• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውሃ የህይወትና የሞት ጉዳይ ነው”፤ መፍትሔ መፈለግ “የግድ” ነው፤ አል-ሲሲ

May 7, 2014 08:14 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ በግብጽ ለሚካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያሸንፋሉ እየተባለ የሚጠበቁት ዕጩ ተወዳዳሪ አብዱል ፈታህ አል-ሲሲ “የውሃ ነገር” ለግብጽ “የህይወትና የሞት ጉዳይ” ሲሉ ገለጹ፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር በመሆን መፍትሔ መፈለጉ “የግድ” እንደሆነ አስታወቁ፡፡ በቅርቡ በግድቡ ዙሪያ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡ በውጭ የሚገኙ ሦስት ኢትዮጵያውያን ምሁራን የግድቡ መሠራት ግብጽን “በማይቀር አደጋ” ላይ እንደማይጥላት አስረዱ፡፡

በግብጽ በተላለፈ የቴቪ ስርጭት ትላንት ቃለመጠይቅ የሰጡት የቀድሞው የግብጽ ጦር መሪ ፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ ግድቡን አስመልክቶ ሰፊ ትንተና እንዳልሰጡ አልሃራም የቲቪ ስርጭቱን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ሆኖም ዕጩ ፕሬዚዳንታዊ ተወዳዳሪ “የሌሎችን ፍላጎትና ጥቅም የምንረዳ መሆናችንን ማሳየት ይገባናል፤ (የዚያኑ ያህልም) የራሳችንን ጥቅም ለማስጠበቅ ጽኑ መሆን አለብን፤ (ምክንያቱም) ውሃ ማለት ለእኛ የህይወትና የሞት ጉዳይ ነው” ብለዋል፡፡

አል-ሲሲ በአባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሊደረግ የሚገባው ንግግር ትኩረት ሳይሰጠው ለረጅም ጊዜ የቆየ መሆኑና ውይይቱም የተጀመረው ዘግይቶ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ “ለኢትዮጵያና ለሌሎች አፍሪካ ወንድሞቻችን ተገቢውን ጥረትsisi አለማድረጋችንን ማመን አለብን፤ በዚህ ዓይነቱ ጉዳይ ለመተባበርና መፍትሔ ለማግኘት ድርድርና የጋራ መግባባት ቁልፍ ናቸው” በማለት አል-ሲሲ የግብጽን ፍላጎት አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል በዚሁ የአባይ ግድብ ዙሪያ በቅርቡ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡና በውጭ የሚገኙ ሦስት ምሁራን የግድቡ መሠራት ግብጽን “የማይቀር አደጋ” ላይ እንደማይጥላት አስታውቀዋል፡፡ ፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ፣ ፕሮፌሰር ሰይድ ሃሰንና ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ “Misplaced opposition to the Grand Ethiopian Renaissance Dam” በሚል ርዕስ ባቀረቡት በዚህ ጥናታዊ ጽሁፍ ላይ ታላላቅ ግድቦችን በተመለከተ የሚቀርቡ የተቃውሞ ሃሳቦች መኖራቸውን ዓለምአቀፋዊ መረጃዎችን በማጣቀስ ይተነትናሉ፡፡ ከእነዚህም ሃሳቦች መካከል ጥቂቶቹ የሕዝብ መፈናቀል፣ ሙስና፣ ከኮትራት ውሎች ጋር በተያያዘ ሊኖር የሚገባ ግልጽነት፣ የግንባታና የጥገና ወጪ፣ ወዘተ ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በግድቡ ዙሪያ ያላቸውን ሕጋዊ ጥያቄ የማንሳትና የመጠየቅ መብት እንዳላቸው ምሁራኑ ያስረዳሉ፡፡

በመቀጠልም በቅርቡ ከዓለምአቀፍ የባለሙያዎች ፓናል አምልጦ የወጣ መረጃ በመጥቀስ ግድቡ ከኢኮኖሚ አንጻር መቀጠል የሚችል መሆኑን፣ ዲዛይኑ አንዳንድ መጠነኛ “ማስተካከያዎች” ሊደረግበት የሚገባ ቢሆንም ዓለምአቀፍ ደረጃን የጠበቀ መሆኑን፣ ሥራውን እያካሄደ ያለው ኮንትራክተር ታላላቅ ግድቦችን በመሥራት ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያለው መሆኑን፣ ወዘተ በመጥቀስ የግድቡ ሥራ በግብጽ ላይ መቅሰፍትን የሚያመጣ አለመሆኑን ኢትዮጵያውያኑ ምሁራን ባለ 48 ገጽ ምሥጢራዊ ሰነዱ በመጥቀስ ማጠቃለያ ሰጥተዋል፡፡ የግድቡ ሥራና መጠናቀቅ ግብጽን “የማይቀር አደጋ” ውስጥ እንደማይከታትም ሦስቱ ምሁራን ይናገራሉ፡፡abay and church

በ“ህዳሴው” ግድብ ዙሪያ በግብጽና ኢትዮጵያ መካከል ያለው መካረር ቀጥሎ ከጥቂት ቀናት በፊት ለሁለተኛ ጊዜ ግብጽን ለመጎብኘት ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበረው አቡነ ማቲያስ የግብጹ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ በላኩላቸው መልዕክት ምክንያት ጉብኝቱ መሠረዙን ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ዘግቦ ነበር፡፡ የግድቡ ጉዳይ ወደ ሃይማኖት መንደር መዝለቁ የሁኔታውን አሳሳቢነት የሚያሳይ መሆኑን ጎልጉል በወቅቱ የገለጸ ሲሆን በሥራው ላይ የሚገኙ መሃንዲስ ኢህአዴግ የአገር ሃብት የሆነውን ግድብ ሥራ ለራሱ ርካሽ የፖለቲካ መሣሪያነት መጠቀሙ አግባብ የሌለው መሆኑን መናገራቸውን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

ግብጽን በፕሬዚዳንትነት ይመራሉ እየተባለ የሚጠበቁት አል-ሲሲ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው የተባረሩትን ሙርሲን የሚተኩና የምዕራባውያን ከፍተኛ ድጋፍ ያላቸው “ሥዩመ-ፕሬዚዳንት” የመሆናቸው ጉዳይ የበርካታዎችን ትኩረት የሳበ ነው፡፡ ፊልድ ማርሻል አል-ሲሲ የአባይን ግድብ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ጋር መፍትሔ መፈለጉ “የግድ” እንደሆነ ቢጠቅሱም ውሃ ለግብጻውያን “የህይወትና የሞት ጉዳይ” ከመሆኑ አንጻር የግብጽን ጥቅም አስጠብቃለሁ ብለው መናገራቸው እንዴት ሊታረቅ እንደሚችል ወደፊት በሂደት የሚታይ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያና ግብጽ በአባይ ጉዳይ ገና ብዙ የሚቀራቸው መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule