• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የደቡበ ክልል ሦስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ከኃላፊነት ተነሱ

September 4, 2013 07:29 pm by Editor Leave a Comment

የደቡብ ክልልን ከሚመሩት አራቱ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች መካከል ሦስቱ ከኃላፊነት መነሳታቸውን ምንጮች ገለጹ፡፡

ለሦስቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መነሳት ከነሐሴ 15 እስከ 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ከተደረገው ግምገማ ጋር የተያያዘ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮች፣ ለእያንዳንዳቸው መነሳት የተለያዩ ምክንያቶች መኖራቸውን ያስረዳሉ፡፡ ከኃላፊነታቸው ከተነሱት መካከል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ከሆኑ አንድ ዓመት ያልሞላቸው አቶ ታገሠ ጫፎ ሲሆኑ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አሰፋና በተመሳሳይ ማዕረግ  የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳኒ ረዲ ናቸው፡፡

የአቶ አለማየሁ አሰፋና የአቶ ታገሠ ጫፎ መነሳት የተጠበቀና ውስጥ ለውስጥ ሲነገር የቆየ መሆኑን፣ ያልተጠበቀው ግን የአቶ ሳኒ ረዲ ነበር በማለት አስተያየት የሰጡት የደኢሕዴን አባልና ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ አንድ የክልሉ ባለሥልጣን፣ ሦስቱም ሹማምንት የተገመገሙት በተለያዩ ችግሮች እንደሆነ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡ ‹‹አቶ ታገሠ በአመራር ብቃት ማነስ በተደጋጋሚ ይተቹ እንደነበር ገልጸው፣ አቶ አለማየሁና አቶ ሳኒ ደግሞ አላስፈላጊ ‹‹ኔትወርክ›› በመፍጠር ብልሹ አሠራር በማስፈናቸው ነው፤›› ብለዋል፡፡

በግምገማው የተሳተፉ ምንጮች ደግሞ በተለይ አቶ አለማየሁ ባለፈው ዓመት መጨረሻ አካባቢ በተወከሉበት ዳውሮ ዞን ከፍተኛ ተቃውሞ ሲነሳባቸው የኃይል ዕርምጃ እንዲወሰድ ማድረጋቸው እንደ አንድ ምክንያት መነሳቱን ያስረዳሉ፡፡

በሌላ በኩል የክልሉ የመንግሥት ሠራተኛ የሆኑ አንዳንድ አስተያት ሰጪዎች ለሦስቱም ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከኃላፊነት መነሳት የአመራር ብቃት ማነስ ብቻ ሳይሆን የኪራይ ሰብሳቢነትና የሙስና ችግሮች መኖራቸውን ይገልጻሉ፡፡

በሥነ ሕይወት ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዓሣ ዕርባታ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ያገኙት አቶ ታገሠ ጫፎ እስከ 2000 ዓ.ም. ድረስ የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር፣ ከ2000 እስከ 2003 ዓ.ም. መስከረም ድረስ ብቸኛው የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የንግድ ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ፣ እንዲሁም ወደ ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊነት እስከተዛወሩበት ህዳር 2005 ዓ.ም. ድረስ አራተኛው ምክትል ርዕስ መስተዳድር ሆነው ቆይተዋል፡፡ ከአምስት ዓመት በላይ በኃላፊነት የቆዩበት ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ አንዳንድ ሠራተኞች፣ ‹‹ከአራት መቶ በላይ ሠራተኞች ያሉበትን ቢሮ ሲመሩ አንድም ቀን ሠራተኞችን ሰብስበው አናግረው ችግር የፈቱበት ጊዜ አልነበረም፡፡  ግንኙታቸው ከሥራ ሒደት ባለቤቶች ጋር ስለነበር ዕርምጃም የሚወስዱት ከነዚያ ሰዎች በሚያገኙት መረጃ ብቻ ነበር፤›› በማለት በርካታ ሠራተኞች ሳያውቁዋቸው እሳቸውም የሚያስተዳድሩዋቸውን ሠራተኞች በቅጡ ሳያውቁ መነሳሳታቸውን ይናገራሉ፡፡

እስከ መስከረም 2003 ዓ.ም. ድረስ የደኢሕዴን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመሆን የክልሉን የፖለቲካ እንቅሰቃሴን ሲመሩ የቆዩትና ከዚያ በኋላ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ የነበሩት አቶ አለማየሁ አሰፋ፣ ‹‹ሜትሮ ፖሊታን›› የተሰኘውንና የሐዋሳ ከተማ አስተዳዳር 70/30 (ሰባ በመቶ ብሔር ብሔረሰቦች ተዋፅኦ፣ ሰላሳ በመቶ በሲዳማ ተወላጆች እንዲዋቀር) ባለፈው ሚያዚያ 2004 ዓ.ም. አዘጋጅተው ለውይይት ያቀረቡት መመርያ በተለይ በሲዳማ ተወላጆች ዘንድ ከፍተኛ ትችት እንዳስከተለባቸው ይታወሳል፡፡ ያም ብቻ ሳይሆን ከሲዳማ አርነት ንቅናቄ አፈትልኮ የወጣውን ያንን መመርያ የዞኑ ሕዝብ ዘንድ በመድረሱ በወቅቱ ከፍተኛ ውጥረት ተፈጥሮ ነበር፡፡ በቅርቡ የትምህርት ሚኒስትር የሆኑት የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የማረጋጊያ መግለጫ መስጠታቸው የሚታወስ ነው፡፡

አቶ አለማየሁ አሰፋና አቶ ሳኒ ረዲ ከሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባለፈው ሐምሌ 2005 ዓ.ም. ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሥራ አመራር ሁለተኛ ዲግሪ አግኝተው የተመረቁ ሲሆን፣ በአመራር ብቃት ማነስ ስለመገምገማቸው የተሰጠ አስተያየት የለም፡፡

ሦስቱም ከኃላፊነት የተነሱት ምክትል ርዕሰ መስተዳደሮች ለሰላሳ ስድስቱ የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ከተዋጡት ዘጠኝ አባላት ውስጥ የሚገኙ ቢሆንም፣ ኢሕአዴግ በዚህ ዓመት መጀመሪያ ባህር ዳር ከተማ ባደረገው ጉባዔ አቶ ታገሠ ጫፎና አቶ ደበበ አበራ በመተካካት መርህ መነሳታቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ታገሠ ከንግድ ኢንዱስትሪ ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊነት ለወራት ብቻ ወደ መሩት ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ የተዛወሩት ከባህር ዳር ጉባዔ በኋላ መሆኑ አይዘነጋም፡፡

ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው የተነገረላቸው እነዚህ ሦስቱ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች የካቢኔ አባላትም እንደሚኖሩበት ምንጮች ለሪፖርተር የገለጹ ሲሆን፣ በምትካቸው የሚሾሙትን ተተኪዎች አዲሱ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደሴ ዳልኬ በመጪው መስከረም 2006 ዓ.ም. በሚደረገው ጉባዔ ላይ ይፋ በማድረግ በምክር ቤቱ እንደሚያፀድቁ  ይጠበቃል፡፡  (ምንጭ፤ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule