• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወገናዊ ጥሪ ወገን ለሆነው የትግራይ ህዝብ

August 28, 2016 12:54 am by Editor 2 Comments

ይህን ፅሁፍ ነፃ አስተሳሰብን ከሚያውኩ ግላዊ ባህርያት ነፃ በመሆን ማንበብ ያስፈልጋል። የጎሳ፣ የብሄር ወይም የቋንቋ መለያ አጥር ውስጥ ከቆምን የፅሁፉ አላማም ሆነ ይዘት በውል ላይታየን ይችላል። ቢታየን እንኳን ምናልባት ግምገማችን ሊዛባ ይችላል። ምክንያቱም መልእክቱን ወይም አላማውን የምንገመግመው ከቋንቋችን፣ ከብሄር ማንነታችን ወይም ከትውልድ ቀያችን አንፃር ስለሚሆን ሚዛናችን ወይም ግንዛቤያችን ስህተት ይሆናልና ነው።  ሰው መቼም ሲያስብ፣ ሲወስንና እርምጃ ሲወስድ አስተሳሰቡን፣ አወሳሰኑንና እርምጃ አወሳሰዱን በስሜት ሀይል ከሆነ መነሻው፣ መንገዱም ሆነ ግቡ ስህተት መሆኑ አይቀርም። ውጤቱም ጥፋት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበት ቀውስ መነሻው ያስተሳሰብ፣ ያወሳሰንና የድግጊት መነሻችን ነፃ አእምሮ ሳይሆን ስሜት ብቻ ስለነበረ ይመስለኛል። ሰው በእውነቱ ሳይሆን በስሜቱ ከተመራ መደረሻው ውድቀት መሆኑ አይቀርም። እኔ የምደግፈው እገሌ የሰጠውን ሃሳብ ወይም የያዘውን አቋም ነው፦ ምክንያቱም ብሄሩ የኔ ስለሆነ፤ እንቶኔ የተባለው ፓርቲ ደጋፊ ነኝ፤ ምክንያቱም አባላቱ የኔ ብሄር አባላት ስለሆኑ  በሚል መስመር ብንሄድ የት እንደምንደርስ ለማወቅ ነጋሪ አያስፈልገንም። በጥቅሉ ያመለካከታችንና  የፍርዳችን ትክክለኝነት መስፈሪያው ነፃ መረጃ ወይም ነፃ አእምሮ መሆኑ ቀርቶ ያልተመረመረ ጭፍን ወገንተኝነት ከሆነ ውጤቱ የዘለአለም ጥፋት ነው። ጥፋቱም ከግልና ቡድን አልፎ ላገርና ህዝብ ይተርፋል። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ አበሳና ፍዳ ምንቹ  ይህ ሳይሆን አይቀርም። ብዙዎቻችን እምነትና አቋም የምንይዘው፣ ውሳኔና ፍርድ የምንሰጠው በማስረጃ ሳይሆን በፍረጃ መሆኑ ስለሚታይ የፅሁፌ መልእክት የዚህ ክፉ አባዜ ሰለባ እንዳትሆን ሰግቼ በዋና ከማልወጣው የሃሳብ ባህር ውስጥ ገባሁ እንጂ አነሳሴ እንኳን ስለሰው ግንዛቤ ወይም ያስተሳሰብ ህግ ለመደስኮር አልነበረም። እናም ወደነጥቤ ልመለስ። ግን ለምወደው የትግራይ ህዝብ የምሰጠው ማሳሰቢያ አንባቢ ከቋንቋና የብሄር ማንነት ነፃ በሆነ አመለካከት እንዲመዝነው አደራ ማለቴን አልተውም።

ዛሬ በትግራይ ህዝብና በሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ መካከል የወደፊቱን ዘለአለማዊ ህይወት የሚወስን ታሪካዊ አጋጣሚ ተፈጥሯል። አጋጣሚው እንደሁኔታው ክፉም በጎም ሊሆን ይችላል፣ ይህን የሚወስነው የትግራይ ህዝብ ነው። የትግራይ ህዝብ ዛሬ ወሳኝ በሆነ የታሪክ ነጥብ ላይ ቆሟል። በዚህ ወሳን ነጥብ ላይ ቆሞ የሚሰጠውም ፍርድም ሆነ የሚወስደው ምርጫ ወንድሙ ከሆነው የቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የሚኖረውን የወደፊት ግንኙነት እስከወዳኛው ይወስናል። ምርጫውም በቋንቋና በዘር በሚመስሉት ጥቂት ግለሰቦችና በሌላው ኢትዮጵያዊ መካከል ነው። ምርጫው ቀላል ላይሆን ይችላል ግን ወሳን ነው።

በአንድ በኩል በብኼር ማንነትና በቋንቋ ሚዛን በጭካኔው ወደር የሌለውንና አንድ ሃሙስ የቀረውን የጥቂት አንባገነን ግለሰቦችን ቡድን መወገን ወይም ፍትህ ከተጓደለበት የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ቆሞ ለሃቀኛና አስተማማኝ ዲሞክራሲ አብሮ በመታገል ወንድም ከሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በማይበጠስ የታሪክ ገመድ ተሳስሮ ለዘለአለም መኖር ነው።  በዚህ ወሳን ወቅት ከቋንቋና ብሄር መጀሳሰል በቀር ባመለካከት ከማይወክሉት ጥቂት ገዢዎች ጋር መወገንና  ከብዙሀኑ ህዝብ ጋር መቆራረጥ እጅግ አስፈሪና አደገኛ ምርጫ ነው።

በእኔ አስተያየት አሳምሬ የማውቀውና ደጉ የትግራይ ህዝብ ብዙሃን ወንድሞቹን በጥቂት አንባገነኖች ይለውጣል ብዬ አልገምትም። የትግራይ ህዝብ እስከማውቀው ድረስ ሰላማዊና በኢትዮጵያዊነቱ ጥርጥር የሌለው ቅን ህዝብ ነው። እንደአለመታደል ሆኖ ክልሉ ለረጅም ጊዜ በጦርነት ቁም ስቅሉን ሲያይ የኖረ ህዝብ ቢሆንም በሌሎች ለደረሰበት መከራ ሁሉ የኢትዮጵያን ህዝ ተጠያቂ አድርጎ አያውቅም። በየትኛውም የሀገሪቱ ክልል ከህዝብ ጋር ተስማምቶ ከመኖር በቀር ከማንኛውም ጎሳወይም ብሄር ጋር የተለየ ግጭት ውስጥ ገብቶ የሚያውቅ አይመስለኝም። የሚታወቀውም በሰላማዊነቱና ተግባቢነቱ ነው።

ይሁን እንጂ እንደማንኛውም ህዝብ ሲደርስበት የነበረውን ጭቆና ሰበብ በማድረግ በትከሻው ላይ ተንጠላጥለው ስልጣን ላይ የወጡ እፍኝ የማይሞሉ ብልጣብልጦች በስሙ በመነገድ ሌሎች ወንድሞቹ ከገዢዎች ጋር በአንድ አይን እንዲመለከቱት ያላደረጉት ጥረት የለም። በስሙ ገዝተዋል፣ ጨቁነዋል፣ ገድለዋልም። ለትግራይ ህዝብ ፍትህና ነፃነት የሞቱትን ሺዎች አፈር አልብሰውና ቃልኪዳናቸውን አጥፈው ለትግራይ ህዝብ ሳይሆን እፍኝ ለማይሞሉ ታማኝ ትግሬዎች፣ አማሮች፣ ዖሮሞዎች፣ ጉራጌዎችና ሌሎች አገልጋዮቻቸው ቀለብ ሰፋሪ ሆነዋል። የትግራይ ህዝብ ከህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ገዢ  ቡድን ያገኘው ጥቅም ስም ብቻ ነው። የግፍ አገዛዛቸው ሰለባ ከመሆንም አላመለጠም። ይባስ ብሎ ቋንቋውን በመናገርና በስሙ በመጨቆን በገዛ ወገኖቹ በክፉ አይን እንዲታይ አድርገውታል።

ይልቁንም ከመቼውም በባሰ ዛሬ በሚገኝበት አጣብቂኝ ውስጥ ከተውታል። በአንድ በኩል ከጥቂት ብልጣብልጦች በቀር እንደህዝብ ባላተረፈበት ስርአት እንደጨቋኝ ህዝብ ስለታየ ስርአቱ ቢፈርስ እጠቃ ይሆናል በሚል ስጋት ግፈኞቹን እስከነጉድፋቸው ለመደገፍ ሲያመነታ በሌላ በኩል ደግሞ በጠራራ ፀሃይ የፈጸሙት ግፍና መከራ ለፍትህና ዲሞክራሲ ቀናኢ  የሆነውን ህዝብ ሆድ ማሻከሩ አይቀርም። ለፍትህና ዲሞክራሲ፣ ለነፃነትና እኩልነት ልጆቹን የገበረው የትግራይ ህዝብ እኩልነትና ነፃነት የጠየቁ ሰላማዊና ለጋ ወጣቶች ደም  በየአደባባዩ ሲፈስ አበጀ የሚል አይመስለኝም።

የሆነው ሆኖ ዛሬ የትግራይ ህዝብ ከፊቱ ወሳን ምርጫ ቀርቦለታል። ምርጫው ከገዢው መደብ ጋር በማበር ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እስከወዳኛው መቆራረጥ ወይም ለፍትህና ዲሞክራሲ ደሙን እየገበረ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በመወገን በታሪክ ሞገስና በህዝብ ዘንድ ዘለአለማዊ ፍቅርና ክብር መጎናፀፍ ነው። የትግራይ ህዝብ ምርጫ ፍትህ፣ ዲሞክራሲ፣ እኩልነትና ህዝባዊነት እንደሚሆን የምጠራጠርበት ምክንያት የለኝም። ለምን ቢባል በስልጣን ላይ ያለው ቡድን ከቋንቋውና ብሄርብሄሩ በቀር በምግባሩ የትግራይን ህዝብ ስለማይመስል ነው። ለምን ቢባል የትግራይ ህዝብ ወንድሙ የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ የፍትህ ጥያቄ በንፁህ ህሊና እንጂ በቋንቋና በብሄር ዳኝነት ይዳኘዋል የሚል እምነት ስለሌለኝ ነው። ለምን ቢባል የትግራይ ህዝብ እንደህዝብ የማይታረም የታሪክ ስህተት ለመስራት ይወስናል ብዬ ስለማላምን ነው። ለምን ቢባል የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እንደቡድን የከዳውን የኢትዮጵያ ህዝብ የትግራይ ህዝብ እንደህዝብ ዳግም ይከዳዋል ብዬ ስለማላምን ነው። ስንት የታሪክ ፈተና በጽናት ያለፈው የትግራይ ህዝብ ይህን ልላ የታሪክ ፈተና  ይወድቃል ብዬ አልገምትም።

መልካሙን ለማየት ያብቃን።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    September 6, 2016 10:43 am at 10:43 am

    A very nice idea,if if took the wrong way,it will surely be a disaster for the people of Tigray,a man with out history is like a tree with out roots.This is not our history,our history is Ethiopia under God.

    Reply
  2. Tadesse says

    September 6, 2016 11:15 am at 11:15 am

    Another thing is that we have no any relation with these brutals like Abay Weldu.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule