• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የረመዳን ወግ

July 7, 2014 11:10 pm by Editor 5 Comments

ወቅቱ ረመዳን ነው፡፡ እነሆ ለረመዳን የሚሆን (አንድ ወግ) ልጋብዛችሁ፡፡

ኸሊፋው ዑመር ኢብን አል-ኸጣብ ዘወትር እንደሚያደርገው የነዋሪዎቹን ሁኔታ ለመታዘብ በምሽት በመዲና ጎዳዎች ላይ ይንጎራደድ ነበር፡፡ ወደ አንድ ሰፈር ሲደርስ በስካር መንፈስ የሚለፈልፍ ሰው ድምጽ ሰማ፡፡ ወደ ቤቱ ተጠግቶ በመስኮት ቢያይ ሰውዬው የወይን ጠጅ እየጠጣ ዓለሙን ሲቀጭ አገኘው፡፡ ዑመር አላስቻለውም፡፡ በመስኮት ዘሎ ገባና ሰውዬውን “አንተ ምን መስራትህ ነው?… ከሰው ብትደበቅ ከአላህ መሰወር የምትችል መሰለህ?… ወይን ጠጅ ለምንድነው የምትጠጣው?” በማለት ተቆጣው፡፡

ሰውዬው እንግዳውን ትክ ብሎ ቢያይ ዑመር ነው፡፡ በጣም ደነገጠ፡፡ ስካሩ በአንድ ጊዜ ለቀቀው፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ተረጋጋና ዑመርን እንዲህ አለው፡፡

“ኸሊፋው ልክ ነዎት! ወይን ጠጅ መጠጣቴ ሐጢአት ነው፡፡ ይሁንና እኔ አንድ ጥፋት ብቻ ነው የሰራሁት፡፡ እርስዎ ግን በዚህች ቅጽበት ሶስት ጥፋቶችን ሰርተዋል”፡፡

ዑመር ሰውዬውን እየተመለከተ “ጥፋቶቼ ምን ምን ናቸው?” አለው፡፡

ሰውዬውም እንዲህ ዘረዘረለት፡፡ “አንደኛ አላህ የሌሎችን ነውር አትከታተሉ ብሏል፡፡ እርስዎ ግን ይህንን ቃል ጥሰው እኔ በድብቅ የምሰራውን አይተዋል፡፡ ሁለተኛ አላህ ወደ ሌሎች ሰዎች ቤት ስትገቡ የባለቤቶቹን ፈቃድ ጠይቁ ብሏል፡፡ እርስዎ ግን ያለኔ ፈቃድ ነው ወደ ቤቴ የገቡት፡፡ ሶስተኛ አላህ ወደቤት ስትገቡ በበር ግቡ ነው ያለው፡፡ እርስዎ ግን በመስኮት ነው የገቡት”፡፡

ዑመር ጥፋቱን አንድ በአንድ አመነ፡፡ እናም “ለጥፋቴ ማበሻ ምን ይሻላል ትላለህ ታዲያ?” በማለት ጠየቀው፡፡

ሰውዬውም “ለሁለታችንም ጥፋቶች ማበሻ የሚሆን መድኒት አላህ ተናግሯል፡፡ ይኸውም የጓዶቻችሁን ነውር ደብቁ የሚለው ነው፡፡ እኔም እርስዎ የሰሩትን ጥፋት ለማንም አልናገርም፡፡ እርስዎም የኔን ስካር ለማንም አይንገሩብኝ፡፡ ከአሁን ወዲያ ላልጠጣ በአላህ ስም ቃሌን እሰጣለሁ” አላቸው፡፡

ዑመር በሰካራሙ ሰውዬ ብልሃት በጣም ተንደቆ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ሰውዬው ሞቶ ይህንን ታሪክ ለተከታዮቹ ከማጫወቱ በፊት ለማንም ተናግሮት አያውቅም፡፡

የሰውን ነውር በመከታተል ሱስ የተለከፋችሁ ሰዎች ሆይ! እባካችሁ ተመከሩ፡፡ የሌላውን ነውር እከታተላሁ ብላችሁ ለራሳችሁ ኩንታል ሙሉ ሐጢአት እንዳትፈጽሙ፡፡

የሰውን ነውር ያያችሁ ሰዎች ሆይ! የጓዶቻችሁን ነውር አታውሩ! የባልንጀራችሁን ነውር ከደበቃችሁለት አላህ እናንተንም ከመጥፎው ሁሉ ይሰውራችኋል፡፡

—–

አፈንዲ ሙተቂ
ሰኔ 21/2005
ሀረር- ምስራቅ ኢትዮጵያ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. መስፍን says

    July 9, 2014 02:27 am at 2:27 am

    አፈንዲ ምን አይነት ፍልስፍና ለታስተምር እንደሆነ አልገባኝም ፣ ወሸታሙን ቀጣፊ ባለማለታችን ፣ባንዳውን አገሩን ለጥቅም የሸጠውን
    ባለማጋለጣችን ፣ ከጣሊያንና አሁን ደግሞ በእኛ እደሜ ያየነው ከሰማሌ ጋር በመሆን አገሩን የወጋውን ባለማሳወቃችን ህዝብ እንዲያቀው በለማደረጋችን ፣ይህው አሁን አገራችን የባንዶች መጫወቻ ሆናለች ።ማለት ያለብን በውሸት ሥም አለማጥፋት ፣የሰራን ማመስገን፣እህ ምንተባለ ብሎ ጠይቆ ያለተረጋገጠ ወሬ መንዛት፣መጥፎ መሆን መስበክ እንጂ እንዴት ነውር ይደበቅ በለህ ምሳሌ ታቀርባለህ? የህው እነታምራት
    ላይኔ የሰሩት ተረስቶ የጨበጨብላቸዋል ፣እነ ሰዬ? ! አንዳርጋቸውም የሄው በኤርትራ እርዳታ ነፃ ያወጣናል ብሎ አዳሜ ቴያትር የሰራል! ይህ ሁሉ ነውረኛን በመደበቃችን ነው ።

    Reply
    • shimon says

      July 11, 2014 10:17 am at 10:17 am

      “ረጅም እድሜ!

      Reply
  2. anwar says

    July 9, 2014 04:15 pm at 4:15 pm

    Mesfene I agree the lesson from the story is for people who are close to you or someone you know not to embarrass them in public basically don’t go around and be fault finder .but for the people you mentioned above of course we have to use all our means to fight them dictators and those who support them will never give you your rights .you have to take it. tnx by the way afendy good story I didn’t mean any harm

    Reply
  3. Amenen Gudaye says

    July 11, 2014 03:06 am at 3:06 am

    Mr Afendy if you have another please.

    Reply
  4. ቶቶ says

    August 10, 2014 02:48 pm at 2:48 pm

    እነደው ለመሆኑ ይሄን ታሪክ ከየት ይሆን ያገኙት ውድ ጸሃፊዬ? ነው ወይስ እስላም እንዲህ የሚራራ ነው ብለው ሊሉን ፈልገው ይሆን? ለመሆኑ በእስልምና መጠጥ፡ መጠጣት ከ8-14 ድረስ የሚሆን ግርፋት እንደሚያመጣ ሃዲቱ የተለያዩ ኡለማዎች እንደሚናገሩ ረስተውት ይሆን? ለማንኛውም እስላም ምን እንደሆነ የኢራቁ እስላማዊ እስቴት (ISIL) በተግባር እያሳየን ስለሆነ የእርሶ እስልምና እንደው የጥጥ ከረሜላውን አይነት መሰለ። ነው ወይንስ ከሰሞኑ በሊባኖስ እና በተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅ ያሉ አረብ አገራት በሮመዳን ጾም ጊዜ ምግብ ሲበሉ እንዳይታዩ (እስላም ያልሆኑትን) እንደውም ( Saudi warns non-Muslims on Ramadan fasting /http://www.upi.com/Business_News/Security-Industry/2005/10/01/Saudi-warns-non-Muslims-on-Ramadan-fasting/UPI-67841128194966/?rel=78121373377801) እንደው ቀልዶትን ቢያቆሙ ብዬ ነው

    Reply

Leave a Reply to መስፍን Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule