• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕገወጦቹ!”

April 21, 2015 06:47 am by Editor 1 Comment

አይሲስ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመባቸው ወገኖቻችን ቤተሰቦች መርዶ ሰምተው ሃዘን ተቀምጠው ባሉበት ወቅት ኢህአዴግና “የፌስቡክ የልማት አርበኛ ሚኒስትሮቹ” “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን እያጣራን፤ እስካሁን አላረጋገጥንም” እያሉ ያላግጡ ነበር፡፡

አዲስ አድማስ እንዲህ ይላል፡- “በአዲስ አበባ የኢያሱ ይኩኖአምላክ እና የባልቻ በለጠ ቤተሰቦች ድንገተኛ መርዶ የደረሳቸው እሁድ እለት ነው። በሰላሳዎቹ ዕድሜ ላይ የነበሩት ኢያሱና ባልቻ በአንድ ሰፈር ውስጥ ያደጉ ጎረቤታሞች ናቸው – በቀድሞው ወረዳ 21 ቀበሌ 25፤ በአሁኑ ወረዳ 10። የሟቾቹ ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት አጠገብ ለአጠገብ ስለሆነ ለቅሶውም አንድ ላይ ነው፡፡

“ኢያሱና ባልቻ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ወደ ሊቢያ የሄዱት አንድ ላይ እንደሆነ የገለፀልን የኢያሱ ወንድም፤ የሊቢያውን የግድያ ወሬ የሰማው እሁድ ዕለት ነው – ስልክ ተደውሎ። የደወለለት ሰው፣ “የናንተ ሰፈር ልጆች ሊታረዱ ሲሉ የሚያሳይ ፎቶ በፌስቡክ ተለጥፏል” ብሎ ሲነግረው፤ በደንጋጤ “እነማን ናቸው?” ብሎ ጠየቀ። “የወንድሜን ስም ጨምሮ ነገረኝ፤ የወንድሜን ስም አያውቅም ነበር” ይላል የኢያሱ ወንድም።

“የኔ ፌስቡክ ስለማይሰራ ጓደኛዬ ጋር ሄጄ አየሁ። በደንብ ስላልታየኝ እንደገና ከምሽቱ አራት ሰዓት ስንከፍት ወንድሜን ተንበርክኮ አየሁት። ባልቻን ደግሞ ቀይ ቱታ ካደረጉት መሀል ለየሁት፡፡ ለእናቴ ከመንገሬ በፊት ለሩቅ ዘመዶች ለመናገር እያሰብኩ እያለ እነሱ ቀድመው ሰምተው ለቅሶ ላይ አገኘኋቸው” ብሏል የኢያሱ ወንድም።balcha-and-eyasu

“ኢያሱ ኳታር ሰርቶ የተወሰነ ገንዘብ ይዞ ስለመጣ የባልቻንም ወጪ ሸፍኖለት ነው አብረው የሄዱት። ከኢትዮጵያ ወጥተው በሱዳን ጉዞ የጀመሩት ከሁለት ወር በፊት ነው። “ሱዳን እያሉ በስልክ እንገናኝ ነበር። ገንዘብ ሲያስፈልጋቸው እልክላቸው ነበር” የሚለው የኢያሱ ወንድም፤ “ወደ ሊቢያ ከተሻገሩ በኋላ ግን ስልክ ቁጥር እሰጥሃለሁ ቢለኝም አንገናኝም ነበር” ብሏል።

ስም ለማውጣት፤ ቃላት ለመሰንጠቅና ለመቀመር አቻ የማይገኝለት ኢህአዴግ ለሙታንም ሃዘኔታ የለውም፡፡ “አደገኛ ቦዘኔ፣ አሸባሪ፣ ሕገመንግሥት የሚንዱ፣ የልማት ጸሮች፣ …” እያለ ስም የሚለጥፈው ሳያንሰው ሟቾችንም ህገወጥ እያለ ለመጥራት ምንም አይገደውም፡፡ ኢህአዴግ “እያለባማት” ያለችውን ኢትዮጵያ ጥለው ስለሄዱ “ህገወጥ” ናቸው፡፡ አውሮጳና አሜሪካ ደርሰው ግን “የውጭ ምንዛሪ” መላክ ሲጀምሩ “ዲያስፖራ”፣ “ባለሃብት”፣ “ኢንቨስተር”፣ “የልማት አጋር”፣ የሚለውን ስያሜ ይጎናጸፋሉ፡፡

the twoሰኞ ምሽት የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ላይ የቀረበው ኤርምያስ ዓለማየሁ አይሲስ ስለገደለው አጎቱ ባልቻ በለጠ ሲናገር እንዲህ ብሏል፡፡

“በአንድ አገር ስደት የሚመጣበትን መሠረታዊ ነገር መረዳት (ይገባል)፤ የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ነው እነዚህ ወገኖች የሄዱት፤ … መንግሥት ምንም ያመጣልናል ብለን አናስብም፤ … መንግሥት የመጀመሪያ ዜና ላይ አስተባብሏል፤ ኢትዮጵውያን መሆናቸውን አላረጋገጥንም ብሏል፤ መንግሥት ዕውቅና ሳይሰጥ የውጭ ጣቢያዎች ዕውቅና ሰጥተዋል፤ … ዛሬ በቪዲዮ ስለታየና ግልጽ የሆነ መረጃ ስለተገኘ እንጂ ብዙ ወንድሞቻችን ሄደው አልቀዋል፤ መንግሥት “ስደተኛ” አይላቸውም፤ “ተቸግረው” አይላቸውም “ህገወጥ” ነው የሚላቸው፤ ይህ ሊሰመርበት ይገባል፤ “ህገወጥ ስደተኞች ሞቱ” ብሎ ነው መንግሥት በተደጋጋሚ የሚዘግበው፤ “ሕገወጥ” የሚለው ቃል ለዚያ ነገር ያለውን አመለካከት በግልጽ የሚያሳይ ነው፤ ወንድሞቻችንን ከዚህ የሄዱት ደልቷቸው አይደለም። ተቸግረው ነው። መንግስት ወንድሞቻችንን ስደተኛ ለማለት እንኳን አይፈልግም። ከመንግሥት ምንም (የምንጠብቀውና) የምንፈልገው ነገር የለም”፡፡ (የኢያሱና ባልቻ ፎቶ ከአዲስ አድማስ የተወሰደ)

በጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ የተቀናበረ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    April 22, 2015 03:41 am at 3:41 am

    ^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
    እያሱ ኳታር ሠርቶ ወገኑ ባልቻን ዕረዳውና
    ሊያልፍላቸው አስበው ኑሮአቸው ሊቀና
    ሰው በሀገሩ ሁለተኛ ዜጋ በቋንቋ በነገድ ውገና
    በቁም እሥር ከበይ ተመልካች ተቀምጠው ጎዳና
    ሀገር አቋረጡ ለተሻለ ኑሮ ድሃ ሀገር እናት ናትና
    ያው…ጭራቅ ሰው መሳይ አውሬ ገጠማቸውና
    ከጭንቀት ስቃይ እንዳቀረቀሩ ተቀሉ እንደገና!
    ****
    ይህን ነበር ያሉን ‘ሜንጫ’ ማለት ቡጢ ነው ?
    በቅርብ የፈራን የጮኽነው በእሩቁ አየነው
    ባለሥልጣናቱ ተሳናቸው አሉ ሙታንን መለየት
    ፓርቲ ብሄር ቋንቋ ሆኖ መለያው ልዩ ዜግነት
    እረ እንዴት? ባልቻ እና እያሱ ከመለስ አነሱ
    ልማታዊ አድር-ባይ! ሆድ-አደር! ሲተረማመሱ
    ድንኳን ጥለው በጥቅማጥቅም ወር ሲያስለቅሱ
    ጅግና ለወገኑ በቀዬው ሀዘኑን ላይገልፅ በዱላ መባረሩ
    ለወያናይት!ብቻ ሆነ ሀብት ምህዳር ሀገሩ ?
    ሳውዲያ ዓረቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ የመን፣
    ሊቢያ፣ ግብፅ፣ እስራኤል፣ በሱዳን አለቅን
    ኢህአዴግ ደስታውን ገለፀ ይበላችሁ አለን!
    እረ ለመሆኑ ቆሉብን ፈጩበን አላገጡብን
    ሠላም! ከዛሬ ነገ ስንል ዳሩ መሀል ሲሆን ታገስን
    አሁንስ አበዙት! አሁንስ ናቁት ትውልዱን
    ሰብከው ያጃጃሉን ልዩነታችን ነጣጥሎ አስበላን
    እንግዲህ ይነጋል ስንል ጨለመ በወገናችን
    ግዜው አሁን ነው የእንቢተኝነት አንድነታችን!!።
    ለሃይማኖታቸው ፅናት ለተቀሉ ነፍስ ይማርልን!
    በለው!*********

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule