• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጁነዲን መጨረሻ አልታወቀም

December 1, 2012 12:58 am by Editor 1 Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም የኢትዮጵያን ታላቅ የሥልጣን መቀመጫ ሲረከቡ “ለተደረገልን ምደባ አመሰግናለሁ” ማለታቸውን ተከትሎ የከፍተኛ ባለሥልጣናት ሹመት “ምደባ” የሚል ስያሜ አግኝቷል። ትላንት ለተወካዮች ምክር ቤት በቀረበ የሽግሽግ ምደባ አቶ ጁነዲን ሳዶ ከምደባ ተዘለው ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ይፋ ሆኗል።

የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ወንበራቸውን ለአቶ ሙክታር ከድር እንዲያስረክቡ ተደርጓል። ኦህዴዱ አቶ ሙክታር የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ ታክሎላቸው አቶ ጁነዲን ሲመሩት የነበረውን የሲቪል ሰርቪስ ተቋም እንዲመሩ ሲደረግ አቶ ሃይለማርያም ስለአዲሱ ተሿሚ አቶ ሙክታር ቁርጠኛነትና ብቃት ሲያብራሩ ስለ አቶ ጁነዲን ከሃላፊነት መነሳት ግን ያሉት ነገር የለም።

አድሃና ሃይለ

ለዚህም ይመስላል የመድረክ አባል ብቸኛው ተቃዋሚ አቶ ግርማ ሰይፉ “ህዝብ የማወቅ መብት አለው” በማለት ስም ሳይጠሩ አቶ ጁነዲን የተነሱበት ምክንያት እንዲገለጽ “የተከበረውን” ፓርላማ የጠየቁት። ሚኒስትሮች ሲሾሙ መልካም ነገራቸው የሚገለጸውን ያህል ከስልጣን ሲነሱም ምክንያቱና በደላቸው ለህዝብ ሊነገር እንደሚገባው ሲጠይቁ መረጃው በፓርላማ ውስጥ ላሉት ሁሉ ጠቃሚ እንደሚሆን በማመላከት ነበር።

የነገሩ አካሄድ ያላማራቸው ህወሓቱ ዶ/ር አድሃና ሃይለ ምደባውን በተመለከተ “መክረንበታል” በማለት ምደባውን ወደ ማጸደቁ ስነስርዓት መሸጋገሩ እንደሚሻል ባሳሰቡት መሰረት ምክትል አፈ ጉባኤዋ መድረኩን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰጡ።“አመሰግናለሁ ምክትል አፈጉባኤ” በማለት ምላሻቸውን የጀመሩት አቶ ሃይለማርያም ከምደባው በፊት በቂ የተባለ ግምገማና የተለያዩ ልምዶች መወሰዳቸውን ደጋግመው በመግለጽ አቶ ግርማ ላነሱት መሰረታዊ ጥያቄ መልስ ሳይሰጡ አልፈውታል።

አቶ ጁነዲን ባለቤታቸው ከማንኛውም ችግር የጸዱና በእናታቸው ኑዛዜ አማካይነት መስጂድ ለማሰራት ከመንቀሳቀሳቸው ውጪ በተከሰሱበትና ፖሊስ ጠረጠርኳቸው ባለው ጉዳይ ሊገመቱ እንደማይገባ አቋማቸውን በመግለጽ ለሚዲያ ባሰራጩት መልክት ይፋ አድርገው ነበር። በዛው ሰሞን ኦህዴድ ውስጥ በተካሄደ “የመደብ ትግል” ግምገማ ከኦህዴድ ስራ አስፈጻሚነታቸው እንዲገለሉ መወሰኑ ይታወሳል።

በ1997 ዓ ም ምርጫ ኢተያ ወረዳ ተወዳድረው ከተሸነፉ በኋላ በይግባኝ እንደገና ለመመረጥ የቻሉት አቶ ጁነዲን በድጋሚው ምርጫ ሃይማኖታቸውን ተገን በማድረግ ያካሄዱት ቅስቀሳ ቀደም ሲል የኦሮሞ ኮንግረንስ ተወካይ የሆኑትን የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ እጩ የመረጡትን ሰዎች መቆሚያና መቀመጫ ያሳጣ እንደነበር የሚስታውሱ በሰጡት አስተያየት “አቶ ጁነዲን በልዩ ክትትል ስር እንዲሆኑና ከኦሮሚያ ፕሬዚዳንትነታቸው እንዲነሱ የተደረገበትም ምክንያት አርሲ ኢተያ ላይ ያካሄዱት የዳግም ምርጫ ዘመቻ ጣጣ ነው” ይላሉ። በወቅቱ የተደረገውን ቅስቀሳ ዛሬ መድገም አስፈላጊ እንዳልሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች “ወቅቱን ስናስበው ይዘገንነናል” በማለት ዝርዝር ከማቅረብ ተቆጥበዋል።

በተመሳሳይ እዛው ኢተያ ምርጫ ጣቢያ በዝረራ ከተሸነፉ በኋላ መንገድ ላይ የምርጫ ኮሮጆ በማዘረፍ እንዲደገም በተደረገው ምርጫ ተወዳድረው ያሸነፉት አባዱላ ገመዳ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ በተወሰነው መሰረት ስልጣን የማስተላለፉ ስነስርዓት እንዳለቀ አቶ ጁነዲን “በሃላፊነቴ እንደማልቀጥል አስቀድሜ ከዓመት በፊት አውቀው ነበር” ማለታቸው በወቅቱ አነጋጋሪ ጉዳይ ነበር።

በቅርቡ ኦህዴድ ውስጥ ተፈጥሯል በተባለው ችግር ሳቢያ በተካሄደ ግምገማ ከስራ አስፈጻሚነት የተነሱት አቶ ጁነዲን ሳዶ ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ህግ ፊት እንደሚቀርቡ ኦህዴድ ያካሄደውን ግምገማ አስመልክቶ ውስጥ አዋቂዎችን በመጥቀስ ሰንደቅ ጋዜጣ መዘገቡ አይዘነጋም። ሪፖርተር ጋዜጣ በበኩሉ በተመሳሳይ ከድርጅት ስራ አስፈጻሚነት መነሳታቸውን ዜና ሲያደርግ ወደፊት ወደ ቀድሞው ሃላፊነታቸው ሊመለሱ እንደሚችሉ ተናግሮ ነበር። ከወራት በኋላ አቶ ጁነዲን ከስልጣናቸው ቢነሱም መጨረሻቸው ምን ሊሆን ይችላል የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።

ለጀርመን ድምጽ አማርኛው ክፍለጊዜ አጭር አስተያየት የሰጡት የአፍሪቃ ቀንድ ፖለቲካ በመተንተን የሚታወቁት አቶ ዩሱፍ ያሲን አቶ ጁነዲን ሳዶን አስመልክተው ለቀረበላቸው ጥያቄ “ምንም ማለት አይቻልም” በማለት ነበር መልሳቸውን ጀመሩት።ሲያብራሩም የአቶ ጁነዲን ባለቤት ቢከሰሱም እሳቸው ግን በሽብርተኛነት ከተከሰሱት 29 ተጠርጣሪዎች መካከል የሉበትም፣ በግምገማም ወቅት ተነሳ የተባለው ትክክለኛ ፍርድ አልሰጡም የሚል በመሆኑ ለጊዜው በግልጽ የታወቀ ነገር ስለሌለ አሰተያየት ለመስጠት እንደማይቻል በመጥቀስ አስተያየታቸውን ደምድመዋል። አስተያየት ሰጪው እንዳሉት ከመንግስት በኩል እስካሁን ጥርት ያለ መረጃ ባለመቅረቡ ጉዳዩ አስተያየት ለመስጠት እንደሚያስቸግር በተመሳሳይ ጎልጉል ያነጋገራቸው ገልጸዋል።

አቶ ዩሱፍ አጠቃላይ ምደባውን አስመልክቶ ግን በብሄር ተደራጅተው እንዲወዳደሩ የተፈጠሩት የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በስልጣንና በሃብት ክፍፍል የተነሳ የገቡበት ችግር በዚህ ሽግሽግ መፍትሄ ያገኛል የሚል እምነት እንደሌላቸው ተናግረዋል። ከአቶ መለስ ሞት በኋላ በስብሳባ የተጠመዱበት ችግር የጠና እንደሚመስላቸው የገለጹት አቶ ዩሱፍ፣ ወደፊት ኢህአዴግ በሚያካሂደው ጉባኤ፣ አሊያም ከሁለት ዓመት ተኩል በኋላ እስከሚያካሄደው ምርጫ ድረስ ችግሩን ለማስታመም የታቀደ እንደሚመስላቸው አመልክተዋል። የተደረገውን ሽግሽግ ችግር ፈቺ ሳይሆን በአገሪቱ ዋና ስልጣን እርከኖች ላይ የአንበሳው ድርሻ የማን ነው የሚለው ጉዳይ ያስከተለው ችግር በዚህ ውስን በሆነ ሽግሽግ መፍትሄ ሊያገኝ እንደማይችልም ጠቁመዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የጠ/ሚ/ር መንበር የተነፈገው ኦህዴድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነቱንም መቀመጫ በትላንትናው ምደባ ተዘልሏል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የኦህዴድ ጉባዔ አቋም ወዴት እንደሚያመራ ከወዲሁ ፍንጭ የለም፡፡ ይሁን እንጂ ጁነዲንን አስመልክቶ የኦህዴድ ምክርቤት በተለይ የሚወስነው ውሳኔ ከአቶ ሙክታር የምክትል ጠ/ሚ/ርነት ምደባ በላይ አጓጊ ሆኗል፡፡ የዛሬ አራት ዓመት አካባቢ አቶ ሙክታር ከኦሮሚያ ምክትል ፕሬዚዳንትነት ተነስተው በኢህአዴግ ቢሮ ያለሥራ እንዲቀመጡ ሲደረግ በወቅቱ ሚ/ር የነበሩት አቶ ጁነዲን በወዳጆቻቸው አማካኝነት አቶ ሙክታር ወደ ጠ/ሚ/ር ቢሮ ኃላፊነት እንዲጠጋጉ ታላቁን ሚና መጫወታቸው በተለያየ ወቅት መገለጹ ይታወሳል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    December 2, 2012 12:18 am at 12:18 am

    Were you Amhara hater just to please your masters – the woyane ethnic fascists or have you done something usefull to Ethiopia and the people you were supposed to serve.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule