• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የረመዳን ወግ

July 7, 2014 11:10 pm by Editor 5 Comments

ወቅቱ ረመዳን ነው፡፡ እነሆ ለረመዳን የሚሆን (አንድ ወግ) ልጋብዛችሁ፡፡

ኸሊፋው ዑመር ኢብን አል-ኸጣብ ዘወትር እንደሚያደርገው የነዋሪዎቹን ሁኔታ ለመታዘብ በምሽት በመዲና ጎዳዎች ላይ ይንጎራደድ ነበር፡፡ ወደ አንድ ሰፈር ሲደርስ በስካር መንፈስ የሚለፈልፍ ሰው ድምጽ ሰማ፡፡ ወደ ቤቱ ተጠግቶ በመስኮት ቢያይ ሰውዬው የወይን ጠጅ እየጠጣ ዓለሙን ሲቀጭ አገኘው፡፡ ዑመር አላስቻለውም፡፡ በመስኮት ዘሎ ገባና ሰውዬውን “አንተ ምን መስራትህ ነው?… ከሰው ብትደበቅ ከአላህ መሰወር የምትችል መሰለህ?… ወይን ጠጅ ለምንድነው የምትጠጣው?” በማለት ተቆጣው፡፡

ሰውዬው እንግዳውን ትክ ብሎ ቢያይ ዑመር ነው፡፡ በጣም ደነገጠ፡፡ ስካሩ በአንድ ጊዜ ለቀቀው፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ተረጋጋና ዑመርን እንዲህ አለው፡፡

“ኸሊፋው ልክ ነዎት! ወይን ጠጅ መጠጣቴ ሐጢአት ነው፡፡ ይሁንና እኔ አንድ ጥፋት ብቻ ነው የሰራሁት፡፡ እርስዎ ግን በዚህች ቅጽበት ሶስት ጥፋቶችን ሰርተዋል”፡፡

ዑመር ሰውዬውን እየተመለከተ “ጥፋቶቼ ምን ምን ናቸው?” አለው፡፡

ሰውዬውም እንዲህ ዘረዘረለት፡፡ “አንደኛ አላህ የሌሎችን ነውር አትከታተሉ ብሏል፡፡ እርስዎ ግን ይህንን ቃል ጥሰው እኔ በድብቅ የምሰራውን አይተዋል፡፡ ሁለተኛ አላህ ወደ ሌሎች ሰዎች ቤት ስትገቡ የባለቤቶቹን ፈቃድ ጠይቁ ብሏል፡፡ እርስዎ ግን ያለኔ ፈቃድ ነው ወደ ቤቴ የገቡት፡፡ ሶስተኛ አላህ ወደቤት ስትገቡ በበር ግቡ ነው ያለው፡፡ እርስዎ ግን በመስኮት ነው የገቡት”፡፡

ዑመር ጥፋቱን አንድ በአንድ አመነ፡፡ እናም “ለጥፋቴ ማበሻ ምን ይሻላል ትላለህ ታዲያ?” በማለት ጠየቀው፡፡

ሰውዬውም “ለሁለታችንም ጥፋቶች ማበሻ የሚሆን መድኒት አላህ ተናግሯል፡፡ ይኸውም የጓዶቻችሁን ነውር ደብቁ የሚለው ነው፡፡ እኔም እርስዎ የሰሩትን ጥፋት ለማንም አልናገርም፡፡ እርስዎም የኔን ስካር ለማንም አይንገሩብኝ፡፡ ከአሁን ወዲያ ላልጠጣ በአላህ ስም ቃሌን እሰጣለሁ” አላቸው፡፡

ዑመር በሰካራሙ ሰውዬ ብልሃት በጣም ተንደቆ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ሰውዬው ሞቶ ይህንን ታሪክ ለተከታዮቹ ከማጫወቱ በፊት ለማንም ተናግሮት አያውቅም፡፡

የሰውን ነውር በመከታተል ሱስ የተለከፋችሁ ሰዎች ሆይ! እባካችሁ ተመከሩ፡፡ የሌላውን ነውር እከታተላሁ ብላችሁ ለራሳችሁ ኩንታል ሙሉ ሐጢአት እንዳትፈጽሙ፡፡

የሰውን ነውር ያያችሁ ሰዎች ሆይ! የጓዶቻችሁን ነውር አታውሩ! የባልንጀራችሁን ነውር ከደበቃችሁለት አላህ እናንተንም ከመጥፎው ሁሉ ይሰውራችኋል፡፡

—–

አፈንዲ ሙተቂ
ሰኔ 21/2005
ሀረር- ምስራቅ ኢትዮጵያ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. መስፍን says

    July 9, 2014 02:27 am at 2:27 am

    አፈንዲ ምን አይነት ፍልስፍና ለታስተምር እንደሆነ አልገባኝም ፣ ወሸታሙን ቀጣፊ ባለማለታችን ፣ባንዳውን አገሩን ለጥቅም የሸጠውን
    ባለማጋለጣችን ፣ ከጣሊያንና አሁን ደግሞ በእኛ እደሜ ያየነው ከሰማሌ ጋር በመሆን አገሩን የወጋውን ባለማሳወቃችን ህዝብ እንዲያቀው በለማደረጋችን ፣ይህው አሁን አገራችን የባንዶች መጫወቻ ሆናለች ።ማለት ያለብን በውሸት ሥም አለማጥፋት ፣የሰራን ማመስገን፣እህ ምንተባለ ብሎ ጠይቆ ያለተረጋገጠ ወሬ መንዛት፣መጥፎ መሆን መስበክ እንጂ እንዴት ነውር ይደበቅ በለህ ምሳሌ ታቀርባለህ? የህው እነታምራት
    ላይኔ የሰሩት ተረስቶ የጨበጨብላቸዋል ፣እነ ሰዬ? ! አንዳርጋቸውም የሄው በኤርትራ እርዳታ ነፃ ያወጣናል ብሎ አዳሜ ቴያትር የሰራል! ይህ ሁሉ ነውረኛን በመደበቃችን ነው ።

    Reply
    • shimon says

      July 11, 2014 10:17 am at 10:17 am

      “ረጅም እድሜ!

      Reply
  2. anwar says

    July 9, 2014 04:15 pm at 4:15 pm

    Mesfene I agree the lesson from the story is for people who are close to you or someone you know not to embarrass them in public basically don’t go around and be fault finder .but for the people you mentioned above of course we have to use all our means to fight them dictators and those who support them will never give you your rights .you have to take it. tnx by the way afendy good story I didn’t mean any harm

    Reply
  3. Amenen Gudaye says

    July 11, 2014 03:06 am at 3:06 am

    Mr Afendy if you have another please.

    Reply
  4. ቶቶ says

    August 10, 2014 02:48 pm at 2:48 pm

    እነደው ለመሆኑ ይሄን ታሪክ ከየት ይሆን ያገኙት ውድ ጸሃፊዬ? ነው ወይስ እስላም እንዲህ የሚራራ ነው ብለው ሊሉን ፈልገው ይሆን? ለመሆኑ በእስልምና መጠጥ፡ መጠጣት ከ8-14 ድረስ የሚሆን ግርፋት እንደሚያመጣ ሃዲቱ የተለያዩ ኡለማዎች እንደሚናገሩ ረስተውት ይሆን? ለማንኛውም እስላም ምን እንደሆነ የኢራቁ እስላማዊ እስቴት (ISIL) በተግባር እያሳየን ስለሆነ የእርሶ እስልምና እንደው የጥጥ ከረሜላውን አይነት መሰለ። ነው ወይንስ ከሰሞኑ በሊባኖስ እና በተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅ ያሉ አረብ አገራት በሮመዳን ጾም ጊዜ ምግብ ሲበሉ እንዳይታዩ (እስላም ያልሆኑትን) እንደውም ( Saudi warns non-Muslims on Ramadan fasting /http://www.upi.com/Business_News/Security-Industry/2005/10/01/Saudi-warns-non-Muslims-on-Ramadan-fasting/UPI-67841128194966/?rel=78121373377801) እንደው ቀልዶትን ቢያቆሙ ብዬ ነው

    Reply

Leave a Reply to anwar Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule