• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ እየተበረበረ ነው

December 28, 2012 09:57 am by Editor 2 Comments

“አዲሱ ቴሌ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ/ኢንሳ” በሚል ርዕስ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ያዘጋጀው ጥናታዊ ሪፖርት የታላላቅ አገር የስለላ ተቋማት፣ ለጉዳዩ አግባብ ያላቸው መምሪያዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ትኩረት መሳቡ ታወቀ። ሪፖርቱን አገራቱ በራሳቸው ቋንቋ በመተርጎም የህወሃት/ኢህአዴግን የስለላ መረብ ከተለያየ አቅጣጫ እየመረመሩት ነው።

የጎልጉል ምንጭ የሆኑ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንዳስታወቁት አኢጋን የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ) ጋር በማጋባት ስለላው በምን ዓይነት መልኩ እንደሚካሄድ በማመልከት ይፋ ያደረገው ባለ 47 ገጽ ሰነድ የተጠቀሱትን ክፍሎች ቀልብ የሳበው ዘገባው በወጣ ማግስት ነበር።

ሪፖርቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ የሪፖርቱ ባለቤት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዘገባውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር ሰነዱን የሚጠቀሙ አካሎች እውቅና እንዲሰጡት ተጠይቆ እንደነበር ያስታወሱት የመረጃው ምንጭ፣ አኢጋን ተከታታይ ሪፖርቶችን የማዘጋጀት እቅድ እንዳለውና መረጃው በዋናነት ለኢትዮጵያዊ ወገኖች እንዲደርስ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ለጊዜው የትርጉም ስራው ላይ ትኩረት እንደማያደርግ መግለጹን ተናግረዋል። ይሁንና አኢጋን ሪፖርቱን መጠቀም ለሚፈልጉና ተጨማሪ መረጃ ለሚፈልጉ ለመተባበር ዝግጁ መሆኑን በገለጸው መሰረት ሪፖርቱ ወደ ተለያዩ ቋንቋዎች ለመተርጎም በቅቷል።

ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ እና ሌሎች የአውሮጳ መንግሥታ ሪፖርቱን ለራሳቸው ለመተርጎም ቅድሚያውን የያዙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ካላቸው አገሮች መካከል ዋና የሚባሉት አስቀድሞ ከሚያደርጉት ጥንቃቄ በበለጠ ከስላለው መረብ ወጥመድ ውስጥ እንዳይወድቁ የማስጠንቀቂያ መመሪያ ከተላለፈላቸው ሰነባብቷል።

የደህንነቱን ስራ ከቴሌ ጋር በማገናኘት የተካኑትን የቻይና የቴሌኮም ኩባንያዎች በማስገባትና የአውሮፓን የቴሌኮም ተቋማትን “ወግዱ” በማለት ህወሃት/ኢህአዴግ እንዲሰናበቱ ማድረጉ ዋና ርዳታ ሰጪ አገሮችን ቅር አሰኝቷል። ከዚህም በላይ ከቴሌኮም ንግዱ ጎን ለጎን አገራቱን ከመረጃና ከአጋርነት ማግለሉ የፈጠረው ቅሬታ ቀን ጠብቆ የህወሃት/ኢህአዴግን አመራር ዋጋ እንደሚያስከፍለው የመረጃው ባለቤት ጨምረው ገልጸዋል።

የዓለም ታላላቅ አገሮችን ቀልብ የሳበውና ከፍተኛ መረጃዎችን የያዘው ሪፖርት በአገር ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥተው በሚሰሩ የኅትመት፣ የድረገጽ፣ የድምጽና ምስል መገናኛዎች ሰፊ ሽፋን አለማግኘቱ የሪፖርቱን ባለቤት ብቻ ሳይሆን በትርጉሙ ላይ የተሳተፉትን አገራት የመረጃ ሰዎችን ያስገረመ ጉዳይ እንደነበር፣ ይሁንና በቅርቡ ሪፖርቱ ህይወት ዘርቶ በሁሉም ወገን እንደ ሰነድ የሚወሰድ እንደሚሆን የንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በላከው የኢሜይል መልዕክት ተናግሯል። በመልዕክቱ ስማቸውን መዘርዘር ባያስፈልግም የተለያዩ የስለላ ድርጅቶችና አገሮች ሪፖርቱ በእንግሊዝኛ ተዘጋጅቶ እንዲሰጣቸው ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ክፍሉ ገልጾዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) አኢጋን ያወጣውን ሪፖርት ተከትሎ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት እለት ድረስ መቃወሚያም ሆነ ማስተባበያ አላቀረበም። ኢንሳ በቻይና የቴሌኮም ኩባንያ ዜድቲኢ አማካይነት የዜጎችን እንቅስቃሴ ወደ መረጃ ቋት ውስጥ በማስገባት የሚያካሂደው ስለላ፣ በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አመራሮች ላይ እንዲሁም ኤምባሲዎች ላይ የሚያካሂደው ክትትልና በንጹሃን ላይ በሚፈጽመው አፈና በቅርቡ ይፋ የሚወጣ ከየአቅጣጫው ተቃውሞ ሊቀርብበት እንደሚችል ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አመልክተዋል።

ኢህአዴግ በደቡብ ሱዳን የሚያካሂደውን ጣልቃ ገብነትና ጥቅምን የመጋራት “ወረራ” እና የህወሃት ወገን የሆኑ ነጋዴዎች በጁባ ስለሚያካሂዱት ስለላ አኢጋን በዝርዝር አቀርበዋለሁ ያለውን ተጨማሪ መረጃ አስመልክቶ በጥልቀት እየሰራበት መሆኑን ለጎልጉል አስታውቋል። መረጃውን መቼና እንዴት በምን ዓይነት መልኩ ይፋ እንደሚያደርግ ግን ቀን ቀጥሮ አላስታወቀም።


ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ሕዝብ ግንኙነት ባገኘው ፈቃድ መሠረት “አዲሱ ቴሌና ኢንሳ፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ” በሚል ርዕስ የወጣውን ዘገባ ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡ አኢጋን በዘገባው ላይ በግልጽ እንዳስቀመጠው ጽሁፉን “ለማስተማሪነት፣ የቅስቀሳ ዘመቻ ለማካሄድ፣ ለጥናትና ምርምር እንደ ምንጭ በመጥቀስ ያለ ምንም ክፍያ መጠቀም ይቻላል፡፡”

“አዲሱ ቴሌ”
እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት
ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡

የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ከሚያካሂዳቸው በርካታ ተግባራት በተጨማሪ ላለፉት ወራት የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ያካሄደውንና ሊያካሂድ ያሰበውን የስለላ ተግባር ሲመረምር ቆይቷል፡፡ በተለይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አዲሱ ቴሌን (ኢትዮ ቴሌኮምን) ከዋንኛው የስለላ መ/ቤት ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል NISS (National Intelligence and Security Service) እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ወይም በእንግሊዝኛው (Information Network Security Agency (INSA) – ኢንሳ ጋር በማጋባት ስለላውን በምን ዓይነት መልኩ ለማካሄድ እንዳሰበ የሚያትት ባለ 47 ገጽ ግርድፍ ዘገባ አቅርበናል፡፡

“አዲሱ ቴሌ” እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ)፡ የህወሃት/ኢህአዴግ የስለላ መረብ በሚል ርዕስ የቀረበው ይህ መረጃ በኢትዮጵያችን የተካሄደውንና በመካሄድ ላይ ያለውን የአፈና መዋቅር በጥቂቱ የሚያወሳ ነው። ዘገባው የህወሃት/ኢህአዴግ የደኅንነትና የአፈና ተቋማት ከቴሌኮም አገልግሎት ጋር እንዴትና ለምን እንደተቆራኙ፣ የምዕራብ አገራት የቴሌኮም ቴክኖሎጂ የተገፋበትን ምስጢር፣ አዲሱን ቴሌ ከአገር ወዳዶች በማጽዳት የህወሃት/ኢህአዴግን ፖለቲካና ስውር አጀንዳ ማስፈጸም ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው ክፍሎች ወይም የአገዛዙ “ቁሶች” እንዲዛወር የተደረገበትን ምክንያት፣ በፖለቲካ ድርጅቶችንና ኃላፊዎች እንዲሁም መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) ላይ የሚካሄደውን ስለላ በመጠኑ ለማሳየት ጥረት ተደርጓል፡፡

በመጨረሻም ይህንን የስለላ መረብ በመጣስ ሕዝባችን ትግሉን በምን ዓይነት መልኩ ማከናወን እንዳለበትና እንዴት የመረጃ ጫካ ውስጥ በመግባት መደበቅ እንደሚቻል የተወሰኑ ሃሳቦችን ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡

ዘገባውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዘገባውን በWord ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Ethio Telecom, Full Width Top, INSA, Middle Column, NISS

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    December 29, 2012 02:05 pm at 2:05 pm

    The home grown fascists do whatever means possible to prolong their reign of terror. The solution is to unite and get rid of these fascists who castrate the Ethiopian people. Say no to woyane ethnic fascism and ethnic cleansing. http://vimeo.com/18242221 Amharas being castrated by the fascists and this is not only a problem of one ethnic group and all peace loving people should say no to this barbaric deeds.

    Reply
  2. AbdLillah says

    March 20, 2013 07:25 am at 7:25 am

    The information age faster than controllable, if woyane succeeded will be a miracle because Egypt was the main ethernet communication connection center in Africa and Middle East so may Mubarek missing something here? If Arab spring brought down the rich leaders in the Arab world our nation with empty banknotes can save themself the extremist fanatic TPLF regime? I doubt.!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule