• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕገወጦቹ!”

April 21, 2015 06:47 am by Editor 1 Comment

አይሲስ አሰቃቂ ግድያ የፈጸመባቸው ወገኖቻችን ቤተሰቦች መርዶ ሰምተው ሃዘን ተቀምጠው ባሉበት ወቅት ኢህአዴግና “የፌስቡክ የልማት አርበኛ ሚኒስትሮቹ” “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን እያጣራን፤ እስካሁን አላረጋገጥንም” እያሉ ያላግጡ ነበር፡፡

አዲስ አድማስ እንዲህ ይላል፡- “በአዲስ አበባ የኢያሱ ይኩኖአምላክ እና የባልቻ በለጠ ቤተሰቦች ድንገተኛ መርዶ የደረሳቸው እሁድ እለት ነው። በሰላሳዎቹ ዕድሜ ላይ የነበሩት ኢያሱና ባልቻ በአንድ ሰፈር ውስጥ ያደጉ ጎረቤታሞች ናቸው – በቀድሞው ወረዳ 21 ቀበሌ 25፤ በአሁኑ ወረዳ 10። የሟቾቹ ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት አጠገብ ለአጠገብ ስለሆነ ለቅሶውም አንድ ላይ ነው፡፡

“ኢያሱና ባልቻ የዛሬ ሁለት ወር ገደማ ወደ ሊቢያ የሄዱት አንድ ላይ እንደሆነ የገለፀልን የኢያሱ ወንድም፤ የሊቢያውን የግድያ ወሬ የሰማው እሁድ ዕለት ነው – ስልክ ተደውሎ። የደወለለት ሰው፣ “የናንተ ሰፈር ልጆች ሊታረዱ ሲሉ የሚያሳይ ፎቶ በፌስቡክ ተለጥፏል” ብሎ ሲነግረው፤ በደንጋጤ “እነማን ናቸው?” ብሎ ጠየቀ። “የወንድሜን ስም ጨምሮ ነገረኝ፤ የወንድሜን ስም አያውቅም ነበር” ይላል የኢያሱ ወንድም።

“የኔ ፌስቡክ ስለማይሰራ ጓደኛዬ ጋር ሄጄ አየሁ። በደንብ ስላልታየኝ እንደገና ከምሽቱ አራት ሰዓት ስንከፍት ወንድሜን ተንበርክኮ አየሁት። ባልቻን ደግሞ ቀይ ቱታ ካደረጉት መሀል ለየሁት፡፡ ለእናቴ ከመንገሬ በፊት ለሩቅ ዘመዶች ለመናገር እያሰብኩ እያለ እነሱ ቀድመው ሰምተው ለቅሶ ላይ አገኘኋቸው” ብሏል የኢያሱ ወንድም።balcha-and-eyasu

“ኢያሱ ኳታር ሰርቶ የተወሰነ ገንዘብ ይዞ ስለመጣ የባልቻንም ወጪ ሸፍኖለት ነው አብረው የሄዱት። ከኢትዮጵያ ወጥተው በሱዳን ጉዞ የጀመሩት ከሁለት ወር በፊት ነው። “ሱዳን እያሉ በስልክ እንገናኝ ነበር። ገንዘብ ሲያስፈልጋቸው እልክላቸው ነበር” የሚለው የኢያሱ ወንድም፤ “ወደ ሊቢያ ከተሻገሩ በኋላ ግን ስልክ ቁጥር እሰጥሃለሁ ቢለኝም አንገናኝም ነበር” ብሏል።

ስም ለማውጣት፤ ቃላት ለመሰንጠቅና ለመቀመር አቻ የማይገኝለት ኢህአዴግ ለሙታንም ሃዘኔታ የለውም፡፡ “አደገኛ ቦዘኔ፣ አሸባሪ፣ ሕገመንግሥት የሚንዱ፣ የልማት ጸሮች፣ …” እያለ ስም የሚለጥፈው ሳያንሰው ሟቾችንም ህገወጥ እያለ ለመጥራት ምንም አይገደውም፡፡ ኢህአዴግ “እያለባማት” ያለችውን ኢትዮጵያ ጥለው ስለሄዱ “ህገወጥ” ናቸው፡፡ አውሮጳና አሜሪካ ደርሰው ግን “የውጭ ምንዛሪ” መላክ ሲጀምሩ “ዲያስፖራ”፣ “ባለሃብት”፣ “ኢንቨስተር”፣ “የልማት አጋር”፣ የሚለውን ስያሜ ይጎናጸፋሉ፡፡

the twoሰኞ ምሽት የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ላይ የቀረበው ኤርምያስ ዓለማየሁ አይሲስ ስለገደለው አጎቱ ባልቻ በለጠ ሲናገር እንዲህ ብሏል፡፡

“በአንድ አገር ስደት የሚመጣበትን መሠረታዊ ነገር መረዳት (ይገባል)፤ የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ነው እነዚህ ወገኖች የሄዱት፤ … መንግሥት ምንም ያመጣልናል ብለን አናስብም፤ … መንግሥት የመጀመሪያ ዜና ላይ አስተባብሏል፤ ኢትዮጵውያን መሆናቸውን አላረጋገጥንም ብሏል፤ መንግሥት ዕውቅና ሳይሰጥ የውጭ ጣቢያዎች ዕውቅና ሰጥተዋል፤ … ዛሬ በቪዲዮ ስለታየና ግልጽ የሆነ መረጃ ስለተገኘ እንጂ ብዙ ወንድሞቻችን ሄደው አልቀዋል፤ መንግሥት “ስደተኛ” አይላቸውም፤ “ተቸግረው” አይላቸውም “ህገወጥ” ነው የሚላቸው፤ ይህ ሊሰመርበት ይገባል፤ “ህገወጥ ስደተኞች ሞቱ” ብሎ ነው መንግሥት በተደጋጋሚ የሚዘግበው፤ “ሕገወጥ” የሚለው ቃል ለዚያ ነገር ያለውን አመለካከት በግልጽ የሚያሳይ ነው፤ ወንድሞቻችንን ከዚህ የሄዱት ደልቷቸው አይደለም። ተቸግረው ነው። መንግስት ወንድሞቻችንን ስደተኛ ለማለት እንኳን አይፈልግም። ከመንግሥት ምንም (የምንጠብቀውና) የምንፈልገው ነገር የለም”፡፡ (የኢያሱና ባልቻ ፎቶ ከአዲስ አድማስ የተወሰደ)

በጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ የተቀናበረ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    April 22, 2015 03:41 am at 3:41 am

    ^^^^^^^^^^^^^^^^^^^^
    እያሱ ኳታር ሠርቶ ወገኑ ባልቻን ዕረዳውና
    ሊያልፍላቸው አስበው ኑሮአቸው ሊቀና
    ሰው በሀገሩ ሁለተኛ ዜጋ በቋንቋ በነገድ ውገና
    በቁም እሥር ከበይ ተመልካች ተቀምጠው ጎዳና
    ሀገር አቋረጡ ለተሻለ ኑሮ ድሃ ሀገር እናት ናትና
    ያው…ጭራቅ ሰው መሳይ አውሬ ገጠማቸውና
    ከጭንቀት ስቃይ እንዳቀረቀሩ ተቀሉ እንደገና!
    ****
    ይህን ነበር ያሉን ‘ሜንጫ’ ማለት ቡጢ ነው ?
    በቅርብ የፈራን የጮኽነው በእሩቁ አየነው
    ባለሥልጣናቱ ተሳናቸው አሉ ሙታንን መለየት
    ፓርቲ ብሄር ቋንቋ ሆኖ መለያው ልዩ ዜግነት
    እረ እንዴት? ባልቻ እና እያሱ ከመለስ አነሱ
    ልማታዊ አድር-ባይ! ሆድ-አደር! ሲተረማመሱ
    ድንኳን ጥለው በጥቅማጥቅም ወር ሲያስለቅሱ
    ጅግና ለወገኑ በቀዬው ሀዘኑን ላይገልፅ በዱላ መባረሩ
    ለወያናይት!ብቻ ሆነ ሀብት ምህዳር ሀገሩ ?
    ሳውዲያ ዓረቢያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ የመን፣
    ሊቢያ፣ ግብፅ፣ እስራኤል፣ በሱዳን አለቅን
    ኢህአዴግ ደስታውን ገለፀ ይበላችሁ አለን!
    እረ ለመሆኑ ቆሉብን ፈጩበን አላገጡብን
    ሠላም! ከዛሬ ነገ ስንል ዳሩ መሀል ሲሆን ታገስን
    አሁንስ አበዙት! አሁንስ ናቁት ትውልዱን
    ሰብከው ያጃጃሉን ልዩነታችን ነጣጥሎ አስበላን
    እንግዲህ ይነጋል ስንል ጨለመ በወገናችን
    ግዜው አሁን ነው የእንቢተኝነት አንድነታችን!!።
    ለሃይማኖታቸው ፅናት ለተቀሉ ነፍስ ይማርልን!
    በለው!*********

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule