• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚዲያው “እንቦጭ” ዘርዓይ አስገዶም ተነቀለ

May 14, 2018 08:08 pm by Editor 6 Comments

ለበርካታ ጋዜጠኞች ከሥራ መፈናቀል፤ ከአገር መሰደድ ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅነት የህወሓት ሥራ አስፈጻሚ የነበረው ዘርዓይ አስገዶም ከሥልጣኑ ተነስቷል።

አንደበቱ በቅጡ ያልተገራና ፍጹም የህወሓትን ዓላማ በአደባባይ በማስፈጸም የሚታወቀው ዘርዓይ፤ ከዚህ እንደፈለገ ከሚነዳው መ/ቤት መልቀቁ በሚዲያው ማኅበረሰብ ዘንድ እንደ ታላቅ አዎንታዊ እርምጃ ተወስዷል።

አንዳንድ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በላይ በቀለ፣ መሠረት አታላይ፣ ዮናስ ዲባባ፣ አስካለ በላይ፣ ካሳሁን ፈይሳ፣ እና ሌሎችም የሙያው ሰዎች በዚሁ የህወሓት ተጋዳላይ ትዕዛዝ ከሥራቸው እንዲለቁ መገደዳቸው ይታወቃል።

ዘርዓይ በሥልጣን በቆየባቸው ዓመታት ሦስት ብቻ በአማርኛ የሚታተሙ ጋዜጦች የነበሩ ሲሆን በክልላዊ ነጻነት የሚንቀሳቀሱትን የአማራ ሚዲያና የኦሮሚያ ብሮድካስትን በመዝለፍ የሚታወቅ መሆኑን የዞን ፱ ጦማሪ አጥናፍ ብርሃኔ ትዊት አድርጓል። የጋዜጠኛነት ወይም የጋዜጣ ማተም ፈቃድ ለማውጣት ቢሮው የሚሄዱ ሁሉ ከፍተኛ የሆነ የማንነት ምርመራ እንደሚካሄድባቸውና ፈቃድ እንደሚከለከሉ አጥናፍ ጨምሮ ጠቅሷል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ በተጻፈ ደብዳቤ ዘርዓይ አስገዶም ከቦታው ተነስቶ በምትኩ የደኢህዴኑ ሰሎሞን ተስፋዬ ተሹሟል። አዲሱ ተሿሚ የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቭዥን ምክትል ሥራ አስኪያጅ በመሆን አገልግሏል።

የሥርዓቱ ተሿሚ እንደመሆኑ ሰሎሞንም ብዙ ለውጥ ላያመጣ ይችላል ቢባልም የዘርዓይ መነሳት ግን ድርጅቱን በተወሰነ ነጻነት እንዲሠራ የሚያስችለውና በክልል የሚዲያ ሥራዎች ላይ የዘርዓይን በህወሓት የተቃኘ ተጽዕኖ እንዲነሳ የሚያደርግ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህም በተጨማሪ በዘርዓይ ዘመን ለጋዜጠኝነትና የጋዜጣ ኅትመት ሥራ ፈቃድ ለማውጣት የሚደረገውን ከማንነት ጋር የተያያዘ አፈናና ክልከላ በማስቆም ለግሉ ፕሬስ አንጻራዊ ነጻነት ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ዘርዓይ አስገዶም፤ ሃጫሉ ሁንዴሣ ቄሮ አራት ኪሎ ግባ በማለት በሚሊኒየም አዳራሽ ያቀረበውን ዜማ አጥብቆ የተቃወመና “ጸረ ሕዝብ ነው” በማለት የኮነነ ነበር። ዘፈኑ በቀጥታ ስርጭት በኦሮሞያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ኦቢኤን) በመተላለፉ ኦቢኤንን በመኮነን የዛቻ ንግግር በማድረግ ለትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ጭፍን ወገነተኛነቱን በግልጽ የመሰከረ ነበር። የአማራ ሚዲያንም የቴዲ አፍሮ ዘፈን ላይ የሚታየው ኮከብ አልባው ሠንደቅ ዓላማ በስብሰባዎች ላይ ሲታይ ምንም ሳይሉ በማስተላለፋቸው ዘርዓይ ወቀሳ ማቅረቡ ይታወሳል።

በእነዚህና በሌሎች በርካታ በሚዲያው ላይ በሠራቸው የአፈና ተግባራት ዘርዓይ አስገዶም በአንዳንዶች ዘንድ የሚዲያው “እንቦጭ” ተብሎ ይጠራል። (ፎቶ፤ ዘርዓይ አስገዶም፤ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: asgedom, Full Width Top, Middle Column, tplf, zeray

Reader Interactions

Comments

  1. Dawit Tesfaye says

    May 15, 2018 03:56 pm at 3:56 pm

    Thanks God.
    የቆየ ከሚስቱ ይወልዳል፡፡ እስከ ግንቦት 30 ምን ተጨማሪ እንሰማ ይሆን?

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    May 15, 2018 05:16 pm at 5:16 pm

    ተነቀለ? ቂቂቂ!!! ጨበርባሪ ወሬኛ ሁላ! መስሎሻል

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    May 15, 2018 08:52 pm at 8:52 pm

    እስቲ ምን እንደምትሆኑ እናያለን! ጨበርባሪዎች! ወልቂጤዎች!

    Reply
    • Yonas says

      May 16, 2018 07:32 pm at 7:32 pm

      Known TPLF cadre, paid with blood money for every keyboard stroke. Yemeshebet.

      Reply
  4. እዝራ says

    May 17, 2018 08:34 pm at 8:34 pm

    ሙሉጌታ ሐጎስ ይገባናል ። አፍቅሮ ተጋሩ ምደር እንደጠበበቻችሁ።
    ግን ግን እነ ዘርዓይ አስገዶምን ተጋሩ ብቻ እንጅ የሚወዳው፣ መላው ኢትጵያዊያን ከተከዜ ወዲህ ያለው መላው ኤርትራዊ ከመረብ ወዲያ ያለው በሙሉ ነቀዝ ብሎ የእህል ጎተራዉን ሁሉ ይመርጋል እንጅ እህሉን የሚፈጀዉን አንበጣ ማን ዝም ብሎ ያያል..? አንበጣን በዲዲቲ ካላጠፉት እህል መፈጀቱን መች ያቆማል እና ሙሉጌታ ሐጐስ ?

    Reply
  5. Alem says

    May 17, 2018 09:49 pm at 9:49 pm

    ውድ ጎልጉል፣
    የሚዲያው “እንቦጭ” ዘርዓይ አስገዶም ተነቀለ። ግሩም ርእስ ነው!
    ሌላኛው የወደድኩላችሁ፣ “ነፍጠኛ”ን ለወያኔ መጠቀማችሁ ነው።
    በርቱ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule