• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ኧረ እኔስ ጨነቀኝ”

November 4, 2013 09:58 pm by Editor Leave a Comment

ሰውየው ያገባት ሚስቱ ቤተሰቦቿ ሃብታሞች ነበሩ። እሱ ደግሞ መናጢ የሚባል ደሃ ነበር። አንድ ቀን የማይቀረው ሞት የሚስቱን አባት ነጠቀና ቀብር ወጡ። አስከሬን እየተከተሉ ሲያለቅሱ ባል ሚስቱ ጎን ሆኖ ልክ እንደሷ “አባቴ አባቴ” በማለት ያለቅስ ጀመር። ሚስትም ” የት የወለደህን ነው አባቴ የምትለው” በማለት አፍታ ወስዳ ባሏን ገሰጸችው።

ባል ለቅሶውን ቀየረና “አባቷ፣ አባቷ …” በማለት ያስነካው ጀመር። ይህን ጊዜ ሚስት አሁንም ለቅሶዋን ቆም አድርጋ “የበላኸው ጨማ፣ የጠጣኸው ጠጅ አያንቅህም? አባቷ አባቷ የምትለው” አለችው። ባልም ደንግጦ ላፍታ ዝም በማለት ካሰበ በኋላ “አረ እኔስ ጨነቀኝ፣ አረ እኔስ ጨነቀኝ … ” በማለት እያለቀሰ የባለቤቱን አባት ሸኘ። ይህ አጠር ተደርጎ የቀረበ የቀድሞ ምሳሌ ነው።

ኢትዮጵያውያን አገራቸውን ይወዳሉ። አገራቸውን በልጅ፣ በሚስት፣ በእናት፣ በአባት፣ በቤተሰብ … እየሰየሙ አንጎራጉረዋል። ተቀኝተዋል። ተደርሰዋል። ፎክረዋል። አቅራርተዋል። በዚህች አገራቸው ጉዳይ ለሚመጣ ማናቸውም ችግር “ቀልድ የለም” በማለት ልዩነታቸውን ወደ ጎን በመተው ተፋልመዋል። ወድቀዋል። ባንዲራቸውን ከፍ አድርገው ዘምረዋል።

በአንድ ወቅት ተፈጥሯል ተብሎ ከተመሰከረልን “የባንዳነት ገድል” ውጪ፣ እኛ ኢትዮጵያዊያን ጠላት ሲመጣብን፣ ወራሪ ሃይል ሲያድምብን፣ አገራችንን ሊደፍሩ የሚቃጣቸው ሲነሱብን መተባበርና አንድ መሆን ልዩ ባህላችን ነው። የምንኮራበት ስጦታችንም ነው። ጠላትን ለመመከት በተደረገ ጥሪ በገዢዎቹ አኩርፎ “ወዲያ በሉ” የሚል ትውልድ አገራችን አላበቀለችም። ጠላትን ደቁሶና አሳፍሮ የሚመልስ ትውልድ እንጂ!!

ህወሃት እመራዋለሁ የሚለውን ህዝብና አገር ወደ ጎን በማለት ከሻዕቢያ ጋር ፍቅር ተጣብቶ በቀልን በዘራበት ወቅት፣ ኢትዮጵያን የሚወዱ ዜጎችን በጠላትነት እየፈረጀ ሲወነጅል፣ የብሔር መርዝ እየዘራ አብሮ የኖረ ህዝብ ሲያጋጭ፣ አገርን ዘርፎ ለዘራፊ አሳልፎ ሲሰጥና የኢኮኖሚ አሻጥር በመፈጸም የህዝብ ሃብት ላይ ለጠቅላይ ሲጫወት፣ “ያገባናል” በማለት ለአገራቸው የሚከራከሩትን በጠራራ ጸሐይ ሲገል፣ ሲያስርና ሲያንገላታ ቆይቶ ራሱ በፈጠረው ችግር ህጻናትን በጀት ሲያስቆላ “ዞር በል” ያለው አልነበረም። ይልቁኑም ከዳር እስከዳር በመነሳት በባድመ ጦርነት ፈንጂ ላይ በመሮጥ አገርንና ህዝብን የሚያኮራ ገድል ለመፈጸም ተችሏል።

“ጦርነትን እንሰራዋለን” የሚሉት ህወሃቶች ግራ ሲገባቸው፣ እንደ ህወሃት ተግባርና ተንኮል ሳይሆን ለአገር ቅድሚያ በመስጠት ሻዕቢያን በመደቆስ ድል ከተቀዳጁ በኋላ ዳግም ክህደት ተፈጽሞባቸው ውሉ ባልታወቀ ጦርነት ወገኖቻችን አሁን ድረስ በጦር ሜዳ እሳት ዳር ተጥደው ይገኛሉ። ይህ የሚሆነው ህወሃት ሊንደው ሌት ተቀን የሚባትትበት የቀደመው የአገር ፍቅር የትብብር መንፈስ እንጂ ሌላ ኢህአዴግ የፈጠረው ውለታ ይዟቸው አይደለም። ይህ በጎ ታሪካችን ነው። አገር ወዳድ የሆንን በሙሉ እንኮራበታለን። እንመካበታለን።

በሌላ በኩል አስደንጋጭ ታሪክ አለን። ለመልካም ነገር የመተባበር ችግር አለብን። አገርን ለመታደግና በሰለጠነ መንገድ ልዩነትን የመቻቻል ጣጣ አለብን። በልዩነት ውስጥ ተባብሮ አገርን ወደ መልካም ጎዳና የማሸጋገር ራዕይና ፈቃደኛነት የለንም። የዛሬ አርባ ዓመት አካባቢ የግራው ፍልስፍና አራማጆች ነን በሚሉ የተሰበከው “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ …” የሚል ለአንዱ ህልውና የሌላው መጥፋት ግዴታ እንደሆነ የታመነበት አስተሳሰብ እስካሁን ግራ አጋብቶን አለ፡፡ በንጉሱም፣ በደርግም ሆነ በዘመነ ኢህአዴግ ሊታረቅ ያልቻለው ይህ በሽታችን “በሞተ ስርዓትና አገዛዝ” እንድንመራ አስገድዶናል። ይህ በሽታችን ስር ከመስደዱ የተነሳ የአገራችንን ሁኔታና አካሄድ እንደ አልቃሹ ሰውዬ “አረ እኔስ ጨነቀኝ” የሚያሰኝ ሆኗል።

እርስ በርስ የመጠላለፍና አንዱን በሌላው ላይ የማሳደም፣ ራዕይና አርቆ አሳቢነት፣ ከሁሉም በላይ ቀናነት የጎደለው የተቃውሞ ፖለቲካ መንደር ለሁሉም ወገኖች ዋስትና በሚሰጥ መልኩ አለመቃኘቱ የአገሪቱን ህልውና በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎታል። በዚሁ ሳቢያ ህወሃት የዘራው የጥላቻ መርዝ የሚያረክስ መስመር የሚዘረጋልንና በተበዳዮችና በበዳዮች ዘንድ ክብር የሚሰጠው “ተተኪ” መሪ ማግኘት አቅቶን፤ ያሉን ተቃዋሚ ሃይሎችም “በጠላቶቻችን መቃብር ላይ …” በማለት ካልፈረሰ በስተቀር መገንባት አይቻልም በሚል ግራ የገባው ዲስኩር ሰክረው ሁለት አስርት ዓመታት “አረ እኔስ ጨነቀኝ” እያልን ለመኖር ተገደናል።

ኢህአዴግ ወላልቋል። አሁን ከብበውና አንቀው ከያዙት ችግሮች አንጻር፣ እንኳን ለማይወዱት በስሙ ለሚምሉበት ግልገሎቹና ባሮቹ ዋስትናቸው ሊሆን እንደማይችል እየተነገረ ነው። ሙስናው፣ ድህነቱ፣ ፖለቲካዊ ንቅዘቱ፣ ማርጀቱ፣ በቡድን መከፋፈሉ፣ የተሳፈረበት የግፍ ባቡር ነዳጅ መጨረሱ፣ በከፍተኛ ደረጃ መተማመን የማይችሉበት ደረጃ ለመድረሳቸው ምስክር ሆኗል። ይኸው አደገኛ ወቅት አገር ወዳዶችን እያስጨነቀ ነው። አገር በቡድንና በደቦ ይመራል በሚል ዘባተሎ ምክንያት በየቀኑ የሚሰማው የስርኣቱ የመደንበር ምልክት ህግና ህጋዊነት ማክተማቸውን የሚያረጋግጥ ሆኗል። በህወሃትም ሆነ በኢህአዴግ ደረጃ አለቃና ታዛዥ መለየት አልተቻለም። የበላይና የበታች ተቀላቅሎ አቤት ማለት ያዳገተበት ወቅት ላይ ተደርሷል። “ህግ ፈረሰ፤ መንግስት ፈረሰ” ነውና !!

አሁን ያለንበት ወቅት በለውጥ ቋፍ ላይ ነው። ከውስጥም ከውጪም ራሱ ህወሃትና ድቃይ ድርጅቶቹ ዘንድ ፍርሃቻ አይሏል። በትራፊ ዘመን ከህሊናቸው ጋር ለመታረቅ የሚመኙም አሉ። ባለቀ ወቅት አገራችን እንዳለች እንድትቀጥል እርቅን የሚሹ ኢህአዴጋዊያን ጥቂት አይደሉም። የህዋሃት ሰዎችም ቢሆኑ ከዚህ የስጋት ርእደት ውጪ እንዳልሆኑ እየተሰማ ነው። በሁሉም ደጅ “አረ እኔስ ጨነቀኝ” የሚሉ በዝተዋል። ያጣነውና የተቸገርነው ለበጎ ተግባር የሚያስተባብር ጀግና ብቻ ነው። በወዳጅም፣ በጠላትም፣ በመሃል ሰፋሪውም፣ በአብዛኛው አድፋጮችም (silent majority)፣ በህወሃት ቁንጮዎችም ሆነ ሌሎች ስማቸው ባልተጠቀሱት ዘንድ ተቀባይነት ያለህ፣ ያለሽ፣ ያላችሁ፣ የጸዳችሁ፣ ያልተነካካችሁ፣ “እንከበራለን” የሚል ጽኑ እምነት ያላችሁ “አረ እኔስ ጨነቀኝ” ለሚሉ ወገኖች ድረሱ!!

ሁሉንም ወገን ነጻ የሚያወጣ ማን ነው? ማን ናት? ለሰብዓዊነት የቆመ … እንደ ሴትየዋ እንደ ራስህ ሳይሆን እኔ እንደምልህ … ከሚል የትዕዛዝና የታቃዋሚ መንግሥትነትና አምባገነንነት የራቀ፤ ራሱን ጨምሮ ሌላውን ነጻ የሚያወጣ እምነት ለኢትዮጵያ!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule