• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዎላይታ አመራሮች “ከህወሃትና ኦነግ ሸኔ አካላት ጋር በድብቅ ስብሰባ ያረጉ ነበር”

August 11, 2020 05:56 am by Editor 2 Comments

የዎላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኮምቤን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ከትላንት በስቲያ በመከላከያ ሠራዊት መያዛቸው ተሰምቷል።

እሁድ አመሻሹን የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እና የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊዎች ለደቡብ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ የዎላይታ ዞን አመራሮች በዞኑ ኮማንድ ፖስት ዛሬ ከሰዓት መያዛቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አለማየሁ ባውዲ እንዳሉት የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች የተለያዩ ህገወጥ አደረጃጀቶችን ፈጥረው ግጭት የመቀስቀስ ፍላጎታቸውን እንዲያስፈጽሙ እያደረጉ ነበር ብለዋል። 

አመራሮቹ በፓርቲ ደረጃ እንዲሁም በግለሰብ ደረጃ ሀገር ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ተቀናጅተው በመስራት ላይ ይገኛሉም ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ አለማየሁ ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ በማለት ከገለጿቸው ህወኃትና ኦነግ ሸኔ አካላት ጋር በድብቅ ሰው እየላኩ ስብሰባ እንደሚያደርጉ እና ተልዕኮ እንደሚቀበሉ ተናግረዋል። ለዚህም ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት መረጃዎች ተገኝተዋል ብለዋል።

የኮማንድ ፖስቱ ትዕዛዝ በመተላለፍ ህገወጥ ስብሰባዎች እንዲሁም ሰልፎችን እንዳደረጉ ተገልጿል። ህብረተሰቡ የሰጡትን አመራር ቢቀበላቸው አካባቢው ግጭቶች ይፈጠሩ እንደነበር አቶ አለማየሁ ተናግረዋል።

አቶ አለማየሁ ከሕገ መንግሥት ውጭ በመንቀሳቀስ ክልሉን የግጭት ቀጠና ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን ገልፀው ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ በተደጋጋሚ ቢነገራቸውም በእኩይ ድርጊታቸው መቀጠሉን ምረጣቸውን አብራርተዋል። 

የዞኑ ህዝብ የአመራሩን የጥፋት ተልዕኮ ሳይቀበል መቆየቱን በመጥቀስ ሃላፊው ለህዝቡ ምስጋና አቅርበዋል። በአሁኑ ወቅት ዞኑ በተረጋጋ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ህዝቡ የሰላም እሴቱን እንዲያስቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።

በዛሬው ዕለት (ዕሁድ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋሉት አመራሮችን ጨምሮ 26 ግለሰቦች መሆናቸውን አል አይን ዘግቧል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ትናንት የዎላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ተከትሎ በሶዶ ከተማ የተከሰተው አለመረጋጋት ዛሬም ጠዋት አንዳንድ ቦታዎች ቀጥሎ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰዓት ከተማዋ አንጻራዊ ሰላም መኖሩን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በወላይታ ዞን በአሁን ሰዓት ብጥብጥ አስነስታችኋል የተባሉ ሰዎች በመከላክያ ኃይል በቁጥጥር ሥር እየዋሉ እንደሆነና እስካሁን በተነሳው ግርግር ስንት ሰው እንደተጎዳ የታወቀ ነገር የለም ትላንት ምሽት ግን አንድ ሰው ሲሞት 14 መቁሰላቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ወላይታ ሶዶ ከተማ ሙሉ በሙሉ አለመረጋጋቷን ማረጋገጥ ችለናል። አሁንም አልፎ አልፎ የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አሳውቀዋል።

በዛሬው ዕለት (ሰኞ) ሁለት (2) ሰዎች መሞታቸውን ከአሶሼትድ ፕሬስ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል። ሌሎች ግን የሟቾች ቁጥር ከ20 በላይ ነው ይላሉ።

በተጨማሪም ዛሬ በወላይታ ሶዶ ከተማ የንግድ እንዲሁም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አለመኖሩን የቲክቫህ ኢትዮ አባላት አሳውቀዋል።

ከወላይታ ሶዶ ከተማ ወደ ተለያዩ ወረዳዎች የሚደረግ ጉዞ ተቋርጧል/የለም። አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊትና የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል በከተማ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

(ከተለያዩ መደበኛና የማኅበራዊ ድረገጾች የተጠናቀረ ዘገባ ነው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News

Reader Interactions

Comments

  1. Tazabiw-sew says

    August 20, 2020 06:55 pm at 6:55 pm

    ” በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አለማየሁ ባውዲ . . . ሀገር ለማፍረስ የሚሰሩ በማለት ከገለጿቸው ህወኃትና ኦነግ ሸኔ አካላት ጋር በድብቅ ሰው እየላኩ ስብሰባ እንደሚያደርጉ እና ተልዕኮ እንደሚቀበሉ ተናግረዋል። ለዚህም ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት መረጃዎች ተገኝተዋል ብለዋል”

    የጎልኡል አርታኢ ከላይ እንደተጠቀሰው ይንን ያሉት ዓለማየሁ ባውዲ ናቸው፤ ነገር ግን ይጎልጉል “ዜና” አርዕስት መሆኑ ለምን ይሆን? በጥቅስ ምልክት ቢቀመጥም! እንግዲህ የማትወጡት አዳላጭ ዳገት ላይ ስለሆናችሁ ሸርተት በሉና ተደመሩ፤ በልጥጉ፤ ድሮም ካለኛ የለም የዜና ዘላን ነበራችሁ፤ አሁን ጥሩ የመደመር ግጦሽ መሬት ተግኝቷል

    ታዛቢ

    Reply
    • Editor says

      August 31, 2020 03:57 pm at 3:57 pm

      That is what we did.

      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule