• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደቡብ ሱዳን – የሰላም ድርድር ወይስ ቁማር?

May 13, 2014 11:23 am by Editor 3 Comments

የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ስምምነቱን የማይፈርሙ ከሆነ ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ለዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት (ICC) አሳልፈው እንደሚሰጧቸው መግለጻቸውን በጁባ የጎልጉል ምንጭ አስታወቁ፡፡ ሱዳን ትሪቢዩን በበኩሉ ስምምነቱ የማይፈረም ከሆነ እስር እንደሚጠብቃቸው ሃይለማርያም ለሳልቫ ኪር መናገራቸውን ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ አርብ የተፈጸመው የስምምነት ፊርማ ገና ሳይደርቅ ሁለቱም ኃይላት ወደ እርስበርስ ውጊያው ተመልሰው በመግባት እየተካሰሱ ነው፡፡

እጅግ ደም አፋሳሽ በሆነውና ለበርካታ ዜጎች መፈናቀል ምክንያት የሆነው የደቡብ ሱዳን የእርስበርስ ጦርነት ከጥቂት ቀናት በፊት አዲስ አበባ ላይ በፊርማ ሲጸድቅ ብዙ ተስፋ የተጣለበት ነበር፡፡ ሆኖም ስምምነቱ ከተጽዕኖ ባለፈ መልኩ በዕለቱ በፊርማ ካልጸደቀ ሳልቫ ኪርንም ሆነ ሬክ ማቻርን ሃይለማርያም ደሳለኝ ለዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት አሳልፈው እንደሚሰጧቸው የተነገራቸው መሆኑን የጎልጉል ምንጭ ከጁባ አስረድተዋል፡፡ ሳልቫ ኪር ወደ ጁባ ከተመለሱ በኋላ ከካቢኔያቸውና ቅርብ አማካሪዎቻቸው ጋር በተነጋገሩ ወቅት በስምምነቱ ወቅት የነበረውን ሁኔታ ባስረዱበት ወቅት መናገራቸውን የመረጃው አቀባይ ለጎልጉል አስታውቀዋል፡፡ ሁኔታው ለደቡብ ሱዳን እጅግ አሳፋሪ ከመሆኑ የተነሳ ደቡብ ሱዳን አምባሳደሯን ከኢትዮጵያ እስከማስወጣት እንዳሳሰባት ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡

በበርካታ ወንጀሎች የሚጠየቁት ኪርና ማቻር ማስፈራራሪያውን በቀላሉ እንደማይመለከቱት መገመት የሚቻል ሲሆን በሌላ በኩል ኢህአዴግ ወንጀል በመሥራትና በማሰራት አገር ውስጥ የለመደውን የማጠልሸት ዘዴ በጎረቤት አገሮችም ላይ በመጠቀም የበላይነቱን መግለጹ ስምምነቱን “የሰላም ድርድር ወይስ ቁማር?” ተብሎ እንዲጠየቅ የሚያስገድድ መሆኑን አንዳንድ ወገኖች ያስረዳሉ፡፡

ሱዳን ትሪቢዩን በበኩሉ ሳልቫ ኪርን ጠቅሶ እንደዘገበው ስምምነቱ በማስፈራራትና በተጽዕኖ የተካሄደ መሆኑን ዘግቧል፡፡ “ጠ/ሚ/ሩ ለሬክ ሲነግረው ስምምነቱን ዛሬ ሳትፈርሙ ከዚህ አትወጡም ብሎት ነበር ለእኔ ደግሞ ሰነዱን ካልፈረምክ አስርሃለሁ” በማለት አስፈራርተዋቸው እንደነበር ሳልቫ ኪር መናገራቸውን ዘግቧል፡፡ ሳልቫ ኪር ከሬክ ማቻር ጋር ፊት ለፊት ተገናኝተው ምንም ዓይነት ውይይት ሳያደርጉ ለፊርማ ብቻ መተያየታቸውንም ተናግረዋል፡፡ssudan1

የሃይለማርያም ደሳለኝ እውነተኛ ባለሥልጣንነትና ተጽዕኖ አድራጊነት የታየበት ይህ ስምምነት በኢህአዴግ ውስጥ በምን ዓይነት መልኩ እንደሚቀጥል የሚያወያይ እንደሆነ አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡ አስተያየቱን ከሰጡ መካከል እንዳሉት “ሃይለማርያም ይህንን ማስፈራሪያ ሲሰጡ በአጠገባቸው የነበሩት የህወሃት ባለሥልጣናት እነማን ይሆኑ በማለት በዓይነ ልቦናዬ ሳስብ ነበር፡፡ እነ በረከት፣ ደብረጽዮን፣ … ሳልኳቸው” የሚሉት አስተያየት ሰጪ ሲቀጥሉ “ጠ/ሚ/ሩ በነካ እጃቸው የሕዝብን ድምጽ የሚያፍኑትን፣ ኦሮሞውን በየቦታው እየገደሉ ደሙን የሚጠጡትን፣ አማራውን ለዘመናት ከኖረበት እያፈናቀሉ መሄጃ ያሳጡትን፣ አኙዋኮችን ያረዱትን፣ ኦጋዴኖችን ያጋዩትን፣ ተናገራችሁ፣ ጻፋችሁ በማለት እስርቤት እስኪጠብ ሃሳቡ የገለጸውን ሁሉ ለስቃይና ስደት የዳረጉትን፣ … ወንጀለኞች እንዲሁ ግፋችሁን ካላቆማችሁ ቃሊቲ ወይም ዝዋይ ወይም … እወረውርሃለሁ ብለው አንዴ እንኳን በማስፈራራት ጠ/ሚ/ር መሆናቸውን ቢያሳዩን ብዬ ተመኘሁ” ብለዋል፡፡

በተጽዕኖና ማስፈራሪያ የተፈረመው የደቡብ ሱዳን ስምምነት ፊርማ ገና ሳደርቅ ሁለቱም ወገኖች ተኩስ አቁሙን ጥሰው ፍልሚያቸውን ቀጥለዋል፡፡ እርስበርስም እየተካሰሱ ይገኛሉ፡፡ እሁድ ዕለት የሳልቫ ኪር ኃይሎች በከባድ መሣሪያ የታገዘ የምድር ጥቃት እንደሰነዘሩባቸው የማቻር ኃይሎች ይናገራሉ፡፡ የኪር መንግሥት በበኩሉ ማቻር ስምምነቱን ላለመፈረም በመፈለግ ተቃውሞ ሲያሰማ የነበረ ነው በማለት ዶ/ር ሬክ ማቻርን ይከስሳሉ፡፡

ማቆሚያ የሌለው የሚመስለውና እስካሁን በሺዎች የሚቀቆጠር ህይወትን የቀጠፈውና ለ1.2 ሚሊዮን ዜጎች መፈናቀል ምክንያት የሆነው ጦርነት ወደ ሰላም የመድረሱ ምኞት እየራቀ የሄደ ይመስላል፡፡ ኢህአዴግ ማስፈራሪያ፣ ዛቻ፣ ቁማር፣ … ቢጠቀምም ህልሙ ቅዠት ሆኖበታል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. ፋአድ says

    May 13, 2014 12:02 pm at 12:02 pm

    በመሰረቱ የምስራቅ አፍሪካ አገር መሪዎች ከሀገር መውደምና ከሰው ልጅ ህይወት መጥፋት ይልቅ የሚያስጨንቃቸው የያዙትን ስልጣን መለቀቅ ነው
    በመሆኑም ሁሉንም ብንል ይቀላል /ኬንያ ብቻ ስተቀር / ስልጣን ለህዝቡ እንዲሆን ሊያደርጉት ይቅርና አያስቡትም
    እንደተባለውም ኢህአዴግ አዲስ ፎርሙላ ጀመረ ማለት ነው የሀገር ውስጡ ትግል እየከረረ ሲመጣ ለዓለም ዓቀፍ መንግስታት አፍ ማስያዣ ነው። ቢሆንም የሀገር ውሰጥ ትግል የሚያመጣው ውጤት ታይቶ የኢህአዴግም አንባገነኖችን ፍርዳቸው የሚያገኙ ይሆናሉ

    Reply
  2. aradaw says

    May 15, 2014 12:34 am at 12:34 am

    ከሆነ ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ለዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት (ICC) አሳልፈው እንደሚሰጧቸው መግለጻቸውን በጁባ የጎልጉል ምንጭ አስታወቁ፡፡

    How irony is this. Yesterday the TPLF ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም and the Woyane government openly saying that they do not accept ICC and they showed their support to Uhuru Kenyatta and Beshir. Here today the confused ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም is recognizing ICC and willing to hand over ኪርና ማቻር to ICC.

    Reply
  3. በለው ! says

    May 16, 2014 05:15 am at 5:15 am

    >>>እንቡሼ ገላ…የፊርማ ገለባ..
    ሰላም ነው ብለው ተነፍቶ ጡሩንባ
    በልተው ጠጥተው ተዘምሮ ተጨፍሮላቸው
    የእንባይ ካብ ጦርነት ላይ መዋላቸው!?
    ፊርማ ፈርሞ አገሩ ሲደርስ
    ኀይሌን ለማስከፋት መክሰስ !?
    እረ በስንቱ እንወቃቀስ?
    ስንት አለ የቤታችን ጉድፍ የሚነቀስ!?
    …”Kiir immediately denounced the deal, claiming that he was coerced into signing it through threats from the Ethiopian prime minister. “[Ethiopian PM Hailemariam Dessalegn] told me that ‘if you don’t sign this, I will arrest you here’,” !! *** ኀይለመለስ አይልም! አያደርገውም!የነፍስ አባቱ ማን ሆነና..ዘመኑ ሰጥቶ መቀበል እኮ ነው፡፡ እነሱ ካልበሉ ኀይሌ አያገሳም!ለመሆኑ ሰልቫ ኪር ቢታሰር ምን ይሆናል? ኢህአዴግ ዓለም በቃኝ ዘግቶ ኢትዮጵያ በቃችኝ ከፍቷል ጭራሽ ቃሊቲም ሆነ ቂልንጦ ከሲዊዲን ጋዜጠኞች የነጭ ደም በተለይ የደማቅ ጥቁር ደም አሰረች ተብላ ትደነቅ ነበር። ኢህአዴግ በአፍሪካ ከፍተኛ የፖለቲካ ተምሳሌነቱን ለማረጋገጥ በፋውንዴሽኑ ብዙ አህትና ወንድም ፓርቲ መሪዎችና ካድሬ ቤተሰቦች የምርምር ጥናት ማዕከል እየመጡ እንደሚሰለጥኑ ተነግሮን ነበር። ክፍል አንድ፦ቃል ማፍረስ! አህአዴግ ስንት ግዜ ቃሉን አጥፏል?ለምሳሌ፤ የምርጫ ሥርዓት ህጉን ተፈረመና ምን ተገኘ?00 ከተቃዋሚ አጋር..አጃቢና..አዳናቂ..ፓርቲዎች ሆኑ ምን አተረፉ?

    **…” Kiir said before a crowd at Juba International Airport. “I said ‘if you arrest me in this good place, I am sure I will get good food. So there will be no need to return to Juba. You will feed me for free here.’”አዎን ምን ጠፍቶ!?እንኳን መጥታችሁልን እቤታችሁ ድረስ አምጥተን እናበላችኋለን አደለምን!? ግን ይህ የቀጠናው ጥልቅ ብዬነታችን እሰከመቼ ነው? “የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች” አሉ። ግን ይህ አስገድዶ መሬት መንጠቅና አስገድዶ ማስፈረም ለመደብን ወይስ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ልማታዊ የሙስና መር ፖለቲካ ባሕል ይሆን!? ኢህአዴግ ለሱማሊያ ያወጣውን የሰው ኀይል ለሱዳን ሰላምና የተቀናቃኝ ፓርቲ ድርድር የከፈለውን መስዋትነት ለምን ለሀገር ውስጥ ‘ተፎካካሪና ተወዳዳሪ’ ፖለቲካ ፓርቲዎች የሰላም ድርድር ላይ ተግቶ መስራት ተሳነው!? ትርፋማነት የለውም ማለት ነው? ለደቡብ ሱዳን መጨነቅ የነበረባቸው የነዳጁ ባለቤቶች አውሮፓውያንና ካናዳውያን መሆን አልነበረባቸውም? ምን አልባት ኢህአዴግ ንብረት ኣስጠባቂ ሆኖ ሥልጣኑን እንዲጠብቁለት መማፀኛ(አጅ መንሻ) ይሆን? ለማናቸውም ሲልቫ ኪር ጎረቤት፣ ወዳጅ፣ ተቃዋሚን ጠባቂ ብቻ ሳይሆን ከባለሥልጣን ቤተሰብ ጋብቻም ነውና ኅይሌ ጠንቀቅ…እየተስተዋለ ይች በፓርላማ የለመደች እጅ ማወናጨፍና ደማቅ ጩኽት ውጭ ትወጣና መግቢያ እንዳይጠፋ ዋ በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule