• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዎላይታ አመራሮች “ከህወሃትና ኦነግ ሸኔ አካላት ጋር በድብቅ ስብሰባ ያረጉ ነበር”

August 11, 2020 05:56 am by Editor 2 Comments

የዎላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኮምቤን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ከትላንት በስቲያ በመከላከያ ሠራዊት መያዛቸው ተሰምቷል።

እሁድ አመሻሹን የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊዎች ለደቡብ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ የዎላይታ ዞን አመራሮች በዞኑ ኮማንድ ፖስት ዛሬ ከሰዓት መያዛቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አለማየሁ ባውዲ እንዳሉት የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች የተለያዩ ህገወጥ አደረጃጀቶችን ፈጥረው ግጭት የመቀስቀስ ፍላጎታቸውን እንዲያስፈጽሙ እያደረጉ ነበር ብለዋል። 

አመራሮቹ በፓርቲ ደረጃ እንዲሁም በግለሰብ ደረጃ ሀገር ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመስራት ላይ ይገኛሉም ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ አለማየሁ ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ በማለት ከገለጿቸው ህወኃትና ኦነግ ሸኔ አካላት ጋር በድብቅ ሰው እየላኩ ስብሰባ እንደሚያደርጉ እና ተልዕኮ እንደሚቀበሉ ተናግረዋል። ለዚህም ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት መረጃዎች ተገኝተዋል ብለዋል።

የኮማንድ ፖስቱ ትዕዛዝ በመተላለፍ ህገወጥ ስብሰባዎች እንዲሁም ሰልፎችን እንዳደረጉ ተገልጿል። ህብረተሰቡ የሰጡትን አመራር ቢቀበላቸው አካባቢው ግጭቶች ይፈጠሩ እንደነበር አቶ አለማየሁ ተናግረዋል።

አቶ አለማየሁ ከሕገ መንግሥት ውጭ በመንቀሳቀስ ክልሉን የግጭት ቀጠና ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን ገልፀው ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም በእኩይ ድርጊታቸው መቀጠሉን ምረጣቸውን አብራርተዋል። 

የዞኑ ህዝብ የአመራሩን የጥፋት ተልዕኮ ሳይቀበል መቆየቱን በመጥቀስ ሃላፊው ለህዝቡ ምስጋና አቅርበዋል። በአሁኑ ወቅት ዞኑ በተረጋጋ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ህዝቡ የሰላም እሴቱን እንዲያስቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።

በዛሬው ዕለት (ዕሁድ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋሉት አመራሮችን ጨምሮ 26 ግለሰቦች መሆናቸውን አል አይን ዘግቧል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ትናንት የዎላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ተከትሎ በሶዶ ከተማ የተከሰተው አለመረጋጋት ዛሬም ጠዋት አንዳንድ ቦታዎች ቀጥሎ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰዓት ከተማዋ አንጻራዊ ሰላም መኖሩን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በወላይታ ዞን በአሁን ሰዓት ብጥብጥ አስነስታችኋል የተባሉ ሰዎች በመከላክያ ኃይል በቁጥጥር ሥር እየዋሉ እንደሆነና እስካሁን በተነሳው ግርግር ስንት ሰው እንደተጎዳ የታወቀ ነገር የለም ትላንት ምሽት ግን አንድ ሰው ሲሞት 14 መቁሰላቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ወላይታ ሶዶ ከተማ ሙሉ በሙሉ አለመረጋጋቷን ማረጋገጥ ችለናል። አሁንም አልፎ አልፎ የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አሳውቀዋል።

በዛሬው ዕለት (ሰኞ) ሁለት (2) ሰዎች መሞታቸውን ከአሶሼትድ ፕሬስ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል። ሌሎች ግን የሟቾች ቁጥር ከ20 በላይ ነው ይላሉ።

በተጨማሪም ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ የንግድ እንዲሁም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አለመኖሩን የቲክቫህ ኢትዮ አባላት አሳውቀዋል።

ከወላይታ ሶዶ ከተማ ወደ ተለያዩ ወረዳዎች የሚደረግ ጉዞ ተቋርጧል/የለም። አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊትና የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል በከተማ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

(ከተለያዩ መደበኛና የማኅበራዊ ድረገጾች የተጠናቀረ ዘገባ ነው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News

Reader Interactions

Comments

  1. Tazabiw-sew says

    August 20, 2020 06:55 pm at 6:55 pm

    ” በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አለማየሁ ባውዲ . . . ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ በማለት ከገለጿቸው ህወኃትና ኦነግ ሸኔ አካላት ጋር በድብቅ ሰው እየላኩ ስብሰባ እንደሚያደርጉ እና ተልዕኮ እንደሚቀበሉ ተናግረዋል። ለዚህም ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት መረጃዎች ተገኝተዋል ብለዋል”

    የጎልኡል አርታኢ ከላይ እንደተጠቀሰው ይንን ያሉት ዓለማየሁ ባውዲ ናቸው፤ ነገር ግን ይጎልጉል “ዜና” አርዕስት መሆኑ ለምን ይሆን? በጥቅስ ምልክት ቢቀመጥም! እንግዲህ የማትወጡት አዳላጭ ዳገት ላይ ስለሆናችሁ ሸርተት በሉና ተደመሩ፤ በልጥጉ፤ ድሮም ካለኛ የለም የዜና ዘላን ነበራችሁ፤ አሁን ጥሩ የመደመር ግጦሽ መሬት ተግኝቷል

    ታዛቢ

    Reply
    • Editor says

      August 31, 2020 03:57 pm at 3:57 pm

      That is what we did.

      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule