• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስኳር ነገር!

May 25, 2016 11:54 pm by Editor Leave a Comment

እንዴት ስነበታችሁ? ስሞኑን በሀገራችን ዙሪያ ከሰማናቸው አስደማሚ ነገሮች አንዱ የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሸን ጉዳይ ነው:: ለዚህም ነው ይህን አጭር ጽሁፍ መሳይ ነገር – የስኳር ነገር ብዬ መስየሜ:: እንግዲህ እንደሰማነው የሰኴር ኮርፖሬሸን ከመከላክያ ብረታ ብረት ኢንጅነሪንግ (ሜቴክ) ጋር በመሳለጥ 77 ቢሊዮን ብር (3. 8 ቢሊዬን የአሜሪካን ዶላር) እንደሰለቀጡ ነው የኦዲት ቢሮም፣ ባለስልጣናቱም ጀባ ያሉን:: በስራ አጋጣሚ ከኮርፖሬሽኑ እና ከሜቴክ ጋር በነበረኝ ግንኝነት ስለ ጉዳዩ የማውቀውን ያህል ለማካፈል እየሞከርኩ ነው:: ከዚህ ጥረቴ አንዱ በቅርቡ በሜይ  23, 2016  በኢሳት አምስተርዳም ስቱዲዮ እንወያይ በሚለው ፕሮግራም ላይ ተካፍዬ ነበር። የዚህ ጽሁፍ አላማም በውውይቱ የጠቀሰኳቸውን ጉዳዬች በተጨማሪም በሰአት ጥበት ምክንያት አልተጠቀሱም ብዬ ያሰብኳቸውን ጉዳዬች ለመዳስስ ነው።

እንግዲህ በህወሐት ጐራ ላለፉት ስድስት (ሰባት) አመታት በትልቁ ሲጐሰሙ ከነበሩ ትላልቅ (ሜጋ) ፕሮጅክቶች የስኳር ኰርፖሬሽን ዋንኛው ነው። በተጨባጭ መረጃዎች መሰረት በላዪም የመንግስት ቱባ ባለስልጣናት እንዳመኑት የስኳር ነገር “ወፍ የለም” እንደሚሉት ከሆነ ከራርሞአል፡፡ አይደለም ሰባት አዳዲስ የስኳር ፋብሪካዎች ይቅርና  የነበሩትን “ማስፋፊያ ፕሮጀክት” ብለው ነካክተው ምስቅልቅሉን አውጥተውታል፡፡ “ጥድቁ ቀርቶ በቅጡ በተኰነንኵ” እንዲሉ::

ላለፉት ስባት እና ስድስት አመታት እከሌ የሚባለው ኘሮጀክት ይህን ያህል ተጠናቋል፤ ያኛዉ ደግሞ በሚቀጥለው አመት ማምረት ይጀምርና ይህን ያህል ሚሊዬን ኩንታል ስኳር ወደ ዉጭ አገራት እንልካለን፤ እና የመሳሰሉትን የመግለጫ ጋጋታዎች ለሕዝቡ በስኳር ኰርፖሬሽን እና በሜቴክ የተጋቱ እንደ ስኳር ነጭ የሆኑ ዉሸቶች ናቸዉ። ለምን ይዋሻል? እንጠይቃለን። እስከመቼስ? በዉሸት እንዲህ ያሰከሩንስ ምን ሆኑ? ለዚህ ሁሉ ዉሸት ሐላፊነት ማን ወሰደ? አሁንም እንጠይቃለን። መልስ እስኪገኝ።

ባከነ የተባለዉ ገንዘብስ? 77 ቢሊዬን ብር (3.8 ቢሊዬን ዶላር)። ባከነ የሚለዉ ቃል ለእኔ ብዙ አይመስጠኝም። አማረኛ ማሳመሩን ትተን እዉነቱን በግልፅ አማርኛ መተንፈስ ነው የሚያዋጣው። ስለዚህ ተዘረፈ። ተሰረቀ። ነው የሚባለው። ሜቴክ በስኳር ኳርፖሬሽን ኘሮጀክቶች ስም ከኢትዬጵያ ሕዝብ ላይ ብሎም በሕዝብ ስም የተገኘውን የብድር ብር ዘረፈው ብንል እውነታውን በተሻለ መልኩ ይገለፃል። እንደ እኔ አሁን አማርኛ የምናጣፍጥበት ወቅት ላይ አይደለንም። 20 ሚሊዬን ሕዝብ ተርቦ የሚላስ የሚቀመስ ጠፍቶ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለተረጂ ወገኖቻችን የ 1.5 ቢሊዬን ዶላር ያለህ እያለ ሲጮህ፣ ሜቴክ ደግሞ 3.8 ቢሊዬን ዶላር ላፍ አድርጐ አየሁሽ አላየሁሽ እያለ ሲያፌዝብን የምን አማርኛ ማሳመር ነዉ? ምንስ ሊበጀን?

በግሌም ከኮርፖሬሽኑ ጋር ለመስራት የተስማሙ የውጭ ኩባንያዎችን በመወከል እሰራ ስለነበር የዘረፋውን ሒደት ለመታዘብ ችያአለሁ። የውጭ ኩባንያዎችን ወክዬ ከኮርፖሬሽኑ ጋር የተወሰኑትን ፕሮጀክቶች ለመውሰድ ስደራደር፣ ሜቴክ ከኋላ “ቀይዋን ያየ” በሚመስል ጨዋታ ስኳር ኮርፖሬሽን ሆኖ ብቅ አለ። ለካስ ኮርፖሬሽኑ ለስሙ ነው እንጂ ሙሉ በሙሉ በሜቴክ ቁጥጥር ስር ነው። ድርድሩንም፣ ብሩንም ወደ እኔ አለን ሜቴክ በወታደራዊ ቀጭን ትእዛዝ። ያው ወታደሮች አይደል የሚመሩት ወዴት እንደሆነ ባይታወቅም። የሜቴክ ሐላፊዎች የድፍረታቸው ድፍረት ገንዘቡን ብቻ ሳይሆን፣ በብድር ከሚገኘው ገንዘብ ላይ ኢንተረስት ሬትን ለመቀሸብ ሳይቀር ይደራደራሉ!? ወይ ድፍረት! አጃኢብ የሚያሰኝ ነው። በነገራችን ላይ ይህ ብድር በኢትዬጵያ ሕዝብ ስም እና በኢትዬጵያ ሶቨሪን ጋራንቲ (ዋስትና) የሚገኝ ነው። የማላስቸግራችሁ ከሆነ እና በግሌ ከሜቴክ ጋር የገባሁበትን እሰጥ እገባ ወይም ውዝግብ ለማወቅ ከፈለጋችሁ ከኢሳት ጋር ባደረኩት ውይይት በዚህ ማስፈንጠሪያ መኰምከም ይቻላል።

ጐበዝ ይኼ የሙስና ጉዳይ ብቻ አይደለም። በሙስና በሚታሙ አገሮች ሰርቼአለሁ። በእነዚህ አገራት ሌላው ቢቀር ሙስናው እንዴት እንደተከወነ ማየት የሚቻልበት መዋቅር (structure) አለ። በኢትዬጵያ ሁኔታ ይኸ ፈፅሞ አይታይም። ዘረፋው እጅግ አስፈሪ እና አደገኛ ነው። ሕወሐት አገሪቱን በኢኮኖሚ ሴክተሮች በመከፋፈል በምርቃና ፕሮጀክቶች ስም ሰቅዞ ያለማቋረጥ እየዘረፈ እና እየሰረቀ ነው። ስለዚህ ወይ ጉድ!? ወይ ሜቴክ? ወይ ስኳር ኮርፓሬሽን? እያልን በመደመም እንደ ተከታታይ ፊልም የምናየው የሙስና ጉዳይ ብቻ አይደለም። ኢትዬጵያ በዝርፊያ እየተናጠች ነው። የዝርፊያው መጠን እና አካሔድ እንደ አገር የመዝለቃችንን ነገር ፈተና ውስጥ ያስገባ ውስብስብ ቀውስ ነው።

ዳሩ ለውጥ አይቀሬ ነው። እንዲያው በዘገየ ቁጥር ለለዋጩ ሐይል አዲስ ጉልበት ሲጨምር፣ ለተለዋጩ ግን ወደ ማይወጡት ማጥ ውስጥ መነከር ነው። እንዲህ በአገር ላይ እያፌዙ መቀጠል ከቶ አይዘልቅም፣ አያዛልቅም። ለዘራፊዎች ግን አንድ ነገር ልበል። በቅርቡ አቶ አሰፋ ጨቦ “የትዝታ ፈለግ” የሚለውን መጽሐፍቸውን አስመልክተው አንድ ቃለ-መጠይቅ ሲሰጡ የተናገሩት ገጠመኝ ትዝ አለኝ። ደርግ ወድቆ ህወሐት አዲስ አበባን በተቆጣጠረበት ወቅት ነው አሉ። አዲስ አበባ ቀውጢ ሆናለች። እሳቸውም ከእስር የተፈቱበት ሰሞን ነው። እናም የጓደኛቸውን መኪና ይዘው ለመንዳት በአካባቢው ያገኙትን ሰው ቤንዚን የት ማግኘት እንደሚችሉ ይጠይቃሉ። ሰውየውም የት ማግኘት እንደሚችሉ ጠቁሟቸው፣ አንድ ነገር ግን ጠየቃቸው “ለመሆኑ ቤንዚኑን ቀድተህ መኪናውን የት ልትነዳው ነው በዚህ በቀውጢ ጊዜ?” እኔም ኢትዬጵያን እየዘረፉ ያሉትን ዘራፊ ባለስልጣናት ተመሳሳይ ጥያቄ ልጠይቅ። ለመሆኑ ይኼን ሁሉ ዘርፋችሁ የት እና መቼ ልትበሉት ነው?? ሊበላ?! አለች አሉ።

አገራችንን ፈጣሪ ይባርክ።

ወንድማአገኝ እጅጉ። ከ-ስቶኰልም፤ ስዊድን


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule