• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ

November 7, 2014 08:12 pm by Editor 1 Comment

ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡

በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ (ምንጭ እና ፎቶ: ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 7, 2014 11:10 pm at 11:10 pm

    አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል ተከሰሰ:
    “ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ ለሕዝብ በሰጠው በራሪ ወረቀቱ ላይ፡_
    * የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣!
    *መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣!
    * በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆም!
    *መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ!
    የሚመክሩ ሀሳቦችንና የማህበሩን አላማና ለህዝብ ሲያስተዋወቅ ነው።አራት ነጥብ።
    *******************!
    ***መንግስት ያሠረው በበራሪ ወረቀቱ ላይ ያለውን ፈፅሜአለሁ ምንአገባህ ብሎ ነው?
    ***በሕገመንግስቱ ይህ ለገዢው ፓርቲ ብቻ ይፈቀዳል ብሎ ነው?
    ***ይህንን ድርጊቴን ህዝብ የመቀበል ግዴታ አለበት ብሎ ነውን?
    ***ሕዝቡ እየተሰደበ እየተረገጠ በትናንሽ ጥቅማጥቅም ተይዞ ይኖራልና ችግሩን አትንገረው ብሎ ይሆን?
    ***ይህ ሌላ አማራጭ የሌለው ሕዝብ በሙሉ ፍቃደኛነት ሊረገጥ ተስማምቷል ብሎ ነው?
    *** ለእኛ በእኛ ሰው የሆነ ያለእኛ ምንም የማይሆን ግን ተበታትኖ የሚጠፋ ነው ብሎ ተማምኖ ይሆን?
    *** በፈጣንና አሳላጭ መንገድ በቅፅበት የሚያድገው ከሕዝብ በላይ ከመንግስት በታች የሆነው ቡድን ይሆን?
    ***የነጭ ባነዲራ ትርጓሜ ያልገባቸው ብጥብጥ ወዳድ(እነጭር ሲል አንወድም ይሆኑ?)
    *** ይህ ጭፍን ደጋፊ(ተደጋፊ)…ጭፍን ተቃዋሚ(አቋቋሚ) ዕርቅ ሰላም አንድንት ኀብረት ያቃዣቸው ይሆኑ?
    ***በእርግጥም አውራው ገዢ ፓርቲ ተራራ ውጡና፣ ገደል አቋርጡና ጉልበቴን ፈትሹ ብሎ እየገፋ ይሆን?
    *** መንቀሳቀስ፣ መዘዋወር፣ መሰለፍ፣ መሰብሰብ፣ በከልልና በክልከላ ከተለወጠ ዜግነት ቀርቶ በሊዝ መኖር ተጀመረ?
    ***በውስጥ የብሔርና ቋንቋ ብጥብጥ የቡድን መናቆር ትርፋማ የሆኑ ተደራጅተው አቆብቁበው እየጠበቁ ይሆን?
    “ማንም ሰው በፖለቲካ አመለካከቱ አልታሰረም! ሊታሰርም አይገባም!ኢህአዴግ ከስሕተቱ ይማራል! ከተባለ..የሰላም ማኅበር ማቋቋምና የህዝብ ብሶትን ለመንግስት ማሳወቅ በየትኛው ሕግና ሰንደቅ ወንጀለኛ ያደርግ ይሆን?
    _____ለመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ መከላከያ ለሕዝብ፣ ለሀገር ሉዓላዊነት ከቆመ ይህንን የተበላሸ(የበሰበሰ) ሥርዓት መምከር ወይንም የከፋ ውጥንቅጥ ውስጥ ከመግባታችን በፊት ማንአለብኝነት፣ የህዝብ ንቀት፣አምባገነን፣ የወሮ-በላ ቡድን እንዲወገድ አስተዳደሩን በሠላም ተረክቦ ለፍትሀዊ አስተዳዳር ማስረከብ ሀገራዊ ቃለ-መሐላ ግዴታ የገባበት፣ ኀላፊነትም የወሰደበት ለግለሰብና ለፖለቲካ ፓርቲ ዕድገት፣ ብልፅግና ሳይሆን ለሕዝብ ሠላምና ደህንነት መሆኑን አይዘንጋ!። ሠላም ለሁሉም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule