• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ እየተበረበረ ነው

December 28, 2012 09:57 am by Editor 2 Comments

“አዲሱ ቴሌ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ/ኢንሳ” በሚል ርዕስ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ያዘጋጀው ጥናታዊ ሪፖርት የታላላቅ አገር የስለላ ተቋማት፣ ለጉዳዩ አግባብ ያላቸው መምሪያዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ትኩረት መሳቡ ታወቀ። ሪፖርቱን አገራቱ በራሳቸው ቋንቋ በመተርጎም የህወሃት/ኢህአዴግን የስለላ መረብ ከተለያየ አቅጣጫ እየመረመሩት ነው።

የጎልጉል ምንጭ የሆኑ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንዳስታወቁት አኢጋን የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ) ጋር በማጋባት ስለላው በምን ዓይነት መልኩ እንደሚካሄድ በማመልከት ይፋ ያደረገው ባለ 47 ገጽ ሰነድ የተጠቀሱትን ክፍሎች ቀልብ የሳበው ዘገባው በወጣ ማግስት ነበር።

ሪፖርቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ የሪፖርቱ ባለቤት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዘገባውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር ሰነዱን የሚጠቀሙ አካሎች እውቅና እንዲሰጡት ተጠይቆ እንደነበር ያስታወሱት የመረጃው ምንጭ፣ አኢጋን ተከታታይ ሪፖርቶችን የማዘጋጀት እቅድ እንዳለውና መረጃው በዋናነት ለኢትዮጵያዊ ወገኖች እንዲደርስ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ለጊዜው የትርጉም ስራው ላይ ትኩረት እንደማያደርግ መግለጹን ተናግረዋል። ይሁንና አኢጋን ሪፖርቱን መጠቀም ለሚፈልጉና ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን በገለጸው መሰረት ሪፖርቱ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ለመተርጎም በቅቷል።

ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ እና ሌሎች የአውሮጳ መንግሥታ ሪፖርቱን ለራሳቸው ለመተርጎም ቅድሚያውን የያዙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ካላቸው አገሮች መካከል ዋና የሚባሉት አስቀድሞ ከሚያደርጉት ጥንቃቄ በበለጠ ከስላለው መረብ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቁ የማስጠንቀቂያ መመሪያ ከተላለፈላቸው ሰነባብቷል።

የደህንነቱን ስራ ከቴሌ ጋር በማገናኘት የተካኑትን የቻይና የቴሌኮም ኩባንያዎች በማስገባትና የአውሮፓን የቴሌኮም ተቋማትን “ወግዱ” በማለት ህወሃት/ኢህአዴግ እንዲሰናበቱ ማድረጉ ዋና ርዳታ ሰጪ አገሮችን ቅር አሰኝቷል። ከዚህም በላይ ከቴሌኮም ንግዱ ጎን ለጎን አገራቱን ከመረጃና ከአጋርነት ማግለሉ የፈጠረው ቅሬታ ቀን ጠብቆ የህወሃት/ኢህአዴግን አመራር ዋጋ እንደሚያስከፍለው የመረጃው ባለቤት ጨምረው ገልጸዋል።

የዓለም ታላላቅ አገሮችን ቀልብ የሳበውና ከፍተኛ መረጃዎችን የያዘው ሪፖርት በአገር ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥተው በሚሰሩ የኅትመት፣ የድረገጽ፣ የድምጽና ምስል መገናኛዎች ሰፊ ሽፋን አለማግኘቱ የሪፖርቱን ባለቤት ብቻ ሳይሆን በትርጉሙ ላይ የተሳተፉትን አገራት የመረጃ ሰዎችን ያስገረመ ጉዳይ እንደነበር፣ ይሁንና በቅርቡ ሪፖርቱ ህይወት ዘርቶ በሁሉም ወገን እንደ ሰነድ የሚወሰድ እንደሚሆን የንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በላከው የኢሜይል መልዕክት ተናግሯል። በመልዕክቱ ስማቸውን መዘርዘር ባያስፈልግም የተለያዩ የስለላ ድርጅቶችና አገሮች ሪፖርቱ በእንግሊዝኛ ተዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ክፍሉ ገልጾዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) አኢጋን ያወጣውን ሪፖርት ተከትሎ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት እለት ድረስ መቃወሚያም ሆነ ማስተባበያ አላቀረበም። ኢንሳ በቻይና የቴሌኮም ኩባንያ ዜድቲኢ አማካይነት የዜጎችን እንቅስቃሴ ወደ መረጃ ቋት ውስጥ በማስገባት የሚያካሂደው ስለላ፣ በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ላይ እንዲሁም ኤምባሲዎች ላይ የሚያካሂደው ክትትልና በንጹሃን ላይ በሚፈጽመው አፈና በቅርቡ ይፋ የሚወጣ ከየአቅጣጫው ተቃውሞ ሊቀርብበት እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አመልክተዋል።

ኢህአዴግ በደቡብ ሱዳን የሚያካሂደውን ጣልቃ ገብነትና ጥቅምን የመጋራት “ወረራ” እና የህወሃት ወገን የሆኑ ነጋዴዎች በጁባ ስለሚያካሂዱት ስለላ አኢጋን በዝርዝር አቀርበዋለሁ ያለውን ተጨማሪ መረጃ አስመልክቶ በጥልቀት እየሰራበት መሆኑን ለጎልጉል አስታውቋል። መረጃውን መቼና እንዴት በምን ዓይነት መልኩ ይፋ እንደሚያደርግ ግን ቀን ቀጥሮ አላስታወቀም።


ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ሕዝብ ግንኙነት ባገኘው ፈቃድ መሠረት “አዲሱ ቴሌና ኢንሳ፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ” በሚል ርዕስ የወጣውን ዘገባ ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡ አኢጋን በዘገባው ላይ በግልጽ እንዳስቀመጠው ጽሁፉን “ለማስተማሪነት፣ የቅስቀሳ ዘመቻ ለማካሄድ፣ ለጥናትና ምርምር እንደ ምንጭ በመጥቀስ ያለ ምንም ክፍያ መጠቀም ይቻላል፡፡”

“አዲሱ ቴሌ”
እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት
ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ከሚያካሂዳቸው በርካታ ተግባራት በተጨማሪ ላለፉት ወራት የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ያካሄደውንና ሊያካሂድ ያሰበውን የስለላ ተግባር ሲመረምር ቆይቷል፡፡ በተለይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ ጋር በማጋባት ስለላውን በምን ዓይነት መልኩ ለማካሄድ እንዳሰበ የሚያትት ባለ 47 ገጽ ግርድፍ ዘገባ አቅርበናል፡፡

“አዲሱ ቴሌ” እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ መረጃ በኢትዮጵያችን የተካሄደውንና በመካሄድ ላይ ያለውን የአፈና መዋቅር በጥቂቱ የሚያወሳ ነው። ዘገባው የህወሃት/ኢህአዴግ የደኅንነትና የአፈና ተቋማት ከቴሌኮም አገልግሎት ጋር እንዴትና ለምን እንደተቆራኙ፣ የምዕራብ አገራት የቴሌኮም ቴክኖሎጂ የተገፋበትን ምስጢር፣ አዲሱን ቴሌ ከአገር ወዳዶች በማጽዳት የህወሃት/ኢህአዴግን ፖለቲካና ስውር አጀንዳ ማስፈጸም ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው ክፍሎች ወይም የአገዛዙ “ቁሶች” እንዲዛወር የተደረገበትን ምክንያት፣ በፖለቲካ ድርጅቶችንና ኃላፊዎች እንዲሁም መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) ላይ የሚካሄደውን ስለላ በመጠኑ ለማሳየት ጥረት ተደርጓል፡፡

በመጨረሻም ይህንን የስለላ መረብ በመጣስ ሕዝባችን ትግሉን በምን ዓይነት መልኩ ማከናወን እንዳለበትና እንዴት የመረጃ ጫካ ውስጥ በመግባት መደበቅ እንደሚቻል የተወሰኑ ሃሳቦችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

ዘገባውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዘገባውን በWord ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Ethio Telecom, Full Width Top, INSA, Middle Column, NISS

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    December 29, 2012 02:05 pm at 2:05 pm

    The home grown fascists do whatever means possible to prolong their reign of terror. The solution is to unite and get rid of these fascists who castrate the Ethiopian people. Say no to woyane ethnic fascism and ethnic cleansing. http://vimeo.com/18242221 Amharas being castrated by the fascists and this is not only a problem of one ethnic group and all peace loving people should say no to this barbaric deeds.

    Reply
  2. AbdLillah says

    March 20, 2013 07:25 am at 7:25 am

    The information age faster than controllable, if woyane succeeded will be a miracle because Egypt was the main ethernet communication connection center in Africa and Middle East so may Mubarek missing something here? If Arab spring brought down the rich leaders in the Arab world our nation with empty banknotes can save themself the extremist fanatic TPLF regime? I doubt.!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule