• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሽንፋን በአራት አቅጣጫ ከብቦ ጦርነት የከፈተው ትህነግ እርምጃ እየተወሰደበት ነው

September 1, 2021 03:31 pm by Editor 1 Comment

ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም አሸባሪው እና ተስፋፊው የትህነግ ቡድን በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ በተካሄደው የሕግ ማስከበር እርምጃ የተረፈው የጠላት ጦር የሸሸው ምዕራብ ጎንደርን በሚያዋስነው የሱዳን ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ነበር፡፡ ከሕግ ማስከበር እርምጃው በኋላ ላለፉት 10 ወራት በአካባቢው ጥቃት ለመሰንዘር ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርጉም በስፍራው ባለው የወገን ጦር እየተመታ ተመልሷል፡፡

ዛሬ ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የጠላት ጦር ሽንፋን በአራት አቅጣጫ በኩል በመክበብ ጦርነት ከፍቶ ነበር ያሉት የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ጣሰው በሁሉም ግንባሮች በአካባቢው የጥምር ጦር አባላት ተገቢው እርምጃ ተወስዶበታል ብለዋል፡፡

በጦርነቱ የጠላትን ጦር በማገዝ እና በመምራት የአሸባሪው እና ተስፋፊው የትህነግ ቡድን ሌላኛው ሴል (ህዋስ) የሆነው ጽንፈኛው የቅማንት ታጣቂ ቡድን አባላት እንዳሉበት የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይል፣ ሚሊሻ፣ ፋኖ እና የአካባቢው ወጣቶች በተደራጀ ሁኔታ ምላሽ እየሰጡ ነው ብለዋል፡፡

ውስን የሆኑት ጽንፈኛ የቅማንት ታጣቂ ቡድን አባላት በርካታውን እና ሰላማዊውን የቅማንት ሕዝብ እንደማይዎክሉ የገለጹት አቶ ደሳለኝ በጦርነቱ ውስጥ የወገን ጦር በመቀላቀል እየተዋጉ ላሉ እና መረጃ በመስጠት ለሚተባበሩ የቅማንት ማኅበረሰብ አባላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

“በቲሃ በኩል ሽንፋን እና ቱመትን” ተከትሎ በአራት አቅጣጫ ከመጣው የጠላት ኀይል በሦስቱ አቅጣጫ የመጣው ቡድን ተደምስሶ ምርኮኛ እና ምርኮ እየተሰበሰበ ነው ተብሏል፡፡ በአንድ አቅጣጫ ይህ ዘገባ በሚጠናቀርበት ጊዜም ውጊያ ላይ ሲሆን ጦርነቱ በቅርብ ስዓት ሙሉ በሙሉ በድል ይጠናቀቃል ነው ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፡፡

ዋና አስተዳዳሪው በመልዕክታቸው በዚህ አውደ ውጊያ ወጣቶች እና የአካባቢው ማኅበረሰብ መንግሥት በዘረጋው የጸጥታ መዋቅር ውስጥ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ወጣቶችና የአካባቢው ማኅበረሰብም በምርኮ የሚያገኙትን ማንኛውንም መሳሪያ ለአካባቢው የጸጥታ መዋቅር እያሳወቁ እንዲታጠቁ ተፈቅዷል ብለዋል፡፡

(አማራ ኮሚዩኒኬሽን ) አሚኮ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. ሥርጉተ ሥላሴ says

    September 3, 2021 02:48 am at 2:48 am

    አመሰግናለሁ። ሼር አድርጌዋለሁ።

    Reply

Leave a Reply to ሥርጉተ ሥላሴ Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule