• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሕዝባቸው ጋር ሊገናኙ ይገባል!

August 18, 2018 12:49 am by Editor 4 Comments

ወደ ሥልጣን ከመጡ ጀምሮ በተደጋጋሚ ከሕዝብ ጋር ቀጥተኛ ሲያደርጉ የነበሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሕዝባቸው ጋር ግንኙነት ሳያደርጉ ሁለት ሳምንታት አልፈዋል። ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተለው ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የጠ/ሚ/ሩ ደጋፊዎችና መላው ሕዝባችን ሁኔታውን እንዲያውቅና አስፈላጊውን ውሳኔ እንዲወስድ ይፋ ለማድረግ ተገድዷል። በእርግጥ ዶ/ር ዐቢይ በተቀነባበረ በሚመስል ስልት ሁለት ሦስት ጊዜ ያህል ለሕዝብ ዕይታ ቀርበዋል። ሆኖም ከወትሮው በተለየ መልኩ ለውጡን አጥብቀው የሚቃወሙና ለማክሸፍ የሚፈልጉ ኃይሎች ያቀነባበሩት በሚመስል የተከናወነው ከሚዲያ ፍጆታ የማያልፍና በጥያቄ ውስጥ ያለውን ሕዝብ ለማርገብ የተሰራ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ሆኖ ነው ያገኘነው። ስለዚህ ሕዝባችን መሪውን የማግኘትና የማነጋገር መብቱ ሊነፈግ አይገባም፤ ይህም ባጭር ጊዜ ውስጥ በጋዜጣዊ መግለጫም ሆነ በፊት ሲደረግ እንደነበረው ዓይነት የውይይት መድረክ መገለጽ ይገባዋል በማለት አኢጋን አቋሙን በግልጽ ያስታውቃል።

ከዚህ በፊት “የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ በየሰዓቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መገለጽ አለበት፤ ከእንግዲህ በኋላ በኢትዮጵያ የድብቅ ፖለቲካ አበቃ፤ …. የእኔ ሥራ የኢትዮጵያን ሕዝብ ፍላጎት … ማስፈጸም ብቻ ነው” የሚል ቃል የገቡልን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም የመደበቅ እና የመሸረብ ፖለቲካ ማብቃቱን ያበሰሩልን መሪያችን ሕዝብ እንዲህ ተጨንቆና ባገሩ ላይ የመኖር ኅልውናው አደጋ ላይ ወድቆ ባለበት ወቅት ከሕዝባቸው ጋር እንደበፊቱ እንዳይነጋገሩ የገደባቸው ኃይል ምንድነው? የጉራጌና የቀቤና ሕዝብ በተጋጨበት ወቅት በፍቅር ተግሳጽ ታረቁ ብለው መክረው ወዲያው ያስማሙ ብልሃተኛ ከሕዝባቸው ጋር እንዳይመክሩ የኅሊና እስረኛ ያደረጋቸው ማነው? ተስፋ በሚሰጠውና የወደፊቱን ብሩህ አድርጎ በሚያሳየው አንደበተ ርዕቱነታቸው ሕዝባቸውን እንዳያረጋጉ አጣብቂኝ ውስጥ የከተታቸው ጉዳይ ምንድነው? ይህንን የሕዝብ ጥያቄ የጋራ ንቅናቄያችን ሕዝብ እንዲያውቀው ይፋ ለማድረግ ተገድዷል።

እጅግ በርካታ የሰቆቃና የመከራ ዓመታትን ያሳለፈው የአገራችን ሕዝብ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና እርሳቸው በሚመሩት ቡድን አማካኝነት ያገኘው ለውጥ ጥቂት ከሚባሉ ቡድኖችና ግለሰቦች በስተቀር በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኘውን ኢትዮጵያዊ ያልጠበቀውን ተስፋ ያጎናጸፈው ነው። በአገራችን ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ አሠራር እያስተዳደሩን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በየጊዜው ባለማቋረጥ ለሕዝባችን የሰጡት ተስፋና ባጭር ጊዜ ውስጥ የፈጸሟቸው ተግባራት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ቀንድ በሚገኙትም አገራት ታስቦ የማታወቅ ለውጥ ያመጣ ነው።

ሆኖም ግን ዶ/ር ዐቢይ የአሜሪካ ጉብኝታቸውን አጠናቅቀው ወደ አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ ሁኔታዎች ተለዋውጠዋል፤ እርሳቸውም እንደቀድሞው ከሕዝባቸው ጋር የሚደርጉትን ግንኙነት በእጅጉ ቀንሰዋል። በእርግጥ ዕረፍት ዐልባ በነበረው የአሜሪካው ጉብኝታቸውና ከዚያ በፊት በነበሯቸው ጊዜያት ያለበቂ ዕረፍት መሥራታቸው፤ በጤናቸው ላይ መቃወስ ሊያስከትል እንደሚችል ማንም መገመት ይችላል። ሆኖም ዝምታቸውን ተከትሎ የወጡ ሕዝብን የሚረብሹና የለውጡ ተቃዋሚዎችን የሚያበረታቱ ዘገባዎች ሊወገዙ የሚገባቸው ናቸው። ጊዜያዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅምን ከማሰብ በፊት እንደ ሚዲያ የአገርን ኅልውና፣ የጠላትን አካሄድ፣ የሕዝብን ጥቅም ማስቀደም ተገቢ ነውና የጋራ ንቅናቄያችን በዚህ ላይ ትኩረት እንዲደረግበት ያሳስባል፤ ሕዝባችንም ምርቱን ከግርዱ እየለየ መረጃ የመቀበል ባሕሉን በማዳበር ለእንደዚህ ዓይነት ዘገባዎች ዕውቅና መንፈግ ይገባዋል። ጸረለውጥ የሆኑ ዘገባዎችንም እንዲሁ ዓላማቸውን አውቆ በመልሶ ማጥቃት ሊቃወማቸው ይገባል።

ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ወደአገር ከተመለሱ ሁለተኛ ሳምንት አልፏቸዋል። በእነዚህ ሳምንታት ውስጥ በርካታ የሚረብሹና የሚያስጨንቁ ሁነቶች ተከስተዋል። ለአብነት ያህል፤ እርሳቸው በወጡ በማግስቱ በግፍ ከተገደሉት ስመኘው በቀለ (ኢንጂነር) በኋላ በርካታ አለመረጋጋቶች በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች ታይተዋል። አሁን እየተረጋጋ ነው በሚባልበት የሶማሊ ክልል በርካታዎች ከመገደላቸውና ከቀያቸው ከመፈናቀላቸው ባሻገር እጅግ ባልተለመደ ሁኔታ እስከ 10 የሚደርሱ አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል፤ ካህናት ተገድለዋል፤ ሻሸመኔ ላይ በሐሰት በተሰራጨ ወሬ አንድ ወገናችን ላይ በቃላት ለመግለጽ የማይቻል አሰቃቂ ተግባር ተፈጽሞበታል፤ በምስራቅ ኢትዮጵያ አካባቢ ከሶማሊ ክልል ከተከሰተው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘና በሌሎች ሰበቦች በርካታ ወገኖች ከቤታቸው እየተፈናቀሉ ነው፤ ቤት ንብረታቸው እየወደመ ነው፤ ሕይወታቻውን ለማዳን የለበሱትንና ልጆቻቸውን ብቻ ይዘው እየሸሹ ነው፤ ከጅጅጋ አካባቢ ተፈናቅለው ሕይወታቸውን አትርፈው አዳማ (ናዝሬት) የደረሱ ወገኖች እዚያም እየተገደሉና መግቢያ እንዲያጡ እየተደረጉ ነው፤ የኢትዮጵያ ሶማሊ ተወላጅ ያልሆኑ በድሬዳዋና አካባቢው የሚገኙና ከጅጅጋ ተሰደው የመጡ በሶማሊ ልዩ ፖሊስና በሄጎዎች ጥቃት ተሰንዝሮባቸው ህጻናት ሳይቀሩ ተገድለዋል፤ ቤ/ክ የተጠለሉ እርጉዞችንና እመጫቶችን ጨምሮ በርካታዎች ከዚያ እንዳይወጡ ተደርገው ምግብና ውሃ በማጣት ስቃይ ተዳርገው ከቆዩ በኋላ ስቃዩ በዝቶባቸው ለልጆቻቸው ውሃ ለማጠጣት የወጡ እናቶች ተገድለዋል፤ የተጠለሉበትም ቤ/ክንም ተቃጥሏል፤ በጅጅጋ የነበረው የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ቅርንጫፍ ጽ/ቤትም ጥቃት ደርሶበት መረጃዎችና ሰነዶቹ ከነኮምፒውተሮቹ ተዘርፈዋል፤ ጽ/ቤቱም ወድሟል፤ በጅቡቲ በሰላም ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን የጥቃት ሰለባ ሆነው 30ሺህ የሚሆኑ ወገኖቻችን ከጅቡቲ ለቅቀው ወጥተው በውሃ ጥምና በምግብ ማጣት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በቴፒ ከተማ በተፈጠረ ሁከትና እስካሁን ባላቆመ ጥቃት ወገኖች እየተገደሉ ነው፤ የጌዲኦን ተፈናቃዮች ጨምሮ በአሁኑ ጊዜ በአገራችን ውስጥ በተፈጠረ አለመረጋጋት በሰላም ከሚኖሩበት ቀዬ የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከሁለት ሚሊዮን በላይ ደርሷል።

በምስራቁ የአገራችን ክፍል እየደረሰ ያለውን በተመለከተ መንግሥት ሁኔታዎች እየረገቡ ነው ቢልም ዋንኛ የጥፋት ኃይል የሆነውን የሶማሊ ልዩ ፖሊስን ትጥቅ ስለማስፈታት የሚነገር አለመኖሩ “ለምን?” የሚል ጥያቄ እንድናነሳ የሚያደርገን ሆኗል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ይህ ሁሉ ሲሆን የእናቶችን እንባ በተግባር ሲጠርጉና ለወገናቸው ደም ሲለግሱ በገሃድ የታዩት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ዝምታ መምረጣቸው የእርሳቸው ባህርይ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። “ልሞትልህ የተዘጋጀሁ ነኝ” ያሉት ሕዝባቸው “ወዴት እየሄድን ነው? አገራችንስ ወዴት እየሄደች ነው?” የሚሉ በርካታ ጥያቄዎች ተወጥሮ ባለበት ሁኔታ (ለሁሉም ነገር እርሳቸው እየተጠየቁ መልስ መስጠት አለባቸው ባንልም) በአስገዳጅ አጣብቂኝ ውስጥ ካልገቡ በስተቀር ሕዝባቸውን ዝም ሊሉት እንደማይችሉ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያምናል። ለጋራ ንቅናቄያችን ከሚደርሱን መረጃዎች በመነሳት ይህንን እምነት ሕዝባችንም ይጋራል ብለን እናምናለን።

ስለዚህ እነዚህንና ከላይ ያነሳናቸውን ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ቀላሉ መንገድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአገራችንን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክተው የአገር ውስጥና የውጪ ጋዜጠኞችን ሰብስበው ያልተገደበ ነጻ መገለጫ መስጠት ይገባቸዋል እንላለን። ከሕዝቡ ጋር አንዳንድ ጊዜ በቀን ከሁለት ጊዜ በላይ ሲገናኝ የቆየ መሪ ኮሪደር ላይ በማነጋገርና ቪዲዮ በመልቀቅ  ወይም ሕዝብ መግቢያ መውጫ አጥቶ በተጨነቀበት ጊዜ ከቡና ላኪዎች ጋር ተገናኘ ብሎ ዜና በመሥራት “ደኅንነቱን” ማሳየት የዶ/ር ዐቢይን ባህርይ የሚገልጽ አይደለም፤ ማንም ሊቀበለው የማይችል ጊዜ መግዣ ነው።

ስለዚህ ይህንን የሕዝብ ጭንቀት ከላይ በጠቀስነውና ባልተገደበ መልኩ በቀጣይ ጥቂት ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ፤ ሕዝብና መሪው እንደቀድሞው እንዲገናኝ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያሳስባል።

ፈጣሪ የአገራችንን ሰላም ያጽናልን፤ ሕዝቧንም ይባርክ።

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)


ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በአሜሪካ አገር በሕግ የተመዘገበ ድርጅት ሲሆን በትርፍ አልባ የሲቪክ ድርጅትነት በ501(c)(3) ምደባ ሥር የተካተተ ነው። ለተጨማሪ መረጃ የአኢጋን ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በስልክ ቁጥር፤ 202-725-1616 ወይም በኢሜል፤ obang@solidaritymovement.org ማግኘት ይቻላል።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: abiy ahmed, Full Width Top, Middle Column, SMNE

Reader Interactions

Comments

  1. Abe says

    August 19, 2018 09:58 pm at 9:58 pm

    Dr . Abiy’s absence from direct public appearance for more than three weeks and some limited media pictures of him to show he still on power (media show off) put a lot of Ethiopians in doubt. I strongly assume and feel some changes are going on in the palace since he came back from USA. It looks like he is leading the country under pressure and control of some external force. All Ethiopians must ask and continuously push for him to go out and respond to direct media interview. Otherwise, its a matter of time before things go in unexpected direction and his team’s favorable change will face set backs.

    Reply
  2. Abe says

    August 20, 2018 01:24 am at 1:24 am

    What professor Mesfin had said about the Ethiopian people getting out in mass for demonstration when announced to come out and sitting back inactively after that, waiting from others to bring the needed change seems happening now. Activists, media personnel and all other concerned citizens have to demand and push to know what is going on now in the Arat Killo palace and take initiative to mobilize all Ethiopians for the likely upcoming power and public confrontation. Everybody should request actively for Dr Abiy to come out and take questions, interviews and publicly announce his status. Otherwise, people must organize and come out for struggle-demonstration, disobedience and other form of opposition before its too late to reverse course. The Arat Killo situation does not seem good now and every movement and observation indicates that.

    Reply
  3. Alem says

    August 20, 2018 04:00 am at 4:00 am

    Imagine the time and organization it takes to
    always appear before the public. Remember
    Dr. Abiy is not superhuman. He needs
    pace himself in his activities. Moreover,
    needs to fulfill his duties as prime minister.
    Tigray Front has declared all-out media war
    attempting to create distance with the
    public. It will not succeed.
    One that needs to happen is
    journalists to check before publishing a story.

    Reply
  4. sergute selassie says

    August 20, 2018 07:16 pm at 7:16 pm

    ጤና ይስጥልጥኝ ዶር ኦባንግ ኢትዮጵያ ሜቶ እንዴት ሰነበትክ? እባክህን ጠንከረህ ታገል።፡ እኔማ ከተጀመረ ጀምሮ ብዙ ጻፍኩኝ በብሎጌ Kenebete በቀንበጥ ህልምም ወንበሩ ባዶ ሆኖዎ ስለዬሁኝ ምንም ጥርጣሬ አልነበረብኝ ኢትዮጵያ ከገቡ ጀምሮ ማለት እችላለሁኝ፤ በዬዕለቱ እጽፋለሁኝ ከነማገነዛቢያ ጭብጦቹ። ወጥተው ይናገሩ ቢባል እንኳን ያው መሰሉ ፌክ ነገር ነው የሚደራረበው። ከተቻለ የካናዳ ኢትዮጵውያን ከነቤተሰባቸው ግብዣ ቢያደርጉላቸው ያን ጊዜ ጉዱ ይታያል። አሁን በወያኔ ሃርነት የበላይነት ቁጥጥር ሥር ናቸው። መሪው ደግሞ አቶ በረከት ስምዖን ናቸው። ደስ ያለኝ ነገር አንተ ይሄን ማመንህ እና ይሆናል ብላችሁ በድርጅታችሁ መወሰናችሁ ነው። ይህ ግን በቂ አይደለም አዌርነሱ ለምታውቃቸው የምዕራባውያን አገሮች ሁሉ ተከታታይ በሆነ ሁኔታ ማሰወቅ ያስፈልጋል። “action is everything” እኔ እንዲያውም ከመደበኛ ቤታቸውም ያወጧቸው ነው የሚመስለኝ። ሲፈልጉቸው ብቻ ነው ከረባት እና ገበርዲን የሚያለብሷቸው። በተረፈ ተባረኩ!
    ነፃነት ለአብይ እና ለቤተሰቡ!
    ቸር ወሬ ያሰማን። አሜን!

    Reply

Leave a Reply to sergute selassie Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule