• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ማክሰምና መሰንጠቅ – ባንዳና ባርነት

January 30, 2015 01:00 pm by Editor 2 Comments

ህወሃት በዘረፈውና በሚዘርፈው ሃብት ተጠቅሞ ለወዳጆቹ የሚያኮራ፣ ትውልድ ለሚላቸው የሚበጅ ተግባራት እያከናወነ እንደሆነ ይነግረናል፤ ይነግሩናል። ውስን ባለሥልጣናትና አበሮቻችው በሃብት ተመንድገዋል። በንዋይ ሰከረው የሚያደርጉት እስኪጠፋቸው ናጥጠዋል። የት ጋር አንደሚያበቃ ባይታወቅም፣ የተደሰቱ፣ የተከፉ፣ የተናቁ፣ የተሰረቁ፣ የሚሰረቁ፣ እየሰረቁ ያሉ፣ የተትረፈረፈላቸው፣ በስማቸው የሚነገድባቸው፣ ባሪያዎችና ባንዳዎች፣ ቀን የሚጠብቁ፣ ጥርሳቸውን የነከሱ፣ … ወዘተ “አብረው” አሉ፡፡

ዘመን፣ ወራትና ቀናት ቅዠትን በመሰሉበት ዓለም፣ ቁራሽ ለሚሞላው ከርስ ራሳቸውንና ማንነታቸውን፣ ከዚያም አልፎ የትም የማይደበቁትን ኅሊናቸውን ያቆሸሹ፣ የአገር “እንግዴ ልጆች” ወይም “ውርጃዎች” ለህወሃት የማከሰምና የመግደል ሴራ ተላላኪ ሆነው የህዝብን ክብር ሰልበው ረክሰው ያረከሳሉ። ከዚህም በላይ ነገ እንደ ውዳቂ ላንቲካ መጣላቸውን እያወቁ፣ አሽከርነት፣ ከሃዲነት፣ ውርደት፣ መለያቸው እንዲሆን መርጠው ተሳቅቀው ይኖራሉ። እነሱን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ባመነበት መንገድ እንዲጓዝ ለመታገል የሚውተረተሩትን ተኩላ ሆነው ያስበሏቸዋል።

ቅንጅትን በሉት። ቅንጅትን አሳረዱት። ተቀራመቱተ። የውስጥ ችግሩ እንዳለ ሆኖ እነርሱ ግን ዕጣ መድበው ተጣጣሉብት። አየለ ጫሚሶና ባልደረቦቻቸው “የክህደት ዋንጫ” ተሞላላቸው። ከዚያም ተጣሉ።

አሁን “ምርጫ” ደርሷል፤ ድንጋጤ ጨምሯል፤ የሕዝብ ሱናሚ አስፈርቷል፤ የህንጻውና የመንገዱ ሁኔታ አልበቃም፤ የሰዉ ህይወት ከመቅለሉ የተነሳ ለሚዛን አልበቃ ባለበት አገር ህይወቱ “በቀላል ባቡር ሊቀልል” ሽር ጉድ ይባላል፤ “ሥራ ላይ ነን፤ ምርጫ ደርሷላ”፤ አስተናጋጇ ህወሃት በለመደችው መንገድ ልታባብል ብዙ ትጥራለች፤ በየማዕዘኑም እያደባች ነው፤ እስከ “ምርጫ” ቤቷን አሳምራ ቄጠማ ጎዝጉዛ፣ ፈንዲሻ ነስንሳ፣ ዕጣኗን አጫጭሳ “እንኮምር” እያለች ነው፡፡ ግን አልበቃትም፤ አላመነችም፤ ተጠራጥራለች፤ ተጨንቃለች፤ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን በተለይም አንድነትን ለማጥፋት “ቡና ጠጡ” በማለት የሚላላኩላት የቦርዱ “ምሁራን” ላይ ታች እያሉ ነው። ኃላፊው ለምን ይህንን የተላላኪነት ሥራ እንደፈለጉት ባይታወቁም የቦርዱ አሽከርካሪ ምክትላቸው ግን “የዜግነት” ድርሻውን እየተወጣ ነው፡፡ “ለወገን ደራሹ ወገን” አይደል የሚባለው! ስለዚህ ህወሃት የሰፈረውን “የሚያገለማ ጽዋ” ለመጋት ርኩቻው ደርቷል። ፕሮፌሰርነት ከሚሰጠው ክብር ይልቅ “ተላላኪነት” ኩራት ሆነ!

ሶስት ዓይነት ባርነት

በአገራችን ሶስት ዓይነት ባርነት እንዳለ ይነገራል፡፡ የእነዚህ ባሪያዎች (ባንዶች) ማንነት ገፍቶ የሚወጣው “ምርጫ” በደረሰ ጊዜ ነው፡፡ አንደኛውና የመጀመሪያው ባሪያ “ምርጫ ቦርድ” የሚባለውና ሌሎች መሰል “የተቋም ባሮች” ናቸው፡፡ ሁለተኛው ባሪያ ምርጫ ቦርድን እና ተመሳሳይ ተቋማትን የሚመሩ አመራሮች ናቸው፡፡ ሦስተኞቹ ባሮች ደግሞ ህዝባቸውን ለንዋይ ሲሉ የሚሸጡ አገልጋዮች ናቸው፡፡ በሌላ ቋንቋ ህወሃት የጠፈጠፋቸው፣ ያቦካቸው፣ የሚነዳቸው፣ ሲፈልግ አዋርዶ የሚያባርራቸው ናቸው፡፡ የዘመንና የትውልድ ሁሉ ተጠያቂ ባንዳዎች!

ሰሞኑን ምርጫ ቦርድ የባርነቱን ዘመን ለማራዘም በለመደ እጁ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ላይ “አብዮታዊ ዴሞክራሲ” ጡጫ ለማሳረፍ፣ ለመሰንጠቅ፣ ለማክሰምና ለማፍረስ ደፋ ቀና እያለ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ቅንጅትን በማፍረስ ታማኝ ሎሌነቱን እንዳስመሰከረ ሁሉ አሁንም ለህዝብ የእንግዴ ልጅነቱን ለህወሃት/ኢህአዴግ ደግሞ ታማኝ አሽከርነቱን ለማረጋገጥ እየተባ ይገኛል፡፡

እኛም እንደ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የባንዳዎችን ጥርቅም እናወግዛለን፡፡ ታሪክና ትውልድም ይህንን እንዳይረሱት እናሳስባለን፤ እንመዘግባለን፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ የሚዘርፉትን፣ እየዘረፉ ያሉትን፣ የተዘረፉትን፣ እየተዘረፉ ያሉትን፣ ዘርፈው የሚያደርጉት የጠፋባቸውን፣ በሃብት የናወዙትን፣ በደም የተጨማለቁትን፣ የራባቸውን፣ ምርጫ ቦርድን፣ የኢህአዴግን ሎሌዎች፣ አሽከሮች፣ ሁሉ ይዛ እየነጎደች ነው፡፡ የጥጋቡም የግፉም ማብቂያ መቼ እንደሆነ ባይታወቅም የከፋቸውና ጥርሳቸውን የነከሱ እንዳሉ ከበቂ በላይ ማስረጃ አለን፡፡ ንጹህ አገር ወዳዶችና እኛም ጎልጉሎች ያንን ቀን አንናፍቀውም፡፡ ባንዶች ግን ይህንን ቀን የማስቀረት አቅም አላችሁና ወደ ኅሊናችሁ ተመለሱ፡፡ ህዝብ ይምረጣቸው ወይም ይጥላቸው አንድነትንም ሆነ ሌሎቹን የተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ከራሳቸው ችግር ጋር ለህዝብ ውሳኔ ብትተዋቸው ይሻል ነበር፡፡ ነገርግን ውሻ ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ እናንተም ዳግመኛ ባንዳነታችሁን አስመሰከራችሁ፤ ባርነታችሁንም ቀጠላችሁበት፡፡


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. helen geta says

    January 30, 2015 03:41 pm at 3:41 pm

    የኢት/ያ ህዝብ የሚፈልገው ከድህነት የሚያወጣው ኑሮውን የሚያሻሽልለት መንግስት ነው የሚፈልገው።እነሱም ይደጉ ሁሉም ይደግ ነገር ግን ወያኔ ብቻ አይደለም እየዘረፈ ያለው በሁሉም ክልል ካዲሪ የተባለ በሙሉ እየዘረፉ ነው።መቃወም ያለብን ፓሊሲው ላይ ነው።የማይጠቅም ዘረኝነት የተሞላ በመሆኑ፡ማንንም አይጠቅምም።

    Reply
  2. Tena says

    February 2, 2015 02:10 pm at 2:10 pm

    Leming anchim kililch hedesh atzerfim? Yeleloch bher bhereseboch hager mebezbez diro qere. Siamrbsh yqeral.
    Zeregnoch melisewu yezeregninet selabwochn zeregna silu yamal! Le’Ethiopia bhereseboch zarem bihon yeteleyaye yezeregn’net sim auchiwu man honena? amarawu aydel?

    Reply

Leave a Reply to helen geta Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ May 16, 2022 03:07 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule