• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሕአዴግ ቁልቁለት

May 31, 2015 06:33 am by Editor 2 Comments

“ፋክት” መፅሔት ላይ ቋሚ አምደኛ በመሆን በየሳምንቱ በወቅታዊ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የሚያተኩሩ ፅሁፎችን ወደ አንባቢ ሲያደርስ የነበረው ሙሉዓለም ገ/መድኅን አዲስ መጽሐፍ ለኅትመት አብቅቷል፡፡

የመፅሃፉ ርዕስ፡- የኢሕአዴግ ቁልቁለት

ደራሲ ፡- ሙሉዓለም ገ/መድህን

የገፅ ብዛት፡- 235

ዋጋ ለአገር ውስጥ፡- 52 ብር ለውጪ አገር፡- 20 ዶላር

አጠቃላይ ይዘት

መፅሃፉ በአራት ክፍሎች እና በአስራ አራት ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን፣ ክፍል አንድ ላይ “ቁልቁለቱን በኢሕአዴግ ጎዳና” በሚል አምስት ምዕራፎች ተካተዋል፡፡ በዚህ ክፍል ብሶት ወለደኝ የሚለው ህወሓት ተነሳሁለት የሚለውን የትግል ዓላማ እንዴት እየቀለበሰው እንደመጣ በዝርዝር ያስቃኛል፣ በመስመር መሀል ከጫካ ጀምሮ የህወሓት የፖለቲካ አሽከር ስለሆነው ኢህዴን/ብአዴን ፖለቲካዊ ክሽፈት ያነሳል፣ ለቁጥር ብቻ ስለሚፈልጉት የኢሕአዴግ ሴቶች የፖለቲካ መሪነት ተሳትፎ ከአህዛዊ መረጃዎች ጋር እያነፃፀረ የሴቶቹን የቁጥር ማሟያነት በማሳያዎች አስደግፎ ያብራራል፣ ስለ ተጨፈለቀው የዳኝነት ነፃነት ጥያቄ እና ፍሬን አልባ ስለሆነው የአገዛዙ የዴሞክራሲ ቁልቁልነት ይተነትናል ፣ የኢህአዴግ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ኢትዮጵያን እንዴት ወደ ሶስተኛው አብዮት እየገፋት እንደሆነ በአገሪቱ የፖለቲካ አደባባይ ላይ እየታዩ ያሉ “አብዮታዊ ሁኔታዎች”ን እያጣቀሰ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ ክፍል ሁለት ደግሞ “በአዙሪት የታጅበው የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የቁልቁለቱ ተፅዕኖ” በሚል የቀረበ ሲሆን፤ በዚህ ክፍል የተካተቱ ምዕራፎች የያዟቸው መልእክቶች የኢትዮጵያን ፖለቲካ ጥልፍልፋዊ ጉዞ ለማሳየት ተክሯል፡፡ በተለይም “የሦስት ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ” በሚለው ምእራፍ ውስጥ ከነ ግርማሜ ንዋይ ትውልድ እስከ ያ ትውልድ ድረስ እንዲሁም ስለዚህኛው ትውልድ ተንከባላይ ዕዳ ማሳያዎችን በማንሳት በዝርዝር ለማብራራት ተሞክሯል፡፡

downward spiral of eprdfክፍል ሶስት የአገሪቱን የሰሜን ምዕራብ ማህበረ-ፖለቲካዊ ሁነቶች የሚያስቃኝ ሲሆን፤ በአካባቢው እየታዩ ያሉ የብሔርተኝነትና የጎጠኝነት ስሜቶች፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ፣ የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል የአዋሳኝ ድንበር ወዝግብን በተመለከተ፣ በአካባቢው ስላለው ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር እና ስለ ቅማንት የማንነት ጥያቄና ውዝግቡ በዝርዝር ያስቃኛል፡፡

የመፅሃፉ የመጨረሻ ክፍል የሆነው ክፍል አራት “ቁልቁለቱን ለማቆም ትልቁ የቤት ስራችን” የሚል ሲሆን፤ በዚህ ክፍል አገሪቱ ካለፉት አራት አስርታት ወዲህ የተጓዘችበትን የማህበረ-ፖለቲካ ጉዞ በማስቃኘት መጪው ጊዜ እጅግ አስከፊ መሆኑን በማሳየት መአቱን ለመሻገር ተቀራርቦ መወያየቱና አቻቻይ የመፍትሔ ሀሳብ በማፍለቅ አገሪቱን በብሔራዊ እርቅ ማንፃት ምርጫ የሌለው መንገድ መሆኑን በስፋት ይተነትናል፡፡

ስርጭት

መፅሀፉን በአገር ቤት በዋናነት በአዲስ አበባ ብሔራዊ ቲያትር ጀርባ “አይናለም መፅሐፍት መደብር” እና ጃፋር መፅሃፍት መደብር ውስጥ በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡ መፅሃፉ ለጊዜው በሰሜን አሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ባሉ የኢትዮጵያን ሬስቶራንቶች እና የሐበሻ ሱፐር ማርኬቶች በ20 ዶላር የቀረበ ሲሆን፤ በቀጣይ ቋሚ የመሸጫና ማከፋፈያ ቦታ ለማመቻቸት ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ በሌሎች የሰሜን አሜሪካ ግዛቶች፣ ካናዳ፣ አውሮፓ፣ አውስትራሊያ፣ መካከለኛው ምስራቅ፣ ደቡብ አፍሪካና መሰል አገራት መፅሐፉን ለመሸጥ የሚቻልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የመፅሃፉን ዋና አከፋፋይ በስልክ ቁጥር 0918 19 19 43 በመደወል ማነጋገር ይቻላል፡፡

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Getiye Diriba says

    July 26, 2020 04:17 pm at 4:17 pm

    ለሚደርሰኝ መረጃ ሁሉ አመሠግናለሁ፡፡

    Reply
  2. amsayew says

    March 22, 2021 07:05 am at 7:05 am

    10q

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule