የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤል ''የሰባ ገብዣ'' በሚል ርዕስ ስቅለት ዕለት ያቀረቡትን መልዕክት በተመለከተ እጅግ በርካታ ውግዘትና ፍረጃ ሲሰጥ እየተሰማ ነው። የሊቀ ጳጳሱን ስብዕና እና ማንነት ከማዋረድ ጀምሮ የሚሰጡት ስድብ አዘል “አስተያየቶች” ኢ-መንፈሳዊ፣ ጽንፈኛና አምባገነናዊ ናቸው። ገና ከጅምሩ በማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪና ብዙ ተከታይ አለን የሚሉ በሚሰጡ አስተያየት ሊቀ ጳጳሱን ከመዝለፍና ከማዋረድ አልፈው ግለሰባዊ ማንነታቸውን በማጉላት ሲሳደቡ ተሰምተዋል። እነዚህ “መምህራን” ብለው ራሳቸውን የሰየሙ ወይም ጥቂት ጊዜያት በቤተ ክርስቲያኗ የትምህርት ደጃፍ በማለፋቸው ብቻ “መምህር” ተብለው የሚጠሩ፤ በአቡኑ ላይ ለርካሽ የፖለቲካ መጠቀሚያ የሚውልና ከወንጌል አስተምህሮ የለቀቀ እጅግ ጸያፍ ንግግሮች በማሰማት ከሊቃውንቱ … [Read more...] about ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው

