• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስኳር ነገር!

May 25, 2016 11:54 pm by Editor Leave a Comment

እንዴት ስነበታችሁ? ስሞኑን በሀገራችን ዙሪያ ከሰማናቸው አስደማሚ ነገሮች አንዱ የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሸን ጉዳይ ነው:: ለዚህም ነው ይህን አጭር ጽሁፍ መሳይ ነገር – የስኳር ነገር ብዬ መስየሜ:: እንግዲህ እንደሰማነው የሰኴር ኮርፖሬሸን ከመከላክያ ብረታ ብረት ኢንጅነሪንግ (ሜቴክ) ጋር በመሳለጥ 77 ቢሊዮን ብር (3. 8 ቢሊዬን የአሜሪካን ዶላር) እንደሰለቀጡ ነው የኦዲት ቢሮም፣ ባለስልጣናቱም ጀባ ያሉን:: በስራ አጋጣሚ ከኮርፖሬሽኑ እና ከሜቴክ ጋር በነበረኝ ግንኝነት ስለ ጉዳዩ የማውቀውን ያህል ለማካፈል እየሞከርኩ ነው:: ከዚህ ጥረቴ አንዱ በቅርቡ በሜይ  23, 2016  በኢሳት አምስተርዳም ስቱዲዮ እንወያይ በሚለው ፕሮግራም ላይ ተካፍዬ ነበር። የዚህ ጽሁፍ አላማም በውውይቱ የጠቀሰኳቸውን ጉዳዬች በተጨማሪም በሰአት ጥበት ምክንያት አልተጠቀሱም ብዬ ያሰብኳቸውን ጉዳዬች ለመዳስስ ነው።

እንግዲህ በህወሐት ጐራ ላለፉት ስድስት (ሰባት) አመታት በትልቁ ሲጐሰሙ ከነበሩ ትላልቅ (ሜጋ) ፕሮጅክቶች የስኳር ኰርፖሬሽን ዋንኛው ነው። በተጨባጭ መረጃዎች መሰረት በላዪም የመንግስት ቱባ ባለስልጣናት እንዳመኑት የስኳር ነገር “ወፍ የለም” እንደሚሉት ከሆነ ከራርሞአል፡፡ አይደለም ሰባት አዳዲስ የስኳር ፋብሪካዎች ይቅርና  የነበሩትን “ማስፋፊያ ፕሮጀክት” ብለው ነካክተው ምስቅልቅሉን አውጥተውታል፡፡ “ጥድቁ ቀርቶ በቅጡ በተኰነንኵ” እንዲሉ::

ላለፉት ስባት እና ስድስት አመታት እከሌ የሚባለው ኘሮጀክት ይህን ያህል ተጠናቋል፤ ያኛዉ ደግሞ በሚቀጥለው አመት ማምረት ይጀምርና ይህን ያህል ሚሊዬን ኩንታል ስኳር ወደ ዉጭ አገራት እንልካለን፤ እና የመሳሰሉትን የመግለጫ ጋጋታዎች ለሕዝቡ በስኳር ኰርፖሬሽን እና በሜቴክ የተጋቱ እንደ ስኳር ነጭ የሆኑ ዉሸቶች ናቸዉ። ለምን ይዋሻል? እንጠይቃለን። እስከመቼስ? በዉሸት እንዲህ ያሰከሩንስ ምን ሆኑ? ለዚህ ሁሉ ዉሸት ሐላፊነት ማን ወሰደ? አሁንም እንጠይቃለን። መልስ እስኪገኝ።

ባከነ የተባለዉ ገንዘብስ? 77 ቢሊዬን ብር (3.8 ቢሊዬን ዶላር)። ባከነ የሚለዉ ቃል ለእኔ ብዙ አይመስጠኝም። አማረኛ ማሳመሩን ትተን እዉነቱን በግልፅ አማርኛ መተንፈስ ነው የሚያዋጣው። ስለዚህ ተዘረፈ። ተሰረቀ። ነው የሚባለው። ሜቴክ በስኳር ኳርፖሬሽን ኘሮጀክቶች ስም ከኢትዬጵያ ሕዝብ ላይ ብሎም በሕዝብ ስም የተገኘውን የብድር ብር ዘረፈው ብንል እውነታውን በተሻለ መልኩ ይገለፃል። እንደ እኔ አሁን አማርኛ የምናጣፍጥበት ወቅት ላይ አይደለንም። 20 ሚሊዬን ሕዝብ ተርቦ የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለተረጂ ወገኖቻችን የ 1.5 ቢሊዬን ዶላር ያለህ እያለ ሲጮህ፣ ሜቴክ ደግሞ 3.8 ቢሊዬን ዶላር ላፍ አድርጐ አየሁሽ አላየሁሽ እያለ ሲያፌዝብን የምን አማርኛ ማሳመር ነዉ? ምንስ ሊበጀን?

በግሌም ከኮርፖሬሽኑ ጋር ለመስራት የተስማሙ የውጭ ኩባንያዎችን በመወከል እሰራ ስለነበር የዘረፋውን ሒደት ለመታዘብ ችያአለሁ። የውጭ ኩባንያዎችን ወክዬ ከኮርፖሬሽኑ ጋር የተወሰኑትን ፕሮጀክቶች ለመውሰድ ስደራደር፣ ሜቴክ ከኋላ “ቀይዋን ያየ” በሚመስል ጨዋታ ስኳር ኮርፖሬሽን ሆኖ ብቅ አለ። ለካስ ኮርፖሬሽኑ ለስሙ ነው እንጂ ሙሉ በሙሉ በሜቴክ ቁጥጥር ስር ነው። ድርድሩንም፣ ብሩንም ወደ እኔ አለን ሜቴክ በወታደራዊ ቀጭን ትእዛዝ። ያው ወታደሮች አይደል የሚመሩት ወዴት እንደሆነ ባይታወቅም። የሜቴክ ሐላፊዎች የድፍረታቸው ድፍረት ገንዘቡን ብቻ ሳይሆን፣ በብድር ከሚገኘው ገንዘብ ላይ ኢንተረስት ሬትን ለመቀሸብ ሳይቀር ይደራደራሉ!? ወይ ድፍረት! አጃኢብ የሚያሰኝ ነው። በነገራችን ላይ ይህ ብድር በኢትዬጵያ ሕዝብ ስም እና በኢትዬጵያ ሶቨሪን ጋራንቲ (ዋስትና) የሚገኝ ነው። የማላስቸግራችሁ ከሆነ እና በግሌ ከሜቴክ ጋር የገባሁበትን እሰጥ እገባ ወይም ውዝግብ ለማወቅ ከፈለጋችሁ ከኢሳት ጋር ባደረኩት ውይይት በዚህ ማስፈንጠሪያ መኰምከም ይቻላል።

ጐበዝ ይኼ የሙስና ጉዳይ ብቻ አይደለም። በሙስና በሚታሙ አገሮች ሰርቼአለሁ። በእነዚህ አገራት ሌላው ቢቀር ሙስናው እንዴት እንደተከወነ ማየት የሚቻልበት መዋቅር (structure) አለ። በኢትዬጵያ ሁኔታ ይኸ ፈፅሞ አይታይም። ዘረፋው እጅግ አስፈሪ እና አደገኛ ነው። ሕወሐት አገሪቱን በኢኮኖሚ ሴክተሮች በመከፋፈል በምርቃና ፕሮጀክቶች ስም ሰቅዞ ያለማቋረጥ እየዘረፈ እና እየሰረቀ ነው። ስለዚህ ወይ ጉድ!? ወይ ሜቴክ? ወይ ስኳር ኮርፓሬሽን? እያልን በመደመም እንደ ተከታታይ ፊልም የምናየው የሙስና ጉዳይ ብቻ አይደለም። ኢትዬጵያ በዝርፊያ እየተናጠች ነው። የዝርፊያው መጠን እና አካሔድ እንደ አገር የመዝለቃችንን ነገር ፈተና ውስጥ ያስገባ ውስብስብ ቀውስ ነው።

ዳሩ ለውጥ አይቀሬ ነው። እንዲያው በዘገየ ቁጥር ለለዋጩ ሐይል አዲስ ጉልበት ሲጨምር፣ ለተለዋጩ ግን ወደ ማይወጡት ማጥ ውስጥ መነከር ነው። እንዲህ በአገር ላይ እያፌዙ መቀጠል ከቶ አይዘልቅም፣ አያዛልቅም። ለዘራፊዎች ግን አንድ ነገር ልበል። በቅርቡ አቶ አሰፋ ጨቦ “የትዝታ ፈለግ” የሚለውን መጽሐፍቸውን አስመልክተው አንድ ቃለ-መጠይቅ ሲሰጡ የተናገሩት ገጠመኝ ትዝ አለኝ። ደርግ ወድቆ ህወሐት አዲስ አበባን በተቆጣጠረበት ወቅት ነው አሉ። አዲስ አበባ ቀውጢ ሆናለች። እሳቸውም ከእስር የተፈቱበት ሰሞን ነው። እናም የጓደኛቸውን መኪና ይዘው ለመንዳት በአካባቢው ያገኙትን ሰው ቤንዚን የት ማግኘት እንደሚችሉ ይጠይቃሉ። ሰውየውም የት ማግኘት እንደሚችሉ ጠቁሟቸው፣ አንድ ነገር ግን ጠየቃቸው “ለመሆኑ ቤንዚኑን ቀድተህ መኪናውን የት ልትነዳው ነው በዚህ በቀውጢ ጊዜ?” እኔም ኢትዬጵያን እየዘረፉ ያሉትን ዘራፊ ባለስልጣናት ተመሳሳይ ጥያቄ ልጠይቅ። ለመሆኑ ይኼን ሁሉ ዘርፋችሁ የት እና መቼ ልትበሉት ነው?? ሊበላ?! አለች አሉ።

አገራችንን ፈጣሪ ይባርክ።

ወንድማአገኝ እጅጉ። ከ-ስቶኰልም፤ ስዊድን


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule