• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አበሻና ጽሕፈት

August 4, 2014 08:54 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ ከአንድ ወዳጄ ጋር ስለኢየሩሳሌም ማኅበር ስናወራ መሥራቹ አቶ መኮንን ዘውዴ ትዝ አሉኝና ስለሳቸው ውለታ ሳወራ ነበር፤ ከሳቸው ጋር ተያይዞም ከዚህ በፊት አይ አበሻ! በሚል አጠቃላይ ርእስ አበሻና ልመና ወዘተ. እያልሁ መጻፍ ጀምሬ የነበረው ትዝ አለኝ፤ አንዳንድ ስላልገባቸው ነገር ሁሉ መጻፍ የሚወዱ ሰዎች አቅጣጫውን ሊለውጡት ሙከራ ሲጀምሩ ትቼው ነበር፤ አሁን የመክሸፍን ጉዳይ ደግሜ ለመጻፍ ስጀምር አንዳንድ በጣም መሠረታዊ የሆኑ የመክሸፍ መገለጫዎችን ስጽፍ በመጽሐፍ መልክ እስኪወጣ አላስችል አለኝና አንዱን ሀሳብ አደባባይ ለማውጣት ወሰንሁ፤ በዚያውም አቶ መኮንን ዘውዴን ማስታወሻ ይሆነኛል።

ወደ 1935-36 ግድም በአዲስ አበባ ውስጥ ክፉ ችግር ቸጋርን አስከትሎ ነበር፤ አጼ ኃይለ ሥላሴ ገና ከስደት ከተመለሱ ሁለትና ሦስት ዓመት መሆኑ ነው፤ አገር አልተረጋጋም፤ የኢጣልያኑ አገዛዝ ቅሪት፣ የእንግሊዞች ዘረፋ፣ የሱዳን፣ የኬንያና የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች እንደልባቸው የሚፈነጩበት ጊዜ ነበር፤ በአንድ በኩል በአርበኞቹ ላይ የነበረው ኩራት፣ በሌላ በኩል በኢጣልያኖች፣ በእንግሊዞችና በሌሎች የውጭ አገር ሰዎች የበላይነት ኩራቱ የሚደፈጠጥበት ጊዜ ነበር።

በቤት ውስጥ እናቴና የእናቴ ረዳት ሆና ያሳደገችኝ ሴት ሲቸገሩ በየዕለቱ አያለሁ፤ አብዛኛውን ጊዜ የሁለቱም ችግር ለእኔ ነበር፤ ስለዚህ ኃላፊነት ተሰማኝና የበኩሌን አስተዋጽኦ ለማድረግ ሥራ ያዝሁ፤ የነበረኝ ችሎታ የእጅ ጽሕፈት ብቻ ነበር፤ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት በር ላይ ራፖር ጸሐፊ ሆንሁ፤ የእጅ ጽሑፌ በጣም ጥሩ ስለነበረ አብዛኛዎቹ ሰዎች ወደእኔ በመምጣታቸው ደህና ገንዘብ አገኝ ጀመረ፤ እናቴን ከመርዳት አልፌ ሌላ ሌላ ነገርም ለመልመድ እየዳዳኝ ነበረ፤ ቁልቁለቱን ለመውረድ የሚረዱኝ ነበሩ፤ አንድ ዘመድ ትምህርቴን ብቀጥል እንደሚሻለኝ ነገረኝና ለትምህርት ሚኒስቴር ማመልከቻ ጽፌ አቶ መኮንን ዘውዴ ለሚባሉት አንድሰጥ መከረኝ፤ እኔም እንደተመከርሁት አደረግሁና አቶ መኮንን ማመልከቻዬን ገና ተቀብለው ሲያዩት ማን ነው ይህን ማመልከቻ የጻፈልህ? ብለው ጠየቁኝና እኔ መሆኔን ስነግራቸው ወረቀትና ብዕር ሰጡኝና እስቲ ጻፍ አሉኝ፤ በጣም አስደሰታቸውና ከተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ዲሬክተር የምስክር ደብዳቤ እንዳመጣላቸው ጠየቁኝ፤ በበነጋታው ይዤላቸው ስሄድ እሳቸውም ወዲያው ማዘዣ ሰጡኝና በተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት አዳሪ ሆንሁ፤ የእናቴንና የአሳዳጊዬን ችግር ቀነስሁ።

ከላይ የተዘረዘረው ታሪክ ዓላማ ራሴን ለማስተዋወቅ አይደለም፤ ጽሕፈትን ለማስተዋወቅ ነው፤ በኢትዮጵያ የጽሕፈትን መክሸፍ፣ የእውቀትን መክሸፍ ለማሳየት ነው፤ አቶ መኮንን ዋጋ የሰጡት በኢትዮጵያ ባህላዊ ትምህርት ዋጋ የሚያወጣውን የእጅ ጽሑፍ ውበት ነው፤ በኢትዮጵያ የጽሕፈት ዋና ተግባር ለቤተ ክርስቲያን የጸሎት መጻሕፍትን ለመጻፍና ለቤተ መንግሥት ማዘዣዎችን ዜና መዋዕሎችን ለመጻፍ ነበር።

በሌሎች አገሮች የጽሕፈት ዋና ተግባር እውቀትን ለማሰራጨት፣ እውቀትን ለማስተላለፍና እውቀትን ለመለዋወጥ ነበር፤ ነገር ግን የራሳችን ፊደል ቢኖረንም፣ የጽሕፈት ባህል ጅምሩ ቢኖረንም የጽሕፈት ተጠቃሚዎች ነበርን ለማለት የሚያስደፍር ምንም ነገር የለም፤ እንዲያውም የኢትዮጵያ ታሪክ መክሸፍ ዋናው ቁልፍ አንደነበረ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤ በመጀመሪያ ሁለት መሠረታዊ እውነቶችን ላንጥፍ፡— አንደኛ የፊደሎችና የጽሕፈት ጉዳይ የተጀመረው በምሥራቁ የዓለም ክፍል ዛሬ መሀከለኛ ምሥራቅ በሚባለውና በሩቅ ምሥራቅ አገሮች ነው፤ ሁለተኛ መጻሕፍትን ማሳተሚያ መኪና የተፈጠረው በምዕራባውያን ነው፤ እንደሚባለው በአሥራ አምስተኛው ምዕተ-ዓመት መዝጊያ ላይ ነው፤ ጽሕፈት በምሥራቃውያን ከተፈጠረ ከብዙ ምዕተ-ዓመታት በኋላ ማተሚያ መኪና ተሠራ፤ በጽሕፈት መፈጠርና በጽሕፈት ማተሚያ መፈጠር መሀከል ያለውን የዓመታት ልዩነት በአንድ በኩል፣ በጽሕፈት ፈጣሪዎችና በጽሕፈት ማተሚያ መኪና ፈጣሪዎች መሀከል ያለውን ልዩነት ልብ በሉ፤ ከተቻላችሁም ተወያዩበት።

ነገሩን ወደኢትዮጵያ ስናመጣው የፊደላችን ዕድሜ በሺህ ዓመታት የሚቆጠር ለመሆኑ ድንጋይ ይመሰክራል፤ የጽሕፈት መኪና ከገባ ግን ከመቶ ሃምሳ ዓመት የሚበልጥ አይመስለኝም፤ ዛሬ የመለስ ዜናዊ አገልጋዮች እንደሚሉት የኢትዮጵያ ታሪክ ከመቶ ዓመት አይበልጥም ሲሉ፣ በወግ በሥርዓት የተመዘገበ ታሪክ የለም ማለታቸው ይመስለኛል፤ በዚህም ምክንያት እኛ ባለቤቶች እንሆንበታለን ማለታቸው ነው፤ እንግዲህ መክሸፍ መክሸፍን እንዴት እንደሚወልድ በገሀድ ይታያል፤ ፊደል ከሸፈ፤ ጽሕፈት ከሸፈ፤ እውቀት ከሸፈ፤ ኅትመት ከሸፈ፤ በመክሸፍ መሰላል ወንበሩ ላይ የወጡት የመክሸፍ ልጆች ናቸው፤ እነዚህ የመክሸፍ ልጆች የመክሸፍን ዕድሜ ለማራዘም ቢሞክሩ ምን ያስደንቃል? አፈናውን ቢያጠናክሩት፣ የዜና ማሰራጫዎችን ሁሉ በቁጥጥራቸው ስር አድርገው ውሸታቸውን የሚያጋልጡባቸው ጋዜጦች እንዳይኖሩ ማድረግ የባህርያቸው ነው፤ ደንቁሮ ማደንቆር የባሕርይ ነው።

በመገናኛ ብዙኃን ዛሬ ዓለም የሁሉም ሆናለች፤ ለአፈና አገዛዝ አትመችም፤ ኢትዮጵያውያን ፊደልን ሲንቁ እውነትንና እውቀትን ናቁ፤ እውነትንና እውቀትን ሲንቁ ዳገቱን እየተዉ ቁልቁለቱን ወረዱ! ቀላል ነው፤ መክሸፍ ማለት አንዲህ ነው።

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ሰኔ 2006

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule