• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጸጥታ አስከባሪው” ህወሃት/ኢህአዴግ ጸጥታው ሊገመገም ነው

August 10, 2016 08:08 am by Editor 1 Comment

ከዚህ በፊት ሆኖ የማያውቅ በሚመስል ሁኔታ ኢትዮጵያ በህወሃት/ኢህአዴግ ዘመን ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያገኘች አስመስሎ የሚያወራው ህወሃት “ጸጥታ አስከባሪ ነኝ” እያለ በአፍሪካ ሳይጠሩት አለሁ የሚለውን ያህል አሁን ደግሞ በተራው በአገር ውስጥ ህዝብን ጸጥታ በመንሳት ሊገመገም መሆኑ ተነገረ፡፡ “በኢትዮጵያ ሰላም ለማስከበር በሚል የህወሃት ጄኔራሎች የተባበሩት መንግሥታትን ምደባ እየጠየቁ ነው” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክርቤት ድምጽ የማትሰጥ አባል ሆና መመረጧ የህዳሴው ውጤት ነው፤ የመለስ ራዕይ ተግባራዊነት ነው፤ … በማለት ከፍተኛ ዲስኩር የነፋው፤ ከበሮ የደለቀው ህወሃት “ህዝብን ጸጥታ ነስተሃል” ተብሎ በተባበሩት መንግሥታት የምርመራ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ በንጉሡ ዘመን እንዲሁም በደርግ ጊዜ የጸጥታው ም/ቤት አባል በመሆን ማገልገሏ እንዳይነገር ብዙ ፕሮፓጋንዳ የሠራው ህወሃት የጸጥታው ምክርቤት የአባልነት ዘመኑ በ2017 ከመጀመሩ በፊት ይህ የገጠመው ችግር ያልታሰበ ዱብዕዳ ሆኖበታል፡፡ በመጪዎቹ የአውሮጳውያን ዓመት በጸጥታው ም/ቤት ወንበር ላይ ተቀምጦ በኤርትራና በሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ከማዕቀብ ጀምሮ ያሻውን ዓይነት ውሳኔ እንዲተላለፍ ዝግጅት ያደረገው ህወሃት/ኢህአዴግ የተመኘውን ወንበር በፎቶ እንዳየው በዚያው ሊቀር እንደሚችል አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ ethiopia-security-council

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሆኑት ዘዒድ ራድ አል ሁሴን ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው ለሬውተርስ በሰጡት መግለጫ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣው ህዝብ ላይ ጥይት መተኮሱና 90 ሰልፈኞችን መግደሉ መረጃዎች ደርሰውናል ብለዋል፡፡ ይህንን ለማረጋገጥም ምርመራ ማድረግ የግድ እንደሆነ አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩን የጠቀሰው የዜናው ዘገባ “የኢትዮጵያ መንግሥት ታዛቢዎች ምርመራ እንዲያደርጉ መፍቀድ አለበት” ብሏል፡፡

በሰላም ሰልፍ የወጡና የታሰሩ በሙሉ መለቀቅ አለባቸው ያሉት ኮሚሽነር ዘዒድ መርማሪዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ሄደው ምርመራቸውን ማካሄድ እንዲችሉ ከህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ጋር ንግግር መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡

ከኢሳያስ አፈወርቅ ተቃዋሚዎች ጋር በማበር የተባበሩት መንግሥታት ልዩ ራፖርተር ዘገባ እንዲወጣና ኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ጉድጓድ ሲቆፍር የነበረው ህወሃት የራሱን መቀበሪያ ራሱ ቆፍሯል በማለት አስተያየት ሰጪ ለጎልጉል ተናግረዋል፡፡ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በተደጋጋሚ በበቂ ማስረጃ ገዳይነቱን የመሰከሩለት ህወሃት/ኢህአዴግ፤ በዚህ የተባበሩት መንግሥታት ምርመራ ወንጀለኛ ሆኖ እንደሚገኝ ጥርጥር እንደሌላቸው በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ይናገራሉ፡፡

በአፍሪካ የተለያዩ አገራት የሰላም አስጠባቂ በመሆን ባልተጠራበት ሁሉ ወታደር እየላከ “ሰላም አስከባሪ ነኝ” ሲል የኖረው ህወሃት ሰላመ-ቢስ ብቻ ሳይሆን ጸጥታ አደፍራሽ መሆኑ ይፋ የሚደረግበት ጊዜ ላይ ነን የሚሉ ወገኖች ህወሃት የሻዕቢያን መቀበሪያ ሲያዘጋጅ ራሱ ሊቀበርበት ነው ብለዋል፡፡

የኮሚሽኑ ዘገባ ይፋ በሚሆንበት ጊዜ ሰላማዊ ሰዎችን በመግደልና በማስገደል እጃቸው ያለበትን ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዘገባው በማስረጃ ሰነድነት እንዲያዝ ከማድረግ ባለፈ ጥፋተኞቹን ለፍርድ የሚቀርቡበትንም አካሄድ ያመቻቻል፡፡

ያለ ዕውቀታቸውና ያለ ወታደራዊ ብቃታቸው ለሥራ ማመልከቻ እንዲረዳቸው የጄኔራልነት ሹመት የተጎናጸፉት የህወሃት ወታደራዊ ሹሞችና የቀድሞ የጦር ኃላፊዎች በሌላ የአፍሪካ አገር እንደለመዱት “በኢትዮጵያ ሰላም የለም፤ ጸጥታ ደፍርሷል፤ … የኢትዮጵያን ጸጥታ እናስከብራለን” በማለት የቅጥር ማመልከቻ እያቀረቡና ምደባ እየጠየቁ ይሆናል ሲሉ የህወሃትን ጠባብነትና ጭፍንነት የሚያውቁ ስላቃዊ አስተያየት ይሰጣሉ፡፡

ከዕውቀት ጋር ጠበኛ የሆነውና በተለይ የቁጥር ስሌት ሰለባ የሆነው ህወሃት በቁጥጥሩ ሥር ባደረገው ሚዲያ በአማራና በኦሮሞ ከተሞች የወጡትን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩትን ሰላማዊ ሰልፈኞች “ጥቂት ጸረ ሰላም ኃይሎች” ብሎ በመሰየም ተቃውሞውን በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ማለቱ ለግድያው ራሱ ኃላፊነት ስለመውሰዱ ምስክርነት የሰጠበት ሆኖ ለኮሚሽኑ እንደ ቀዳሚ ግብዓት እንደሚወሰድ ታውቋል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽኑ ምርመራውን እንዲደርግና በህወሃት ሹሞች እንዳይታለል በተለይ በዳያስፖራ ያለው ኢትዮጵያዊ በኮሚሽኑ ላይ ግፊት እንዲያደርግ ተጠይቋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfaye amenu says

    August 19, 2016 12:18 am at 12:18 am

    Des yemell tarke new

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule