀላል ነው፤ መክሸፍ ማለት አንዲህ ነው።

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ሰኔ 2006

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule