• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ33ቱ የአዳማ ፔቴሽን ፈራሚ ፓርቲዎች የተሰጠ መግለጫ

January 10, 2013 04:33 pm by Editor Leave a Comment

በምርጫ አስፈፃሚው፣ ከምርጫ አስተዳደርና በምርጫው ሂደት ላይ የሚታዩ መሠረታዊ ችግሮችን በማንሣት ችግሮቹ ስለሚፈቱበት መንገድ የውይይት /ምክክር/ መድረክ እንዲመቻች ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድና ለመንግሥት አካላት ጥያቄአችንን ማቅረባችን ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማያሣምኑ ምክንያቶች በመስጠት ጥያቄዎቻችንን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረጉን በቃል የገለፀልን ሲሆን ለመንግሥት ላቀረብነው ጥያቄ ምላሹን እየተጠባበቅን ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ የተጣለበትን የአገርና የሕዝብ ኃላፊነት ወደጐን በመግፋት ምርጫውን ሠላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ለማድረግ የመወዳደሪያ ሜዳውን ከማስተካከል ይልቅ የገዢው ፓርቲ ወገንተኝነቱንና ጉዳይ ፈፃሚነቱን ባረጋገጠበት አቋሙ በመግፋት ወደ ምርጫ እንቅስቃሴ መግባቱን በይፋ አውጇል፡፡

እኛ በያዝነው ሠላማዊ የትግል መሥመር በምርጫ የመሣተፍ /አለመሳተፍ ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ያለመሆኑንና የሕዝብ ዘርፈ ብዙ ውስብስብ ጥያቄዎች ምላሽ የምንሰጥበት ብቸኛው የመንግሥት ሥልጣን መያዣ መሣሪያችን መሆኑን በተደጋጋሚ በግልጽ አስቀምጠናል፡፡ የአካባቢ ምርጫ ወደ ሕዝቡ ዘልቆ ለመድረስ የሚያስችል እንደመሆኑ ከአገር አቀፍ ምርጫ ያነሰ ትኩረትና ቦታ የምንሰጠው አይደለም፡፡ ይልቁንም ለምንፈልገው የሥርዓት ለውጥና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ መሠረቱ የሚጣለው በሕዝቡ ውስጥ ስለሆነ ለዚህ ምርጫ ተገቢውን ትኩረት ሰጥተን ጠንክረን ለመንቀሳቀስ ዝግጅታችንን በተባበረና በተቀናጀ መንገድ ለማድረግ እየተንቀሳቀስን ባለንበት ነው የጋራ ጥያቄዎቻችንን ያቀረብነው፡፡ ይሁን እንጂ ምርጫ ቦርድ በኢህአዴግ እየተመራና እየታገዘ ከጊዜ ሰሌዳ በፊት በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ መወያየት ይቅደም በማለት 41 የፖለቲካ ፓርቲዎች በአዳማው ስብሰባ ላይ ላቀረብነው የቦርዱ ሰብሣቢ “የውይይት መድረክ ይዘጋጃል” በማለት የመለሱትን፣ እንዲሁም 33 በሕጋዊና ሠላማዊ መንገድ የምንታገል የፖለቲካ ፓርቲዎች ፔቲሽን ፈርመን ላቀረብነው የቦርዱ ጽ/ቤት ኃላፊ “ባትጠይቁንም ማድረግ ያለብን ነው” “. . .  ጉዳዩን ሣታጮሁት በትዕግሥት ጠብቁ” ማለታቸውን ክደው ከአዳማ በተመለሱ በ4ኛው ቀን አፀደቅን ባሉት የጊዜ ሰሌዳ ገፍተውበታል፡፡ በዚህ መሠረት ቦርዱ መዝግቤ የምሥክር ወረቀት ሰጠሁ ብሎ ከሚዘረዝራቸው 75 የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ 28ቱ ብቻ የምርጫ ምልክት በወሰዱት፣ የምልክት መምረጫ ጊዜ አልፏል /ተጠናቃል/፣ ከማለት አልፎ የሕዝብ ታዛቢዎ አስመርጬ የመራጮች ምዝገባ ጀምሬአለሁ፣ በቀጣይም በጊዜ ሰሌዳዬ መሠረት እቀጥላለሁ የሚል ዘመቻውን ተያይዞታል፡፡ በምርጫ ህጉ መሠረት በምርጫ ዘመን በፓርቲዎች የሚደረገው ቅስቀሳና በፓርቲዎች መካከል በመገናኛ ብዙኃን የሚካሄደውን የፖሊሲዎች አማራጭ አቀራረብ ቦርዱ በፍትሃዊነት የአየር ጊዜ ደልድሎ መምራት ሲገባው ራሱ አፀደቅሁ ካለው የጊዜ ሰሌዳ ውጪ በኢህአዴግና መንግሥት መገናኛ ብዙኃን የምርጫ ውድድር እንቅስቃሴ /ክርክር/ ሲያደርጉ ማስቆም አልፈለገም፣ አልቻለም፡፡

በዚህ ተጨባጭ እውነታ ውስጥ ነው ጥያቄዎቻችሁ የተመለሱ ናቸው . . .በማለት ወደ ምርጫ ማስፈጸም የገባው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ የምርጫ መወዳደሪያው ሜዳ ተስተካክሏልና ያለአንዳች ጥያቄ በምርጫው ተሣትፋ ካልፈለጋችሁ ተውት የሚል የማንአለብኝነት ግልጽ መልዕክት ነው፡፡ ስለሆነም ለጉዳዩ ዋነኛና ቀዳሚ ባለቤት ለሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ምርጫውን ለምትደግፉና ለምትከታተሉ የዓለም ማኅበረሰብ አባላት በድጋሚ የምናስተላልፈው ጥሪ ምርጫ ቦርድ በኢህአዴግ አይዞህ ባይነት በያዘው “ካፈርኩ አይመልሰኝ” አቋም መግፋቱ በጥያቄአችን መሠረት የምርጫ መወዳደሪያ ሜዳውን የሚያስተካክል ስላልሆነ በቀጣይ ተወያይተን የምናሳውቃችሁን የጋራ አቋም በንቃት እንድትጠብቁና ሂደቱን በትኩረት እንድትከታተሉ ነው፡፡

ቦርዱ 28 ፓርቲዎች ብቻ በተመዘገቡበትና ለጥያቄዎቻችን (ጥያቄዎቹ የ41 ፓርቲዎች መሆናቸውን በማጤን) መልስ ባልተሰጠበት ይልቁንም ችግሮቹ እየተባባሱ በመጡበት በምርጫው እቀጥልበታለሁ የሚለው አቋም ምርጫውን ተአማኒ አሣታፊ እና ተቀባይነት ያለው አያደርገውምና ውሣኔውን እንደገና በመመርመር ለአገራችን የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አስተዋጽኦ ለማድረግ አሁንም ጊዜው ያልመሸበት መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ሌሎች አሁን በተያዘው የምርጫ ሂደት ውስጥ የገባችሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረብናቸው ጥያቄዎችና ችግሮቹ የሃገርና የጋራ መሆናቸውን ተረድታችሁ ለዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ዳግም አገራዊ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን፡፡

በተባበረ ትግላችን ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን!

ታህሳስ 25/2005፣ አዲስ አበባ

በአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት የተሰራጨ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule