• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሕአዴግ ቁልቁለት

May 31, 2015 06:33 am by Editor 2 Comments

“ፋክት” መፅሔት ላይ ቋሚ አምደኛ በመሆን በየሳምንቱ በወቅታዊ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን ወደ አንባቢ ሲያደርስ የነበረው ሙሉዓለም ገ/መድኅን አዲስ መጽሐፍ ለኅትመት አብቅቷል፡፡

የመፅሃፉ ርዕስ፡- የኢሕአዴግ ቁልቁለት

ደራሲ ፡- ሙሉዓለም ገ/መድህን

የገፅ ብዛት፡- 235

ዋጋ ለአገር ውስጥ፡- 52 ብር ለውጪ አገር፡- 20 ዶላር

አጠቃላይ ይዘት

መፅሃፉ በአራት ክፍሎች እና በአስራ አራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን፣ ክፍል አንድ ላይ “ቁልቁለቱን በኢሕአዴግ ጎዳና” በሚል አምስት ምዕራፎች ተካተዋል፡፡ በዚህ ክፍል ብሶት ወለደኝ የሚለው ህወሓት ተነሳሁለት የሚለውን የትግል ዓላማ እንዴት እየቀለበሰው እንደመጣ በዝርዝር ያስቃኛል፣ በመስመር መሀል ከጫካ ጀምሮ የህወሓት የፖለቲካ አሽከር ስለሆነው ኢህዴን/ብአዴን ፖለቲካዊ ክሽፈት ያነሳል፣ ለቁጥር ብቻ ስለሚፈልጉት የኢሕአዴግ ሴቶች የፖለቲካ መሪነት ተሳትፎ ከአህዛዊ መረጃዎች ጋር እያነፃፀረ የሴቶቹን የቁጥር ማሟያነት በማሳያዎች አስደግፎ ያብራራል፣ ስለ ተጨፈለቀው የዳኝነት ነፃነት ጥያቄ እና ፍሬን አልባ ስለሆነው የአገዛዙ የዴሞክራሲ ቁልቁልነት ይተነትናል ፣ የኢህአዴግ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ኢትዮጵያን እንዴት ወደ ሶስተኛው አብዮት እየገፋት እንደሆነ በአገሪቱ የፖለቲካ አደባባይ ላይ እየታዩ ያሉ “አብዮታዊ ሁኔታዎች”ን እያጣቀሰ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ ክፍል ሁለት ደግሞ “በአዙሪት የታጅበው የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የቁልቁለቱ ተፅዕኖ” በሚል የቀረበ ሲሆን፤ በዚህ ክፍል የተካተቱ ምዕራፎች የያዟቸው መልእክቶች የኢትዮጵያን ፖለቲካ ጥልፍልፋዊ ጉዞ ለማሳየት ተክሯል፡፡ በተለይም “የሦስት ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ” በሚለው ምእራፍ ውስጥ ከነ ግርማሜ ንዋይ ትውልድ እስከ ያ ትውልድ ድረስ እንዲሁም ስለዚህኛው ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ ማሳያዎችን በማንሳት በዝርዝር ለማብራራት ተሞክሯል፡፡

downward spiral of eprdfክፍል ሶስት የአገሪቱን የሰሜን ምዕራብ ማህበረ-ፖለቲካዊ ሁነቶች የሚያስቃኝ ሲሆን፤ በአካባቢው እየታዩ ያሉ የብሔርተኝነትና የጎጠኝነት ስሜቶች፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ፣ የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል የአዋሳኝ ድንበር ወዝግብን በተመለከተ፣ በአካባቢው ስላለው ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር እና ስለ ቅማንት የማንነት ጥያቄና ውዝግቡ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ የመጨረሻ ክፍል የሆነው ክፍል አራት “ቁልቁለቱን ለማቆም ትልቁ የቤት ስራችን” የሚል ሲሆን፤ በዚህ ክፍል አገሪቱ ካለፉት አራት አስርታት ወዲህ የተጓዘችበትን የማህበረ-ፖለቲካ ጉዞ በማስቃኘት መጪው ጊዜ እጅግ አስከፊ መሆኑን በማሳየት መአቱን ለመሻገር ተቀራርቦ መወያየቱና አቻቻይ የመፍትሔ ሀሳብ በማፍለቅ አገሪቱን በብሔራዊ እርቅ ማንፃት ምርጫ የሌለው መንገድ መሆኑን በስፋት ይተነትናል፡፡

ስርጭት

መፅሀፉን በአገር ቤት በዋናነት በአዲስ አበባ ብሔራዊ ቲያትር ጀርባ “አይናለም መፅሐፍት መደብር” እና ጃፋር መፅሃፍት መደብር ውስጥ በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡ መፅሃፉ ለጊዜው በሰሜን አሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ባሉ የኢትዮጵያን ሬስቶራንቶች እና የሐበሻ ሱፐር ማርኬቶች በ20 ዶላር የቀረበ ሲሆን፤ በቀጣይ ቋሚ የመሸጫና ማከፋፈያ ቦታ ለማመቻቸት ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ በሌሎች የሰሜን አሜሪካ ግዛቶች፣ ካናዳ፣ አውሮፓ፣ አውስትራሊያ፣ መካከለኛው ምስራቅ፣ ደቡብ አፍሪካና መሰል አገራት መፅሐፉን ለመሸጥ የሚቻልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የመፅሃፉን ዋና አከፋፋይ በስልክ ቁጥር 0918 19 19 43 በመደወል ማነጋገር ይቻላል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Getiye Diriba says

    July 26, 2020 04:17 pm at 4:17 pm

    ለሚደርሰኝ መረጃ ሁሉ አመሠግናለሁ፡፡

    Reply
  2. amsayew says

    March 22, 2021 07:05 am at 7:05 am

    10q

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule