• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአዘርባዣኑ ኢህአዴግ

October 11, 2013 09:49 pm by Editor Leave a Comment

ትላንት ረቡዕ በአዘርባዣን የተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ነጻና ፍትሓዊ እንደማይሆን የብዙዎች ግምት ነበር፡፡ ከ10ዓመት በፊት ከአባታቸው ሥልጣን በውርስ የተረከቡት ፕሬዚዳንት ዒልሃም አሊዬቭ የጋዜጠኞችን እና የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ በመገደባቸው የምርጫው ውጤት ምን እንደሚሆን ለመገመት ያዳገተ አልነበረም፡፡ እንደ ኢቲቪና ሬዲዮ በአገሪቷ መንግሥት የሚቆጣጠረውና ለገዢው ፖለቲካ መሣሪያነት የዋለ ሚዲያ በመኖሩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የነጻ ንግግር ገደብ እንዳሳሰባቸው ሲጠቁሙ ቆይተዋል፡፡ ቢቢሲም የምርጫው ውጤት አስቀድሞ የተወሰነ መሆኑን ዘግቦ ነበር፡፡

ምርጫ ተካሂዶ ቆጠራው ከመፈጸሙ በፊት የአዘርባዣን ማዕከላዊ የምርጫ ኮሚሽን ለብልህስልኮች (smartphones) አዘጋጅቶ የለቀቀው ግብረታ (app) ፕሬዚዳንቱ በ72.76 በመቶ ማሸነፋቸውን የሚያሳይ ነበር፡፡ እኤአ በ2003 በተካሄደው ምርጫ አሊዬቭ በ76.84በመቶ በ2008 ደግሞ በ87በመቶ “ማሸነፋቸው” ይታወቃል፡፡

የምርጫው ኮሚሽን ከምርጫ በፊት የወሰነው የፕሬዚዳንቱን ነጠብ ብቻ ሳይሆን የተሸናፊዎቹንም ውጤት ወስኖ ማስቀመጡ በዚህ በተላለፈው መልዕክት ላይ በግልጽ ይታያል፡፡  የተቃዋሚ ፓርቲ ተወዳዳሪ የነበሩት ጃሚል ሃሳናሊ 7.4በመቶ ማምጣታቸውን አክሎበታል፡፡

መረጃው ከተለቀቀ በኋላ ወዲያውኑ የተመለሰ ሲሆን መንግሥት ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ ግብረቱን (app) የሰራው ኩባንያ በስህተት የ2008ዓም ምርጫ ውጤትን ነበር የለቀቀው የሚል ነበር፡፡ በ2008 ደግሞ ፕሬዚዳንት አሊዬቭ 87በመቶ “ማሸነፋቸው” በገሃድ የሚታወቅ ጉዳይ በመሆኑ ማስተባበያው ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡

azarbajan sms
ከምርጫ በፊት ምርጫ ኮሚሽን በስልክ የለቀቀው የምርጫ ውጤት

ማሸነፋቸው አስቀድሞ የተወሰነላቸውና አሁን ደግሞ በስፋት እየተዘገበላቸው ያለው አሊዬቭ በመንግሥታቸው ቴሌቪዥን ቀርበው ሲናገሩ “የአገሬ ዜጎች እምነታቸውን በእኔ ላይ በማድረግ እና ወደፊት ለምናከናውነው የአገራችን ልማት መሳካት በማሰብ ስለመረጡኝ በጣም አመሰግናለሁ” ብለዋል፡፡

የአሊዬቭን ልማታዊ ፓርቲ በመደገፍ የመረጠው ልማታዊ መራጭ ሲናገር “ፕሬዚዳንታችንን የመረጥነው ለአዘርባዣን እንደ ዒልሃም አሊዬቭ ዓይነት ባለራዕይ መሪ የትም ስለማይገኝ ነው” ብሏል፡፡ ከተቃዋሚው በኩል አስተያየቱን የሰጠ ደግሞ እንዲህ በማለት ምሬቱ ገልጾዋል፤ “የዚህ አገር ባለሥልጣናት በዚህች አገር ያለውን ሃብት እንደፈለጉ እንደሚዘርፉ ሁሉ አሁን ደግሞ ድምጻችንን ዘርፈዋል፡፡”

ፕሬዚዳንቱ የምስጋና ንግግሩን የተናገሩት የድምጽ ቆጠራው ከመጠናቀቁ በፊት ሲሆን በሚናገሩበትም ወቅት 85በመቶ ማሸነፋቸውና በድጋሚ ፕሬዚዳንት መሆናቸው በይፋ እየተነገረ ነበር፡፡

በ1997 በአገራችን ላይ በተካሄደው ምርጫም ድምጽ ተቆጥሮ ከመጠናቀቁ በፊት አቶ መለስ በኢቲቪ መስኮት ብቅ ብለው ኢህአዴግ ማሸነፉንና የአገር መሪነቱ መረከቡን ማወጃቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱም እርሳቸው በሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ 197 ንጹሃን ዜጎች መገደላቸው በማስረጃ በመረጋገጡ አቶ መለስን ለፍርድ ለማቅረብ ሁሉን ዓቀፍ ጥረት እየተካሄደ ነበር፡፡

በቀጣይ በተካሄደው ምርጫ በአዘርባዣን በተካሄደው በተለየ መልኩ ኢህአዴግ በ99.6በመቶ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በመቆጣጠሩ ኢትዮጵያ “የልማታዊ ዜጎች” አገር ለመሆን በቅታለች፡፡

በኢትዮጵያ በቅርቡ በሚካሄደው ምርጫ እንደ አዘርባዣን ዓይነት ስህተት እንዳይከሰትና ከምርጫው አንድ ሳምንት በፊት የምርጫ ኮሚሽን ውጤት እንዳያወጣ የሰጉ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበትና በዚህ ረገድ ኢንሣ፣ ኢቲዮ ቴሌኮም፣ ኢቲቪና የምርጫ ኮሚሽን ልማታዊ ተግባራቸውን እንዲወጡ አስቀድመው ያስጠነቅቃሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule