• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ነጻነት ሰው ከመሆን የሚገኝ መብት ነው”

November 15, 2016 02:13 am by Editor 3 Comments

ግዛው ለገሰ በጣም መሠረታዊና አንገብጋቢ፣ ጊዜያዊም ጉዳዮችን አንሥቷል፤ በበኩሌ ጉዳዮቹን በማንሣቱ በጣም እያመሰገንሁት አስተያየቴን በአጭሩ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡

‹‹ህወሓት የተቋቋመው በአማራ ጥላቻ ነው፡፡ ይህን ሀቅ ሳይቀበሉ ስለነፃነት ማታገል አይቻልም፡፡ ነፃነት ደግሞ የዜግነት መበት እንጂ የወል መብት አይደለም፡፡ ነፃነት በማንነት ትግል አይገኝም፡፡›› ግዛው በጣም መሠረታዊ ነጥብና ሀሳብ አቅርበሃል፤ ነገር ግን ድብልቅልቁ ወጣብኝ!

መነሻ፡–‹‹ሕወሀት የተቋቋመው በአማራ ጥላቻ (ላይ?) ነው፤›› ከዚህ ትነሣና፡–

‹‹ይህንን ሀቅ ሳይቀበሉ ስለነጻነት ማታገል (መታገል?) አይቻልም፤›› ትላለህ፡፡

እንደምረዳው ግልጽ ያልሆነልኝ ግዛው ሁለቱን ዓረፍተ ነገሮች እርስበርሳቸውና እያንዳንዳቸውን ከነጻነት ጋር ያቆራኛቸው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ በእኔ አስተሳሰብ ምንም ግንኙነት የላቸውም፤ የአማራን (በአንተው ቃል ለመጠቀም) ጥላቻም ሆነ በአማራ ላይ ያለውን ጥላቻ ይዞ ለነጻነት መታገልም ሆነ ማታገል የማይቻልበት ምክንያት አይታየኝም፤ ነጻነትን ‹‹አማራ›› ከምትለው ጋር አቆራኝተኸዋል! እንዴት ብሎ?

ሁለተኛው ዓረፍተ ነገርህ ለእኔ በጣም ፈር የለቀቀ ነው፤ ለእኔ ነጻነት ሰው ከመሆን የሚገኝ መብት ነው፤ ስለዚህም የሰው ልጆች ሁሉ መሠረታዊ የጋራ (የወል) መብት ነው፤ ከዜግነት ጋር ማያያዝህ በመሠረቱ ትክክል ቢሆንም ነጻነት የሌላቸው ዜጎች በያለበት ይገኛሉ፤ ከዚሁ ጋር አያይዘህ ‹‹ነጻነት በማንነት ትግል አይገኝም፤›› ስትልም በዝቅተኛ ደረጃ ያሉ ማንነቶችን (ለምሳሌ ባል/ሚስት መሆን፣ ክርስቲያን/እስላም መሆን፤ የዚህ/የዚያ ጎሣ አባል መሆን፣ …) ከሆነ ትክክል ትመስለኛለህ፤ በሰውነትና በዜግነት ደረጃ ካየኸው ግን እንለያያለን፤ ለእኔ መሠረታዊው ነጻነት የሚፈልቀው ማንነትን አንደኛ በሰውነት ደረጃ ሁለተኛ በዜግነት ደረጃ እያዩ በመታገል ነው፤ እኩልነት የነጻነት አካል ነው ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፡፡

እኩልነትን ከነጻነት ጋር አቆራኝተህ ለመታገል የምትችለው በሰውነትና በዜግነት ደረጃ ብቻ ነው የምትል ከሆነ አብረን እንቆማለን፤ ሌሎች ዝቅተኞች ማንነቶች ለእኩልነት ቦታ የላቸውም፤ እንዲያውም አብዛኛውን ጊዜ ጸረ-እኩልነት ናቸው! የአንዳንድ ጎሣዎች አቀንቃኞች የጎሣቸው ሥርዓት ‹‹ዴሞክራሲያዊ›› ነው፤ ነጻነት አለበት ይላሉ፤ (በሴቶች ላይ የሚያሳድሩትን ክፉ ጭቆና ይረሱታል!) ይህ ወይ የማያውቁትን ለማሞኘት ነው፤ ወይም ስለዴሞክራሲና ስለእኩልነት፣ ስለነጻነት አለማወቅ ነው፡፡

ግዛው ያነሳኸው ዋና ነጥብ ሁሌም የሚረሳና በጎሠኛነት አረም የተሸፈነ ነው፤ ዜግነት! የአንድ አገርን ሰዎች በሕግ በነጻነትና በእኩልነት አዋኅዶና አዛምዶ የሚይዛቸው ዜግነት ነው፤ በጎሠኛነት ያለው መንገድ የወያኔ ብቻ ነው፤ የወያኔን መንገድ ተከትሎ ወደዜግነት መድረስ የሚቻል አይመስለኝም!

በመጨረሻ አንድ ያነሣኸው ነጥብ አለ፤ ጥላቻ በመሠረቱ ክፉ የአእምሮና የመንፈስ በሽታ ነው፤ በዚህም በሽታ ይበልጥ የሚጎዳው ማኅደሩ ነው፤ ስለዚህም ‹‹አማራን›› መውደድም ሆነ መጥላት፣ ‹‹በአማራ›› መወደድም ሆነ በጥላቻ መታየት ለዜግነት፣ ለአኩልነት፣ ለነጻነትና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግዴታ አይደሉም! በተግባር ፍቅርና አብሮ የመኖር ልምዱ መኖሩን ከተለያዩ ጎሣዎች የወጡት ወጣቶች ተጨባጭ ማስረጃዎች ናቸው፡፡

እንኳን ሰው ነግሯቸውና አይተውም መረዳት የማይችሉ በሥልጣንና በሀብት በተለወሰ ጎሠኛነት የሰከሩትን ለማሳመን አይቻልም፤ በማየት መረዳት የሚቻል ቢሆንማ ኤርትራን አይቶ ልብ መግዛት ቀላል ነበር፤ በፖሊቲካ ጉዳይ ገና በሕጻንነት ደረጃ መሆናችን የሚረጋገጠው ጎሠኛነት በሃያ አምስት ዓመታት ውስጥ እያደገና እየሰፋ፤ ተምረናል የሚሉ ሰዎች የተሰለፉበት የእንጀራ እናት ሆኖ ማደጉና መስፋፋቱ ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ኅዳር/2009

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. ገብረየሱስ says

    November 23, 2016 07:20 pm at 7:20 pm

    ህወሓት የተቋቋመው “በአማራ ጥላቻ ነው” ይህ ስህተት ነው መስተካከል ኣለበት ያንተውና የሌላውን ለመለየት። ልክ እንደ መኢሶን፣ ኢህኣፓ፣ ኢድዩ፣ ደርግ፣ እጨዓት፣ ሌሎችም ህወሓት ተመሰረተ። በሂደት ግን ሌሎች ኣንድነቶች ሲሰው እነ ስብሃት ነጋ፣ ኣባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን፣ ታዳጊው መለስ ዜናዊ እድል ኣግኝተው የኣማራ ጥላቻ ካርታ ተጫወቱበት። ስለዚህ እነኝህን ለይተን ካስቀመጥናቸው ከኣንድነቶች ጋር ለመስራት ይቀላል። ካልሆነ በትግራዮች በኣማራ በኦሮሞ በዓፋሮች ስም እንደ ወያነ በጅምላ መወንጀል እውነተኞች ይራራቃሉ መልካም ስራ ሊሰራም ኣይችልም።

    Reply
  2. Gebito says

    November 25, 2016 04:53 pm at 4:53 pm

    Goitay Golgul,

    Yet again there is an image in the article but no mention of who is who and indication of the source or credit to it. Still you claim to be credited – funny that, especially news mixed with opinions of the author. Last time you said that it was intentional a hand written note was scanned reverse side. Come on guys grow up stop this militancy in your replies to readers. All these recycled cut-and-paste news sites pride yourselves as journalists you don’t even have a single reporter or correspondent anywhere so I suggest take it easy and grow slowly. Don’s chase your tails in attempting to be reliable sources. Gebito!

    Reply
    • Editor says

      November 26, 2016 12:17 am at 12:17 am

      Gebito,

      If, with evidence, you are able to provide us the source of the picture, we will give credit for that. The rest is garbage.

      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule