• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጸጥታ አስከባሪው” ህወሃት/ኢህአዴግ ጸጥታው ሊገመገም ነው

August 10, 2016 08:08 am by Editor 1 Comment

ከዚህ በፊት ሆኖ የማያውቅ በሚመስል ሁኔታ ኢትዮጵያ በህወሃት/ኢህአዴግ ዘመን ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያገኘች አስመስሎ የሚያወራው ህወሃት “ጸጥታ አስከባሪ ነኝ” እያለ በአፍሪካ ሳይጠሩት አለሁ የሚለውን ያህል አሁን ደግሞ በተራው በአገር ውስጥ ህዝብን ጸጥታ በመንሳት ሊገመገም መሆኑ ተነገረ፡፡ “በኢትዮጵያ ሰላም ለማስከበር በሚል የህወሃት ጄኔራሎች የተባበሩት መንግሥታትን ምደባ እየጠየቁ ነው” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክርቤት ድምጽ የማትሰጥ አባል ሆና መመረጧ የህዳሴው ውጤት ነው፤ የመለስ ራዕይ ተግባራዊነት ነው፤ … በማለት ከፍተኛ ዲስኩር የነፋው፤ ከበሮ የደለቀው ህወሃት “ህዝብን ጸጥታ ነስተሃል” ተብሎ በተባበሩት መንግሥታት የምርመራ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ በንጉሡ ዘመን እንዲሁም በደርግ ጊዜ የጸጥታው ም/ቤት አባል በመሆን ማገልገሏ እንዳይነገር ብዙ ፕሮፓጋንዳ የሠራው ህወሃት የጸጥታው ምክርቤት የአባልነት ዘመኑ በ2017 ከመጀመሩ በፊት ይህ የገጠመው ችግር ያልታሰበ ዱብዕዳ ሆኖበታል፡፡ በመጪዎቹ የአውሮጳውያን ዓመት በጸጥታው ም/ቤት ወንበር ላይ ተቀምጦ በኤርትራና በሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ከማዕቀብ ጀምሮ ያሻውን ዓይነት ውሳኔ እንዲተላለፍ ዝግጅት ያደረገው ህወሃት/ኢህአዴግ የተመኘውን ወንበር በፎቶ እንዳየው በዚያው ሊቀር እንደሚችል አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ ethiopia-security-council

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሆኑት ዘዒድ ራድ አል ሁሴን ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው ለሬውተርስ በሰጡት መግለጫ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣው ህዝብ ላይ ጥይት መተኮሱና 90 ሰልፈኞችን መግደሉ መረጃዎች ደርሰውናል ብለዋል፡፡ ይህንን ለማረጋገጥም ምርመራ ማድረግ የግድ እንደሆነ አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩን የጠቀሰው የዜናው ዘገባ “የኢትዮጵያ መንግሥት ታዛቢዎች ምርመራ እንዲያደርጉ መፍቀድ አለበት” ብሏል፡፡

በሰላም ሰልፍ የወጡና የታሰሩ በሙሉ መለቀቅ አለባቸው ያሉት ኮሚሽነር ዘዒድ መርማሪዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ሄደው ምርመራቸውን ማካሄድ እንዲችሉ ከህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ጋር ንግግር መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡

ከኢሳያስ አፈወርቅ ተቃዋሚዎች ጋር በማበር የተባበሩት መንግሥታት ልዩ ራፖርተር ዘገባ እንዲወጣና ኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ጉድጓድ ሲቆፍር የነበረው ህወሃት የራሱን መቀበሪያ ራሱ ቆፍሯል በማለት አስተያየት ሰጪ ለጎልጉል ተናግረዋል፡፡ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በተደጋጋሚ በበቂ ማስረጃ ገዳይነቱን የመሰከሩለት ህወሃት/ኢህአዴግ፤ በዚህ የተባበሩት መንግሥታት ምርመራ ወንጀለኛ ሆኖ እንደሚገኝ ጥርጥር እንደሌላቸው በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ይናገራሉ፡፡

በአፍሪካ የተለያዩ አገራት የሰላም አስጠባቂ በመሆን ባልተጠራበት ሁሉ ወታደር እየላከ “ሰላም አስከባሪ ነኝ” ሲል የኖረው ህወሃት ሰላመ-ቢስ ብቻ ሳይሆን ጸጥታ አደፍራሽ መሆኑ ይፋ የሚደረግበት ጊዜ ላይ ነን የሚሉ ወገኖች ህወሃት የሻዕቢያን መቀበሪያ ሲያዘጋጅ ራሱ ሊቀበርበት ነው ብለዋል፡፡

የኮሚሽኑ ዘገባ ይፋ በሚሆንበት ጊዜ ሰላማዊ ሰዎችን በመግደልና በማስገደል እጃቸው ያለበትን ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዘገባው በማስረጃ ሰነድነት እንዲያዝ ከማድረግ ባለፈ ጥፋተኞቹን ለፍርድ የሚቀርቡበትንም አካሄድ ያመቻቻል፡፡

ያለ ዕውቀታቸውና ያለ ወታደራዊ ብቃታቸው ለሥራ ማመልከቻ እንዲረዳቸው የጄኔራልነት ሹመት የተጎናጸፉት የህወሃት ወታደራዊ ሹሞችና የቀድሞ የጦር ኃላፊዎች በሌላ የአፍሪካ አገር እንደለመዱት “በኢትዮጵያ ሰላም የለም፤ ጸጥታ ደፍርሷል፤ … የኢትዮጵያን ጸጥታ እናስከብራለን” በማለት የቅጥር ማመልከቻ እያቀረቡና ምደባ እየጠየቁ ይሆናል ሲሉ የህወሃትን ጠባብነትና ጭፍንነት የሚያውቁ ስላቃዊ አስተያየት ይሰጣሉ፡፡

ከዕውቀት ጋር ጠበኛ የሆነውና በተለይ የቁጥር ስሌት ሰለባ የሆነው ህወሃት በቁጥጥሩ ሥር ባደረገው ሚዲያ በአማራና በኦሮሞ ከተሞች የወጡትን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩትን ሰላማዊ ሰልፈኞች “ጥቂት ጸረ ሰላም ኃይሎች” ብሎ በመሰየም ተቃውሞውን በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ማለቱ ለግድያው ራሱ ኃላፊነት ስለመውሰዱ ምስክርነት የሰጠበት ሆኖ ለኮሚሽኑ እንደ ቀዳሚ ግብዓት እንደሚወሰድ ታውቋል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽኑ ምርመራውን እንዲደርግና በህወሃት ሹሞች እንዳይታለል በተለይ በዳያስፖራ ያለው ኢትዮጵያዊ በኮሚሽኑ ላይ ግፊት እንዲያደርግ ተጠይቋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfaye amenu says

    August 19, 2016 12:18 am at 12:18 am

    Des yemell tarke new

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule