• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጸጥታ አስከባሪው” ህወሃት/ኢህአዴግ ጸጥታው ሊገመገም ነው

August 10, 2016 08:08 am by Editor 1 Comment

ከዚህ በፊት ሆኖ የማያውቅ በሚመስል ሁኔታ ኢትዮጵያ በህወሃት/ኢህአዴግ ዘመን ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያገኘች አስመስሎ የሚያወራው ህወሃት “ጸጥታ አስከባሪ ነኝ” እያለ በአፍሪካ ሳይጠሩት አለሁ የሚለውን ያህል አሁን ደግሞ በተራው በአገር ውስጥ ህዝብን ጸጥታ በመንሳት ሊገመገም መሆኑ ተነገረ፡፡ “በኢትዮጵያ ሰላም ለማስከበር በሚል የህወሃት ጄኔራሎች የተባበሩት መንግሥታትን ምደባ እየጠየቁ ነው” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክርቤት ድምጽ የማትሰጥ አባል ሆና መመረጧ የህዳሴው ውጤት ነው፤ የመለስ ራዕይ ተግባራዊነት ነው፤ … በማለት ከፍተኛ ዲስኩር የነፋው፤ ከበሮ የደለቀው ህወሃት “ህዝብን ጸጥታ ነስተሃል” ተብሎ በተባበሩት መንግሥታት የምርመራ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ በንጉሡ ዘመን እንዲሁም በደርግ ጊዜ የጸጥታው ም/ቤት አባል በመሆን ማገልገሏ እንዳይነገር ብዙ ፕሮፓጋንዳ የሠራው ህወሃት የጸጥታው ምክርቤት የአባልነት ዘመኑ በ2017 ከመጀመሩ በፊት ይህ የገጠመው ችግር ያልታሰበ ዱብዕዳ ሆኖበታል፡፡ በመጪዎቹ የአውሮጳውያን ዓመት በጸጥታው ም/ቤት ወንበር ላይ ተቀምጦ በኤርትራና በሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ከማዕቀብ ጀምሮ ያሻውን ዓይነት ውሳኔ እንዲተላለፍ ዝግጅት ያደረገው ህወሃት/ኢህአዴግ የተመኘውን ወንበር በፎቶ እንዳየው በዚያው ሊቀር እንደሚችል አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ ethiopia-security-council

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሆኑት ዘዒድ ራድ አል ሁሴን ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው ለሬውተርስ በሰጡት መግለጫ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣው ህዝብ ላይ ጥይት መተኮሱና 90 ሰልፈኞችን መግደሉ መረጃዎች ደርሰውናል ብለዋል፡፡ ይህንን ለማረጋገጥም ምርመራ ማድረግ የግድ እንደሆነ አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩን የጠቀሰው የዜናው ዘገባ “የኢትዮጵያ መንግሥት ታዛቢዎች ምርመራ እንዲያደርጉ መፍቀድ አለበት” ብሏል፡፡

በሰላም ሰልፍ የወጡና የታሰሩ በሙሉ መለቀቅ አለባቸው ያሉት ኮሚሽነር ዘዒድ መርማሪዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ሄደው ምርመራቸውን ማካሄድ እንዲችሉ ከህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ጋር ንግግር መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡

ከኢሳያስ አፈወርቅ ተቃዋሚዎች ጋር በማበር የተባበሩት መንግሥታት ልዩ ራፖርተር ዘገባ እንዲወጣና ኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ጉድጓድ ሲቆፍር የነበረው ህወሃት የራሱን መቀበሪያ ራሱ ቆፍሯል በማለት አስተያየት ሰጪ ለጎልጉል ተናግረዋል፡፡ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በተደጋጋሚ በበቂ ማስረጃ ገዳይነቱን የመሰከሩለት ህወሃት/ኢህአዴግ፤ በዚህ የተባበሩት መንግሥታት ምርመራ ወንጀለኛ ሆኖ እንደሚገኝ ጥርጥር እንደሌላቸው በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ይናገራሉ፡፡

በአፍሪካ የተለያዩ አገራት የሰላም አስጠባቂ በመሆን ባልተጠራበት ሁሉ ወታደር እየላከ “ሰላም አስከባሪ ነኝ” ሲል የኖረው ህወሃት ሰላመ-ቢስ ብቻ ሳይሆን ጸጥታ አደፍራሽ መሆኑ ይፋ የሚደረግበት ጊዜ ላይ ነን የሚሉ ወገኖች ህወሃት የሻዕቢያን መቀበሪያ ሲያዘጋጅ ራሱ ሊቀበርበት ነው ብለዋል፡፡

የኮሚሽኑ ዘገባ ይፋ በሚሆንበት ጊዜ ሰላማዊ ሰዎችን በመግደልና በማስገደል እጃቸው ያለበትን ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዘገባው በማስረጃ ሰነድነት እንዲያዝ ከማድረግ ባለፈ ጥፋተኞቹን ለፍርድ የሚቀርቡበትንም አካሄድ ያመቻቻል፡፡

ያለ ዕውቀታቸውና ያለ ወታደራዊ ብቃታቸው ለሥራ ማመልከቻ እንዲረዳቸው የጄኔራልነት ሹመት የተጎናጸፉት የህወሃት ወታደራዊ ሹሞችና የቀድሞ የጦር ኃላፊዎች በሌላ የአፍሪካ አገር እንደለመዱት “በኢትዮጵያ ሰላም የለም፤ ጸጥታ ደፍርሷል፤ … የኢትዮጵያን ጸጥታ እናስከብራለን” በማለት የቅጥር ማመልከቻ እያቀረቡና ምደባ እየጠየቁ ይሆናል ሲሉ የህወሃትን ጠባብነትና ጭፍንነት የሚያውቁ ስላቃዊ አስተያየት ይሰጣሉ፡፡

ከዕውቀት ጋር ጠበኛ የሆነውና በተለይ የቁጥር ስሌት ሰለባ የሆነው ህወሃት በቁጥጥሩ ሥር ባደረገው ሚዲያ በአማራና በኦሮሞ ከተሞች የወጡትን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩትን ሰላማዊ ሰልፈኞች “ጥቂት ጸረ ሰላም ኃይሎች” ብሎ በመሰየም ተቃውሞውን በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ማለቱ ለግድያው ራሱ ኃላፊነት ስለመውሰዱ ምስክርነት የሰጠበት ሆኖ ለኮሚሽኑ እንደ ቀዳሚ ግብዓት እንደሚወሰድ ታውቋል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽኑ ምርመራውን እንዲደርግና በህወሃት ሹሞች እንዳይታለል በተለይ በዳያስፖራ ያለው ኢትዮጵያዊ በኮሚሽኑ ላይ ግፊት እንዲያደርግ ተጠይቋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfaye amenu says

    August 19, 2016 12:18 am at 12:18 am

    Des yemell tarke new

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule