• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሕአዴግ ቁልቁለት

May 31, 2015 06:33 am by Editor 2 Comments

“ፋክት” መፅሔት ላይ ቋሚ አምደኛ በመሆን በየሳምንቱ በወቅታዊ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን ወደ አንባቢ ሲያደርስ የነበረው ሙሉዓለም ገ/መድኅን አዲስ መጽሐፍ ለኅትመት አብቅቷል፡፡

የመፅሃፉ ርዕስ፡- የኢሕአዴግ ቁልቁለት

ደራሲ ፡- ሙሉዓለም ገ/መድህን

የገፅ ብዛት፡- 235

ዋጋ ለአገር ውስጥ፡- 52 ብር ለውጪ አገር፡- 20 ዶላር

አጠቃላይ ይዘት

መፅሃፉ በአራት ክፍሎች እና በአስራ አራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን፣ ክፍል አንድ ላይ “ቁልቁለቱን በኢሕአዴግ ጎዳና” በሚል አምስት ምዕራፎች ተካተዋል፡፡ በዚህ ክፍል ብሶት ወለደኝ የሚለው ህወሓት ተነሳሁለት የሚለውን የትግል ዓላማ እንዴት እየቀለበሰው እንደመጣ በዝርዝር ያስቃኛል፣ በመስመር መሀል ከጫካ ጀምሮ የህወሓት የፖለቲካ አሽከር ስለሆነው ኢህዴን/ብአዴን ፖለቲካዊ ክሽፈት ያነሳል፣ ለቁጥር ብቻ ስለሚፈልጉት የኢሕአዴግ ሴቶች የፖለቲካ መሪነት ተሳትፎ ከአህዛዊ መረጃዎች ጋር እያነፃፀረ የሴቶቹን የቁጥር ማሟያነት በማሳያዎች አስደግፎ ያብራራል፣ ስለ ተጨፈለቀው የዳኝነት ነፃነት ጥያቄ እና ፍሬን አልባ ስለሆነው የአገዛዙ የዴሞክራሲ ቁልቁልነት ይተነትናል ፣ የኢህአዴግ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ኢትዮጵያን እንዴት ወደ ሶስተኛው አብዮት እየገፋት እንደሆነ በአገሪቱ የፖለቲካ አደባባይ ላይ እየታዩ ያሉ “አብዮታዊ ሁኔታዎች”ን እያጣቀሰ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ ክፍል ሁለት ደግሞ “በአዙሪት የታጅበው የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የቁልቁለቱ ተፅዕኖ” በሚል የቀረበ ሲሆን፤ በዚህ ክፍል የተካተቱ ምዕራፎች የያዟቸው መልእክቶች የኢትዮጵያን ፖለቲካ ጥልፍልፋዊ ጉዞ ለማሳየት ተክሯል፡፡ በተለይም “የሦስት ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ” በሚለው ምእራፍ ውስጥ ከነ ግርማሜ ንዋይ ትውልድ እስከ ያ ትውልድ ድረስ እንዲሁም ስለዚህኛው ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ ማሳያዎችን በማንሳት በዝርዝር ለማብራራት ተሞክሯል፡፡

downward spiral of eprdfክፍል ሶስት የአገሪቱን የሰሜን ምዕራብ ማህበረ-ፖለቲካዊ ሁነቶች የሚያስቃኝ ሲሆን፤ በአካባቢው እየታዩ ያሉ የብሔርተኝነትና የጎጠኝነት ስሜቶች፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ፣ የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል የአዋሳኝ ድንበር ወዝግብን በተመለከተ፣ በአካባቢው ስላለው ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር እና ስለ ቅማንት የማንነት ጥያቄና ውዝግቡ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ የመጨረሻ ክፍል የሆነው ክፍል አራት “ቁልቁለቱን ለማቆም ትልቁ የቤት ስራችን” የሚል ሲሆን፤ በዚህ ክፍል አገሪቱ ካለፉት አራት አስርታት ወዲህ የተጓዘችበትን የማህበረ-ፖለቲካ ጉዞ በማስቃኘት መጪው ጊዜ እጅግ አስከፊ መሆኑን በማሳየት መአቱን ለመሻገር ተቀራርቦ መወያየቱና አቻቻይ የመፍትሔ ሀሳብ በማፍለቅ አገሪቱን በብሔራዊ እርቅ ማንፃት ምርጫ የሌለው መንገድ መሆኑን በስፋት ይተነትናል፡፡

ስርጭት

መፅሀፉን በአገር ቤት በዋናነት በአዲስ አበባ ብሔራዊ ቲያትር ጀርባ “አይናለም መፅሐፍት መደብር” እና ጃፋር መፅሃፍት መደብር ውስጥ በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡ መፅሃፉ ለጊዜው በሰሜን አሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ባሉ የኢትዮጵያን ሬስቶራንቶች እና የሐበሻ ሱፐር ማርኬቶች በ20 ዶላር የቀረበ ሲሆን፤ በቀጣይ ቋሚ የመሸጫና ማከፋፈያ ቦታ ለማመቻቸት ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ በሌሎች የሰሜን አሜሪካ ግዛቶች፣ ካናዳ፣ አውሮፓ፣ አውስትራሊያ፣ መካከለኛው ምስራቅ፣ ደቡብ አፍሪካና መሰል አገራት መፅሐፉን ለመሸጥ የሚቻልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የመፅሃፉን ዋና አከፋፋይ በስልክ ቁጥር 0918 19 19 43 በመደወል ማነጋገር ይቻላል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Getiye Diriba says

    July 26, 2020 04:17 pm at 4:17 pm

    ለሚደርሰኝ መረጃ ሁሉ አመሠግናለሁ፡፡

    Reply
  2. amsayew says

    March 22, 2021 07:05 am at 7:05 am

    10q

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule