ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፬” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አራት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡
መልስ
ፈረሱን እንደሰው – አስታጠቀው ሱሬ
መተኮሱንማ – ማንም ይተኩሳል
ኃይለማርያም – ማሞ አንጀት ይበጥሳል
በማለት በዜማ – የዘመርንላቸው
ኃይለማርያም – ማሞ ማለት እኚህ ናቸው።
ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? –፭” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ የዛሬ ሳምንት መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡
በሕይወት ዘመኑ – ሳይታክት የሰራ
መልካም ፍሬ – ያለው የሀገር በረከት
በሆነ አጋጣሚ – ብቅ ይላል በድንገት
እንደዚሁ ሁሉ – እኝህ ታላቅ አባት
ሲጠራ ስማቸው – ይሰማናል ኩራት
ማናቸው ንገሩኝ – አንባቢም ይሳተፍ
ፎቶቸውን አይቶ – ስማቸውን ይጻፍ
Adonay Bizuayehu Mamo says
እኝህ ሰው ማን ናቸው
እኔም አላውቃቸው
ዛሬ ነው ፌስቡክ ላይ
ከልብ ያየሁዋቸው
ባካችሁ ንገሩኝ
እኝህ ሰው ማን ናቸው ?
Sintayew Sharew says
ላገሩ ያለቀሰ
ብዕሩን ያደማ
ያደረሰ ቁንጮ
ጉዋድ በዓሉ ግርማ
Gebreyes Gebeyehu says
በ አገሩ ጀግና
የሃገሩ ወኔ
የነጻነት ታጋይ
በብዕሩ አማላይ
ከጻፉት የበላይ
ከመጻፉ ኦሮማይ
በአሉ ግርማ
መልስ ለ ቁ ፭ says
እኝህ መልከ መልካም መልከ ቀና ሰዉ
የአገር ጠበቃ ምሁርም ናቸዉ
በፋሽስት ጦርነት አገር ሲወረር
እኚህ መልካም ጎበዝ ተሟግተዉ ነበር
ተጥቁር ወንድሞች በአንድ በማበር
ጦርም አስተባብረዉ ሊልኩ ነበር
በፓን አፍሪካነት በመተባበር
ታሪካቸዉ ሸጋ ልክ እንደ መልካቸዉ
ስማቸዉም ይኸዉ መላኩ በያን ነዉ
dereje mengesha says
የሃገር ጠበቃ የታወቀው ምሁር
መላኩ በያን ነው ለማያቁት ንገር
ላገሩ ነጻነት ቆሞ ሲከራከር
አሜሪካን አገር ሆኖ የቀረው አፈር
ስሙ ግን ያልሞተ ያልገባ መቃብር
መላኩ በያን በል ወለላዬ አትፈር
Bombu says
እንደው በግርድፉ ፎቶውን ሲያሰሉት
የቆየ ይመሥላል ዘመን ያለፈበት
ደግሞ ሲያስተውሉ ግለስቡን ዘልቆ
አለባበሱንም ካዩ ተጠንቅቆ
ወጣት ከመሆኑም ዘና ከማለቱ
ኮፍያው ከራሱ ከረባት ባንገቱ
ሁሉንም አሥማምቶ የተነሳው ፎቶ
ዘመነኛነቱን ያሳያል አጉልቶ
በውጭ አገር ኖረው ያውቃሉ ለማለት
ነበር ሙከራዬ ይሕ ሁሉ መዋተት
ከዚህ በተረፈ የምስማማው እኔ
የመገምት አቅም ባይኖረኝም ወኔ
ቢሆኑ ደስ ይላል በያን ወመላኩ
እንደተጠቀሰው ከላይ በመድረኩ