• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚዲያው “እንቦጭ” ዘርዓይ አስገዶም ተነቀለ

May 14, 2018 08:08 pm by Editor 6 Comments

ለበርካታ ጋዜጠኞች ከሥራ መፈናቀል፤ ከአገር መሰደድ ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅነት የህወሓት ሥራ አስፈጻሚ የነበረው ዘርዓይ አስገዶም ከሥልጣኑ ተነስቷል።

አንደበቱ በቅጡ ያልተገራና ፍጹም የህወሓትን ዓላማ በአደባባይ በማስፈጸም የሚታወቀው ዘርዓይ፤ ከዚህ እንደፈለገ ከሚነዳው መ/ቤት መልቀቁ በሚዲያው ማኅበረሰብ ዘንድ እንደ ታላቅ አዎንታዊ እርምጃ ተወስዷል።

አንዳንድ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በላይ በቀለ፣ መሠረት አታላይ፣ ዮናስ ዲባባ፣ አስካለ በላይ፣ ካሳሁን ፈይሳ፣ እና ሌሎችም የሙያው ሰዎች በዚሁ የህወሓት ተጋዳላይ ትዕዛዝ ከሥራቸው እንዲለቁ መገደዳቸው ይታወቃል።

ዘርዓይ በሥልጣን በቆየባቸው ዓመታት ሦስት ብቻ በአማርኛ የሚታተሙ ጋዜጦች የነበሩ ሲሆን በክልላዊ ነጻነት የሚንቀሳቀሱትን የአማራ ሚዲያና የኦሮሚያ ብሮድካስትን በመዝለፍ የሚታወቅ መሆኑን የዞን ፱ ጦማሪ አጥናፍ ብርሃኔ ትዊት አድርጓል። የጋዜጠኛነት ወይም የጋዜጣ ማተም ፈቃድ ለማውጣት ቢሮው የሚሄዱ ሁሉ ከፍተኛ የሆነ የማንነት ምርመራ እንደሚካሄድባቸውና ፈቃድ እንደሚከለከሉ አጥናፍ ጨምሮ ጠቅሷል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ በተጻፈ ደብዳቤ ዘርዓይ አስገዶም ከቦታው ተነስቶ በምትኩ የደኢህዴኑ ሰሎሞን ተስፋዬ ተሹሟል። አዲሱ ተሿሚ የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቭዥን ምክትል ሥራ አስኪያጅ በመሆን አገልግሏል።

የሥርዓቱ ተሿሚ እንደመሆኑ ሰሎሞንም ብዙ ለውጥ ላያመጣ ይችላል ቢባልም የዘርዓይ መነሳት ግን ድርጅቱን በተወሰነ ነጻነት እንዲሠራ የሚያስችለውና በክልል የሚዲያ ሥራዎች ላይ የዘርዓይን በህወሓት የተቃኘ ተጽዕኖ እንዲነሳ የሚያደርግ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህም በተጨማሪ በዘርዓይ ዘመን ለጋዜጠኝነትና የጋዜጣ ኅትመት ሥራ ፈቃድ ለማውጣት የሚደረገውን ከማንነት ጋር የተያያዘ አፈናና ክልከላ በማስቆም ለግሉ ፕሬስ አንጻራዊ ነጻነት ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ዘርዓይ አስገዶም፤ ሃጫሉ ሁንዴሣ ቄሮ አራት ኪሎ ግባ በማለት በሚሊኒየም አዳራሽ ያቀረበውን ዜማ አጥብቆ የተቃወመና “ጸረ ሕዝብ ነው” በማለት የኮነነ ነበር። ዘፈኑ በቀጥታ ስርጭት በኦሮሞያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ኦቢኤን) በመተላለፉ ኦቢኤንን በመኮነን የዛቻ ንግግር በማድረግ ለትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ጭፍን ወገነተኛነቱን በግልጽ የመሰከረ ነበር። የአማራ ሚዲያንም የቴዲ አፍሮ ዘፈን ላይ የሚታየው ኮከብ አልባው ሠንደቅ ዓላማ በስብሰባዎች ላይ ሲታይ ምንም ሳይሉ በማስተላለፋቸው ዘርዓይ ወቀሳ ማቅረቡ ይታወሳል።

በእነዚህና በሌሎች በርካታ በሚዲያው ላይ በሠራቸው የአፈና ተግባራት ዘርዓይ አስገዶም በአንዳንዶች ዘንድ የሚዲያው “እንቦጭ” ተብሎ ይጠራል። (ፎቶ፤ ዘርዓይ አስገዶም፤ ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: asgedom, Full Width Top, Middle Column, tplf, zeray

Reader Interactions

Comments

  1. Dawit Tesfaye says

    May 15, 2018 03:56 pm at 3:56 pm

    Thanks God.
    የቆየ ከሚስቱ ይወልዳል፡፡ እስከ ግንቦት 30 ምን ተጨማሪ እንሰማ ይሆን?

    Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    May 15, 2018 05:16 pm at 5:16 pm

    ተነቀለ? ቂቂቂ!!! ጨበርባሪ ወሬኛ ሁላ! መስሎሻል

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    May 15, 2018 08:52 pm at 8:52 pm

    እስቲ ምን እንደምትሆኑ እናያለን! ጨበርባሪዎች! ወልቂጤዎች!

    Reply
    • Yonas says

      May 16, 2018 07:32 pm at 7:32 pm

      Known TPLF cadre, paid with blood money for every keyboard stroke. Yemeshebet.

      Reply
  4. እዝራ says

    May 17, 2018 08:34 pm at 8:34 pm

    ሙሉጌታ ሐጎስ ይገባናል ። አፍቅሮ ተጋሩ ምደር እንደጠበበቻችሁ።
    ግን ግን እነ ዘርዓይ አስገዶምን ተጋሩ ብቻ እንጅ የሚወዳው፣ መላው ኢትጵያዊያን ከተከዜ ወዲህ ያለው መላው ኤርትራዊ ከመረብ ወዲያ ያለው በሙሉ ነቀዝ ብሎ የእህል ጎተራዉን ሁሉ ይመርጋል እንጅ እህሉን የሚፈጀዉን አንበጣ ማን ዝም ብሎ ያያል..? አንበጣን በዲዲቲ ካላጠፉት እህል መፈጀቱን መች ያቆማል እና ሙሉጌታ ሐጐስ ?

    Reply
  5. Alem says

    May 17, 2018 09:49 pm at 9:49 pm

    ውድ ጎልጉል፣
    የሚዲያው “እንቦጭ” ዘርዓይ አስገዶም ተነቀለ። ግሩም ርእስ ነው!
    ሌላኛው የወደድኩላችሁ፣ “ነፍጠኛ”ን ለወያኔ መጠቀማችሁ ነው።
    በርቱ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule