• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውሃ የህይወትና የሞት ጉዳይ ነው”፤ መፍትሔ መፈለግ “የግድ” ነው፤ አል-ሲሲ

May 7, 2014 08:14 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ በግብጽ ለሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያሸንፋሉ እየተባለ የሚጠበቁት ዕጩ ተወዳዳሪ አብዱል ፈታህ አል-ሲሲ “የውሃ ነገር” ለግብጽ “የህይወትና የሞት ጉዳይ” ሲሉ ገለጹ፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን መፍትሔ መፈለጉ “የግድ” እንደሆነ አስታወቁ፡፡ በቅርቡ በግድቡ ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡ በውጭ የሚገኙ ሦስት ኢትዮጵያውያን ምሁራን የግድቡ መሠራት ግብጽን “በማይቀር አደጋ” ላይ እንደማይጥላት አስረዱ፡፡

በግብጽ በተላለፈ የቴቪ ስርጭት ትላንት ቃለመጠይቅ የሰጡት የቀድሞው የግብጽ ጦር መሪ ፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ ግድቡን አስመልክቶ ሰፊ ትንተና እንዳልሰጡ አልሃራም የቲቪ ስርጭቱን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ሆኖም ዕጩ ፕሬዚዳንታዊ ተወዳዳሪ “የሌሎችን ፍላጎትና ጥቅም የምንረዳ መሆናችንን ማሳየት ይገባናል፤ (የዚያኑ ያህልም) የራሳችንን ጥቅም ለማስጠበቅ ጽኑ መሆን አለብን፤ (ምክንያቱም) ውሃ ማለት ለእኛ የህይወትና የሞት ጉዳይ ነው” ብለዋል፡፡

አል-ሲሲ በአባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሊደረግ የሚገባው ንግግር ትኩረት ሳይሰጠው ለረጅም ጊዜ የቆየ መሆኑና ውይይቱም የተጀመረው ዘግይቶ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ “ለኢትዮጵያና ለሌሎች አፍሪካ ወንድሞቻችን ተገቢውን ጥረትsisi አለማድረጋችንን ማመን አለብን፤ በዚህ ዓይነቱ ጉዳይ ለመተባበርና መፍትሔ ለማግኘት ድርድርና የጋራ መግባባት ቁልፍ ናቸው” በማለት አል-ሲሲ የግብጽን ፍላጎት አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል በዚሁ የአባይ ግድብ ዙሪያ በቅርቡ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡና በውጭ የሚገኙ ሦስት ምሁራን የግድቡ መሠራት ግብጽን “የማይቀር አደጋ” ላይ እንደማይጥላት አስታውቀዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ፣ ፕሮፌሰር ሰይድ ሃሰንና ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ “Misplaced opposition to the Grand Ethiopian Renaissance Dam” በሚል ርዕስ ባቀረቡት በዚህ ጥናታዊ ጽሁፍ ላይ ታላላቅ ግድቦችን በተመለከተ የሚቀርቡ የተቃውሞ ሃሳቦች መኖራቸውን ዓለምአቀፋዊ መረጃዎችን በማጣቀስ ይተነትናሉ፡፡ ከእነዚህም ሃሳቦች መካከል ጥቂቶቹ የሕዝብ መፈናቀል፣ ሙስና፣ ከኮትራት ውሎች ጋር በተያያዘ ሊኖር የሚገባ ግልጽነት፣ የግንባታና የጥገና ወጪ፣ ወዘተ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በግድቡ ዙሪያ ያላቸውን ሕጋዊ ጥያቄ የማንሳትና የመጠየቅ መብት እንዳላቸው ምሁራኑ ያስረዳሉ፡፡

በመቀጠልም በቅርቡ ከዓለምአቀፍ የባለሙያዎች ፓናል አምልጦ የወጣ መረጃ በመጥቀስ ግድቡ ከኢኮኖሚ አንጻር መቀጠል የሚችል መሆኑን፣ ዲዛይኑ አንዳንድ መጠነኛ “ማስተካከያዎች” ሊደረግበት የሚገባ ቢሆንም ዓለምአቀፍ ደረጃን የጠበቀ መሆኑን፣ ሥራውን እያካሄደ ያለው ኮንትራክተር ታላላቅ ግድቦችን በመሥራት ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያለው መሆኑን፣ ወዘተ በመጥቀስ የግድቡ ሥራ በግብጽ ላይ መቅሰፍትን የሚያመጣ አለመሆኑን ኢትዮጵያውያኑ ምሁራን ባለ 48 ገጽ ምሥጢራዊ ሰነዱ በመጥቀስ ማጠቃለያ ሰጥተዋል፡፡ የግድቡ ሥራና መጠናቀቅ ግብጽን “የማይቀር አደጋ” ውስጥ እንደማይከታትም ሦስቱ ምሁራን ይናገራሉ፡፡abay and church

በ“ህዳሴው” ግድብ ዙሪያ በግብጽና ኢትዮጵያ መካከል ያለው መካረር ቀጥሎ ከጥቂት ቀናት በፊት ለሁለተኛ ጊዜ ግብጽን ለመጎብኘት ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበረው አቡነ ማቲያስ የግብጹ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ በላኩላቸው መልዕክት ምክንያት ጉብኝቱ መሠረዙን ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ዘግቦ ነበር፡፡ የግድቡ ጉዳይ ወደ ሃይማኖት መንደር መዝለቁ የሁኔታውን አሳሳቢነት የሚያሳይ መሆኑን ጎልጉል በወቅቱ የገለጸ ሲሆን በሥራው ላይ የሚገኙ መሃንዲስ ኢህአዴግ የአገር ሃብት የሆነውን ግድብ ሥራ ለራሱ ርካሽ የፖለቲካ መሣሪያነት መጠቀሙ አግባብ የሌለው መሆኑን መናገራቸውን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

ግብጽን በፕሬዚዳንትነት ይመራሉ እየተባለ የሚጠበቁት አል-ሲሲ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው የተባረሩትን ሙርሲን የሚተኩና የምዕራባውያን ከፍተኛ ድጋፍ ያላቸው “ሥዩመ-ፕሬዚዳንት” የመሆናቸው ጉዳይ የበርካታዎችን ትኩረት የሳበ ነው፡፡ ፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ የአባይን ግድብ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር መፍትሔ መፈለጉ “የግድ” እንደሆነ ቢጠቅሱም ውሃ ለግብጻውያን “የህይወትና የሞት ጉዳይ” ከመሆኑ አንጻር የግብጽን ጥቅም አስጠብቃለሁ ብለው መናገራቸው እንዴት ሊታረቅ እንደሚችል ወደፊት በሂደት የሚታይ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያና ግብጽ በአባይ ጉዳይ ገና ብዙ የሚቀራቸው መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule