• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሰላም ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ ታሰረ

November 7, 2014 08:12 pm by Editor 1 Comment

ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማስተባበርና በማቀራረብ እርቅ ለማስፈን እንደሚንቀሳቀስ የሚነገርለት የመግባባት፣ አንድነትና ሰላም (ሰላም) ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ፋንታሁን ብርሃኑ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አቶ ፋንታሁን የታሰረው ‹‹የሰላም ጥሪ›› በሚል ነጭ ሰንደቅ አላማ በማውረብለብና የማህበሩን አላማ የሚገልጹ፣ እንዲሁም ማህበሩ በአሁኑ ወቅት ለአገሪቱ ችግር የሚላቸውን ጉዳዮች በዝርዝር የያዘ በራሪ ወረቀት ለህዝብ በመበተን ማህበሩን በማስተዋወቅ ላይ በነበረበት ጊዜ እንደሆነ ታውቋል፡፡

በራሪ ወረቀቱ የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣ መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆምና መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ የሚመክሩ ሀሳቦች እንዳሉበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ የማህበሩን አላማና በህዝብ ላይ አሉ ያላቸውን ችግሮች ለህዝብ ሲያስተዋወቅ የተያዘው አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል እንደተከሰሰም ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

አቶ ፋንታሁን እሁድ ጥቅምት 23 ሽሮ ሜዳ አካባቢ በራሪ ወረቀት ሲበትን ተይዞ ላዛሪስት በሚባለው ፖሊስ ጣቢያ ታስ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ (ምንጭ እና ፎቶ: ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 7, 2014 11:10 pm at 11:10 pm

    አቶ ፋንታሁን ህዝብን ለማነሳሳትና አመጽ ለመቀስቀስ ሙከራ በማድረግ በሚል ተከሰሰ:
    “ነጭ ሰንደቅ አላማ ሲያውረበልብ፣ ለሕዝብ በሰጠው በራሪ ወረቀቱ ላይ፡_
    * የህሊና እስረኞች መፈታት እንዳለባቸው፣!
    *መንግስት በሀይማኖቶች ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት፣!
    * በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎችን ማፈናቀሉ እንዲቆም!
    *መንግስት በተቋማት ላይ ከሚያደርገው ጣልቃ ገብነት እንዲቆጠብ!
    የሚመክሩ ሀሳቦችንና የማህበሩን አላማና ለህዝብ ሲያስተዋወቅ ነው።አራት ነጥብ።
    *******************!
    ***መንግስት ያሠረው በበራሪ ወረቀቱ ላይ ያለውን ፈፅሜአለሁ ምንአገባህ ብሎ ነው?
    ***በሕገመንግስቱ ይህ ለገዢው ፓርቲ ብቻ ይፈቀዳል ብሎ ነው?
    ***ይህንን ድርጊቴን ህዝብ የመቀበል ግዴታ አለበት ብሎ ነውን?
    ***ሕዝቡ እየተሰደበ እየተረገጠ በትናንሽ ጥቅማጥቅም ተይዞ ይኖራልና ችግሩን አትንገረው ብሎ ይሆን?
    ***ይህ ሌላ አማራጭ የሌለው ሕዝብ በሙሉ ፍቃደኛነት ሊረገጥ ተስማምቷል ብሎ ነው?
    *** ለእኛ በእኛ ሰው የሆነ ያለእኛ ምንም የማይሆን ግን ተበታትኖ የሚጠፋ ነው ብሎ ተማምኖ ይሆን?
    *** በፈጣንና አሳላጭ መንገድ በቅፅበት የሚያድገው ከሕዝብ በላይ ከመንግስት በታች የሆነው ቡድን ይሆን?
    ***የነጭ ባነዲራ ትርጓሜ ያልገባቸው ብጥብጥ ወዳድ(እነጭር ሲል አንወድም ይሆኑ?)
    *** ይህ ጭፍን ደጋፊ(ተደጋፊ)…ጭፍን ተቃዋሚ(አቋቋሚ) ዕርቅ ሰላም አንድንት ኀብረት ያቃዣቸው ይሆኑ?
    ***በእርግጥም አውራው ገዢ ፓርቲ ተራራ ውጡና፣ ገደል አቋርጡና ጉልበቴን ፈትሹ ብሎ እየገፋ ይሆን?
    *** መንቀሳቀስ፣ መዘዋወር፣ መሰለፍ፣ መሰብሰብ፣ በከልልና በክልከላ ከተለወጠ ዜግነት ቀርቶ በሊዝ መኖር ተጀመረ?
    ***በውስጥ የብሔርና ቋንቋ ብጥብጥ የቡድን መናቆር ትርፋማ የሆኑ ተደራጅተው አቆብቁበው እየጠበቁ ይሆን?
    “ማንም ሰው በፖለቲካ አመለካከቱ አልታሰረም! ሊታሰርም አይገባም!ኢህአዴግ ከስሕተቱ ይማራል! ከተባለ..የሰላም ማኅበር ማቋቋምና የህዝብ ብሶትን ለመንግስት ማሳወቅ በየትኛው ሕግና ሰንደቅ ወንጀለኛ ያደርግ ይሆን?
    _____ለመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ መከላከያ ለሕዝብ፣ ለሀገር ሉዓላዊነት ከቆመ ይህንን የተበላሸ(የበሰበሰ) ሥርዓት መምከር ወይንም የከፋ ውጥንቅጥ ውስጥ ከመግባታችን በፊት ማንአለብኝነት፣ የህዝብ ንቀት፣አምባገነን፣ የወሮ-በላ ቡድን እንዲወገድ አስተዳደሩን በሠላም ተረክቦ ለፍትሀዊ አስተዳዳር ማስረከብ ሀገራዊ ቃለ-መሐላ ግዴታ የገባበት፣ ኀላፊነትም የወሰደበት ለግለሰብና ለፖለቲካ ፓርቲ ዕድገት፣ ብልፅግና ሳይሆን ለሕዝብ ሠላምና ደህንነት መሆኑን አይዘንጋ!። ሠላም ለሁሉም።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule