• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጁነዲን መጨረሻ አልታወቀም

December 1, 2012 12:58 am by Editor 1 Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም የኢትዮጵያን ታላቅ የሥልጣን መቀመጫ ሲረከቡ “ለተደረገልን ምደባ አመሰግናለሁ” ማለታቸውን ተከትሎ የከፍተኛ ባለሥልጣናት ሹመት “ምደባ” የሚል ስያሜ አግኝቷል። ትላንት ለተወካዮች ምክር ቤት በቀረበ የሽግሽግ ምደባ አቶ ጁነዲን ሳዶ ከምደባ ተዘለው ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ይፋ ሆኗል።

የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ወንበራቸውን ለአቶ ሙክታር ከድር እንዲያስረክቡ ተደርጓል። ኦህዴዱ አቶ ሙክታር የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ ታክሎላቸው አቶ ጁነዲን ሲመሩት የነበረውን የሲቪል ሰርቪስ ተቋም እንዲመሩ ሲደረግ አቶ ሃይለማርያም ስለአዲሱ ተሿሚ አቶ ሙክታር ቁርጠኛነትና ብቃት ሲያብራሩ ስለ አቶ ጁነዲን ከሃላፊነት መነሳት ግን ያሉት ነገር የለም።

አድሃና ሃይለ

ለዚህም ይመስላል የመድረክ አባል ብቸኛው ተቃዋሚ አቶ ግርማ ሰይፉ “ህዝብ የማወቅ መብት አለው” በማለት ስም ሳይጠሩ አቶ ጁነዲን የተነሱበት ምክንያት እንዲገለጽ “የተከበረውን” ፓርላማ የጠየቁት። ሚኒስትሮች ሲሾሙ መልካም ነገራቸው የሚገለጸውን ያህል ከስልጣን ሲነሱም ምክንያቱና በደላቸው ለህዝብ ሊነገር እንደሚገባው ሲጠይቁ መረጃው በፓርላማ ውስጥ ላሉት ሁሉ ጠቃሚ እንደሚሆን በማመላከት ነበር።

የነገሩ አካሄድ ያላማራቸው ህወሓቱ ዶ/ር አድሃና ሃይለ ምደባውን በተመለከተ “መክረንበታል” በማለት ምደባውን ወደ ማጸደቁ ስነስርዓት መሸጋገሩ እንደሚሻል ባሳሰቡት መሰረት ምክትል አፈ ጉባኤዋ መድረኩን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰጡ።“አመሰግናለሁ ምክትል አፈጉባኤ” በማለት ምላሻቸውን የጀመሩት አቶ ሃይለማርያም ከምደባው በፊት በቂ የተባለ ግምገማና የተለያዩ ልምዶች መወሰዳቸውን ደጋግመው በመግለጽ አቶ ግርማ ላነሱት መሰረታዊ ጥያቄ መልስ ሳይሰጡ አልፈውታል።

አቶ ጁነዲን ባለቤታቸው ከማንኛውም ችግር የጸዱና በእናታቸው ኑዛዜ አማካይነት መስጂድ ለማሰራት ከመንቀሳቀሳቸው ውጪ በተከሰሱበትና ፖሊስ ጠረጠርኳቸው ባለው ጉዳይ ሊገመቱ እንደማይገባ አቋማቸውን በመግለጽ ለሚዲያ ባሰራጩት መልክት ይፋ አድርገው ነበር። በዛው ሰሞን ኦህዴድ ውስጥ በተካሄደ “የመደብ ትግል” ግምገማ ከኦህዴድ ስራ አስፈጻሚነታቸው እንዲገለሉ መወሰኑ ይታወሳል።

በ1997 ዓ ም ምርጫ ኢተያ ወረዳ ተወዳድረው ከተሸነፉ በኋላ በይግባኝ እንደገና ለመመረጥ የቻሉት አቶ ጁነዲን በድጋሚው ምርጫ ሃይማኖታቸውን ተገን በማድረግ ያካሄዱት ቅስቀሳ ቀደም ሲል የኦሮሞ ኮንግረንስ ተወካይ የሆኑትን የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ እጩ የመረጡትን ሰዎች መቆሚያና መቀመጫ ያሳጣ እንደነበር የሚስታውሱ በሰጡት አስተያየት “አቶ ጁነዲን በልዩ ክትትል ስር እንዲሆኑና ከኦሮሚያ ፕሬዚዳንትነታቸው እንዲነሱ የተደረገበትም ምክንያት አርሲ ኢተያ ላይ ያካሄዱት የዳግም ምርጫ ዘመቻ ጣጣ ነው” ይላሉ። በወቅቱ የተደረገውን ቅስቀሳ ዛሬ መድገም አስፈላጊ እንዳልሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች “ወቅቱን ስናስበው ይዘገንነናል” በማለት ዝርዝር ከማቅረብ ተቆጥበዋል።

በተመሳሳይ እዛው ኢተያ ምርጫ ጣቢያ በዝረራ ከተሸነፉ በኋላ መንገድ ላይ የምርጫ ኮሮጆ በማዘረፍ እንዲደገም በተደረገው ምርጫ ተወዳድረው ያሸነፉት አባዱላ ገመዳ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በተወሰነው መሰረት ስልጣን የማስተላለፉ ስነስርዓት እንዳለቀ አቶ ጁነዲን “በሃላፊነቴ እንደማልቀጥል አስቀድሜ ከዓመት በፊት አውቀው ነበር” ማለታቸው በወቅቱ አነጋጋሪ ጉዳይ ነበር።

በቅርቡ ኦህዴድ ውስጥ ተፈጥሯል በተባለው ችግር ሳቢያ በተካሄደ ግምገማ ከስራ አስፈጻሚነት የተነሱት አቶ ጁነዲን ሳዶ ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ህግ ፊት እንደሚቀርቡ ኦህዴድ ያካሄደውን ግምገማ አስመልክቶ ውስጥ አዋቂዎችን በመጥቀስ ሰንደቅ ጋዜጣ መዘገቡ አይዘነጋም። ሪፖርተር ጋዜጣ በበኩሉ በተመሳሳይ ከድርጅት ስራ አስፈጻሚነት መነሳታቸውን ዜና ሲያደርግ ወደፊት ወደ ቀድሞው ሃላፊነታቸው ሊመለሱ እንደሚችሉ ተናግሮ ነበር። ከወራት በኋላ አቶ ጁነዲን ከስልጣናቸው ቢነሱም መጨረሻቸው ምን ሊሆን ይችላል የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።

ለጀርመን ድምጽ አማርኛው ክፍለጊዜ አጭር አስተያየት የሰጡት የአፍሪቃ ቀንድ ፖለቲካ በመተንተን የሚታወቁት አቶ ዩሱፍ ያሲን አቶ ጁነዲን ሳዶን አስመልክተው ለቀረበላቸው ጥያቄ “ምንም ማለት አይቻልም” በማለት ነበር መልሳቸውን ጀመሩት።ሲያብራሩም የአቶ ጁነዲን ባለቤት ቢከሰሱም እሳቸው ግን በሽብርተኛነት ከተከሰሱት 29 ተጠርጣሪዎች መካከል የሉበትም፣ በግምገማም ወቅት ተነሳ የተባለው ትክክለኛ ፍርድ አልሰጡም የሚል በመሆኑ ለጊዜው በግልጽ የታወቀ ነገር ስለሌለ አሰተያየት ለመስጠት እንደማይቻል በመጥቀስ አስተያየታቸውን ደምድመዋል። አስተያየት ሰጪው እንዳሉት ከመንግስት በኩል እስካሁን ጥርት ያለ መረጃ ባለመቅረቡ ጉዳዩ አስተያየት ለመስጠት እንደሚያስቸግር በተመሳሳይ ጎልጉል ያነጋገራቸው ገልጸዋል።

አቶ ዩሱፍ አጠቃላይ ምደባውን አስመልክቶ ግን በብሄር ተደራጅተው እንዲወዳደሩ የተፈጠሩት የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በስልጣንና በሃብት ክፍፍል የተነሳ የገቡበት ችግር በዚህ ሽግሽግ መፍትሄ ያገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል። ከአቶ መለስ ሞት በኋላ በስብሳባ የተጠመዱበት ችግር የጠና እንደሚመስላቸው የገለጹት አቶ ዩሱፍ፣ ወደፊት ኢህአዴግ በሚያካሂደው ጉባኤ፣ አሊያም ከሁለት ዓመት ተኩል በኋላ እስከሚያካሄደው ምርጫ ድረስ ችግሩን ለማስታመም የታቀደ እንደሚመስላቸው አመልክተዋል። የተደረገውን ሽግሽግ ችግር ፈቺ ሳይሆን በአገሪቱ ዋና ስልጣን እርከኖች ላይ የአንበሳው ድርሻ የማን ነው የሚለው ጉዳይ ያስከተለው ችግር በዚህ ውስን በሆነ ሽግሽግ መፍትሄ ሊያገኝ እንደማይችልም ጠቁመዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የጠ/ሚ/ር መንበር የተነፈገው ኦህዴድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነቱንም መቀመጫ በትላንትናው ምደባ ተዘልሏል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የኦህዴድ ጉባዔ አቋም ወዴት እንደሚያመራ ከወዲሁ ፍንጭ የለም፡፡ ይሁን እንጂ ጁነዲንን አስመልክቶ የኦህዴድ ምክርቤት በተለይ የሚወስነው ውሳኔ ከአቶ ሙክታር የምክትል ጠ/ሚ/ርነት ምደባ በላይ አጓጊ ሆኗል፡፡ የዛሬ አራት ዓመት አካባቢ አቶ ሙክታር ከኦሮሚያ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ተነስተው በኢህአዴግ ቢሮ ያለሥራ እንዲቀመጡ ሲደረግ በወቅቱ ሚ/ር የነበሩት አቶ ጁነዲን በወዳጆቻቸው አማካኝነት አቶ ሙክታር ወደ ጠ/ሚ/ር ቢሮ ኃላፊነት እንዲጠጋጉ ታላቁን ሚና መጫወታቸው በተለያየ ወቅት መገለጹ ይታወሳል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    December 2, 2012 12:18 am at 12:18 am

    Were you Amhara hater just to please your masters – the woyane ethnic fascists or have you done something usefull to Ethiopia and the people you were supposed to serve.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule