90ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማክበር ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለምዕተ ዓመት በተጠጋ ጉዞው የሀገርን ሉዓላዊነት ከማስከበር ባለፈ ለአፍሪካ ሀገራት የአየር ኃይል ምስረታ ያበረከተው ታሪካዊ አስተዋጽኦ በኩራት የሚታወስ ነው። በተለይም በ1960ዎቹ አጋማሽ አፍሪካውያን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለመውጣት በሚታገሉበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ለአህጉሪቱ ቀዳሚው እና ብቸኛው የሥልጠና ማዕከል ሆኖ ማገልገሉ የምንኮራበት የታሪካችን አንድ አካል ነው። በወቅቱ የአየር ኃይል ለማቋቋም ፍላጎት የነበራቸው ናይጄሪያ፣ ታንዛኒያ እና ኡጋንዳ የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች እና ቴክኒሻኖቻቸውን በአፍሪካ የተደራጀ ዘመናዊ አየር ኃይል ወደ ነበራት ወደ ኢትዮጵያ በመላክ እንዲሰለጥኑ አድርገዋል። እነዚህ ሰልጣኞችም ወደየመጡበት በመመለስ የየሀገራቸውን አየር ኃይል … [Read more...] about የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም
Ethiopian Air Force
የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ)
ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ሀገራቸው በጠላት ስትወረርና ሉዓላዊነታቸዉ ሲነካ ከያሉበት ተጠራርተው ዘር ፆታ ኃይማኖትና ባህል ሳይገድባቸው በየዘመናቱ የተነሱብንን ታሪካዊ ጠላቶቻችን በማይናወጥ ኅብረታቸው እንዲሁም ከአለት በጠነከረ ፅናት ሁሉንም እንደየ አመጣጣቸው መክተው ኢጥዮጵያችንን ዛሬ ላይ አድርሰዋታል፡፡ ታሪካችን ከምድር ሃይላችን አኩል በአየር ሃይላችንም ይለካል፡፡ በምስረታ ታሪኩ ከ95 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የአየር ክልላችንና የግዛት አንድነታችን በማስጠበቁ ረገድ በወርቅ ቀለም የተፃፈ ታላቅ ታሪክ ያለው በሀገሪቱ አንጋፋው የአቪዬሽን ተቋም ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያኖች በስርዓቶች መለዋወጥና የተረጋጋ መንግስት በየወቅቱ ካለመኖሩ ጋር ተያይዞ ከነበርንበት ከፍታ የቁልቁለት ጉዞ መውረዳችን ዛሬ በበለጠ ቁጭት ለተሻለ ስኬት እጅ ለእጅ ተያይዘን በጋራ … [Read more...] about የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ)


