• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአዘርባዣኑ ኢህአዴግ

October 11, 2013 09:49 pm by Editor Leave a Comment

ትላንት ረቡዕ በአዘርባዣን የተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ነጻና ፍትሓዊ እንደማይሆን የብዙዎች ግምት ነበር፡፡ ከ10ዓመት በፊት ከአባታቸው ሥልጣን በውርስ የተረከቡት ፕሬዚዳንት ዒልሃም አሊዬቭ የጋዜጠኞችን እና የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ በመገደባቸው የምርጫው ውጤት ምን እንደሚሆን ለመገመት ያዳገተ አልነበረም፡፡ እንደ ኢቲቪና ሬዲዮ በአገሪቷ መንግሥት የሚቆጣጠረውና ለገዢው ፖለቲካ መሣሪያነት የዋለ ሚዲያ በመኖሩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የነጻ ንግግር ገደብ እንዳሳሰባቸው ሲጠቁሙ ቆይተዋል፡፡ ቢቢሲም የምርጫው ውጤት አስቀድሞ የተወሰነ መሆኑን ዘግቦ ነበር፡፡

ምርጫ ተካሂዶ ቆጠራው ከመፈጸሙ በፊት የአዘርባዣን ማዕከላዊ የምርጫ ኮሚሽን ለብልህስልኮች (smartphones) አዘጋጅቶ የለቀቀው ግብረታ (app) ፕሬዚዳንቱ በ72.76 በመቶ ማሸነፋቸውን የሚያሳይ ነበር፡፡ እኤአ በ2003 በተካሄደው ምርጫ አሊዬቭ በ76.84በመቶ በ2008 ደግሞ በ87በመቶ “ማሸነፋቸው” ይታወቃል፡፡

የምርጫው ኮሚሽን ከምርጫ በፊት የወሰነው የፕሬዚዳንቱን ነጠብ ብቻ ሳይሆን የተሸናፊዎቹንም ውጤት ወስኖ ማስቀመጡ በዚህ በተላለፈው መልዕክት ላይ በግልጽ ይታያል፡፡  የተቃዋሚ ፓርቲ ተወዳዳሪ የነበሩት ጃሚል ሃሳናሊ 7.4በመቶ ማምጣታቸውን አክሎበታል፡፡

መረጃው ከተለቀቀ በኋላ ወዲያውኑ የተመለሰ ሲሆን መንግሥት ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ ግብረቱን (app) የሰራው ኩባንያ በስህተት የ2008ዓም ምርጫ ውጤትን ነበር የለቀቀው የሚል ነበር፡፡ በ2008 ደግሞ ፕሬዚዳንት አሊዬቭ 87በመቶ “ማሸነፋቸው” በገሃድ የሚታወቅ ጉዳይ በመሆኑ ማስተባበያው ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡

azarbajan sms
ከምርጫ በፊት ምርጫ ኮሚሽን በስልክ የለቀቀው የምርጫ ውጤት

ማሸነፋቸው አስቀድሞ የተወሰነላቸውና አሁን ደግሞ በስፋት እየተዘገበላቸው ያለው አሊዬቭ በመንግሥታቸው ቴሌቪዥን ቀርበው ሲናገሩ “የአገሬ ዜጎች እምነታቸውን በእኔ ላይ በማድረግ እና ወደፊት ለምናከናውነው የአገራችን ልማት መሳካት በማሰብ ስለመረጡኝ በጣም አመሰግናለሁ” ብለዋል፡፡

የአሊዬቭን ልማታዊ ፓርቲ በመደገፍ የመረጠው ልማታዊ መራጭ ሲናገር “ፕሬዚዳንታችንን የመረጥነው ለአዘርባዣን እንደ ዒልሃም አሊዬቭ ዓይነት ባለራዕይ መሪ የትም ስለማይገኝ ነው” ብሏል፡፡ ከተቃዋሚው በኩል አስተያየቱን የሰጠ ደግሞ እንዲህ በማለት ምሬቱ ገልጾዋል፤ “የዚህ አገር ባለሥልጣናት በዚህች አገር ያለውን ሃብት እንደፈለጉ እንደሚዘርፉ ሁሉ አሁን ደግሞ ድምጻችንን ዘርፈዋል፡፡”

ፕሬዚዳንቱ የምስጋና ንግግሩን የተናገሩት የድምጽ ቆጠራው ከመጠናቀቁ በፊት ሲሆን በሚናገሩበትም ወቅት 85በመቶ ማሸነፋቸውና በድጋሚ ፕሬዚዳንት መሆናቸው በይፋ እየተነገረ ነበር፡፡

በ1997 በአገራችን ላይ በተካሄደው ምርጫም ድምጽ ተቆጥሮ ከመጠናቀቁ በፊት አቶ መለስ በኢቲቪ መስኮት ብቅ ብለው ኢህአዴግ ማሸነፉንና የአገር መሪነቱ መረከቡን ማወጃቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱም እርሳቸው በሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ 197 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸው በማስረጃ በመረጋገጡ አቶ መለስን ለፍርድ ለማቅረብ ሁሉን ዓቀፍ ጥረት እየተካሄደ ነበር፡፡

በቀጣይ በተካሄደው ምርጫ በአዘርባዣን በተካሄደው በተለየ መልኩ ኢህአዴግ በ99.6በመቶ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በመቆጣጠሩ ኢትዮጵያ “የልማታዊ ዜጎች” አገር ለመሆን በቅታለች፡፡

በኢትዮጵያ በቅርቡ በሚካሄደው ምርጫ እንደ አዘርባዣን ዓይነት ስህተት እንዳይከሰትና ከምርጫው አንድ ሳምንት በፊት የምርጫ ኮሚሽን ውጤት እንዳያወጣ የሰጉ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበትና በዚህ ረገድ ኢንሣ፣ ኢቲዮ ቴሌኮም፣ ኢቲቪና የምርጫ ኮሚሽን ልማታዊ ተግባራቸውን እንዲወጡ አስቀድመው ያስጠነቅቃሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule