• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኬኒያ፤ ትህነግ አሸባሪ መባሉ በፓርላማው ሊነሳለት ይገባል አለች

August 27, 2021 02:10 pm by Editor 2 Comments

ሐሙስ ዕለት የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በመከረበት ወቅት የኬኒያው ተወካይ ትህነግ አሸባሪ መባሉ ሊነሳለት ይገባል አሉ።

ኢስቶኒያ፣ ፈረንሳይ፣ አየርላንድ፣ ኖርዌይ፣ ዩናይትድ ኪንግደምና አሜሪካ በጠሩት በዚህ ስብሰባ ላይ የመንግሥታቱ ድርጅት ዋና ጸኃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ንግግር አድርገው ነበር። ዋና ጸሃፊውም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ያለው ግጭት ሊቆም እንደሚገባው በመጠቆም ንፁሀን እየተጎዱ ስለሆነ ሰብዓዊ ዕርዳታ ሊያገኙ የሚገባቸው ምቹ ሁኔታ ባለመፈጠሩ እንዳላገኙ አስረድተዋል።

ከዋና ጸሃፊው ንግግር ቀጥሎ የስብሰባው ጠሪዎች በተከታታይ ተናግረዋል። እንቆምለታለን የሚሉትን ዴሞክራሲ በገሃድ መቀመቅ በመክተት ከኢስቶኒያ እስከ ሜክሲኮ ያሉት አገራት በአሜሪካና አውሮጳ የታዘዙትን እንደ በቀቀን በመድገም ሎሌነታቸውን በዓለምአቀፍ መድረክ አስመስክረዋል።   

በአንጻሩ የራሺያዋ ተወካይ ለሞራል ልዕልና እና ሐቅ በመቆም በምዕራባውያኑ የተዘነጋውን እውነታ በማጉላት ኢትዮጵያ የራሷን ችግር የመፍታት ዐቅምና ብቃት እንዳላት በመጥቀስ ጣልቃገብነትን ተቃውመዋል። የኢትዮጵያ የግዛት አንድነት፣ ሎዓላዊነትና ክብር በምንም መገሠሥ እንደሌለበት የጠቆሙ ሲሆን ይህንን አቋማቸውን ሕንድና ቻይና አስተጋብተውታል።

በኢትዮጵያ ምርጫ መካሄዱን ያስታወሱት የራሺያዋ አምባሳደር፤ በዚህም ምርጫ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ አብላጫ ሊያስተዳድራቸው የሚገባውን ፓርቲ መምረጣቸው አገሪቷና የማትከፋፈል፤ ሕዝቧም በአንድነት የቆመ መሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ የራሺያ አምባሳደር ንግግር ኢትዮጵያ ልትበታተን ነው የሚለውን የምዕራቡ ተወካዮችና የአጨብጫቢዎቻቸውን ትርክት ገደል የከተተ ነበር።

ከዚህ በአንጻሩ የኬኒያው ተወካይ ንግግራቸውን ኢትዮጵያን በመክሰስ ወይም በማንኳስ ነበር የጀመሩት። የዛሬው ስብሰባ የሚያሳየን እና ችግሩ እየተባባሰ መሄዱ ኢትዮጵያ የግጭት መከላከልና ማስወገድ ስልቶች የሌላት መሆኑን ነው በማለት ነበር በንግግራቸው መግቢያ ላይ የተናገሩት።   

ከቅኝ ገዢ ጌቶቻቸው ጋር በአንድ መድረክ መታየቱን እንደ ትልቅ ዕድል የቆጠሩት የሚያስመስልባቸው የኬኒያው ተወካይ በአንድ በኩል የጌቶቻቸውን ቃል ለመጠበቅ በሌላ በኩል የኢትዮጵያን ጉርብትና ላለማጣትና ንግግራቸው የሚያስከትለውን በማሰብ አገም ጠቀም የሚባል ንግግር ነበር ያደረጉት። ተወካዩ በአቋመቢስ የበታችነት ወይም የተገዢነት ምስቅልቅሎሽ ሲሰቃዩ ተስተውለዋል።   

ተወካዩ በንግግራቸው ጌቶች እንዳይቆጡ ኢትዮጵያን ሲያብጠለጥሉ ይቆዩና ቀጠል ሲያደርጉ ደግሞ ኢትዮጵያ የነጻነት ቀንዲል፣ የጸረዘረኝነት ትግል ፋና ወጊ፣ ወዘተ በማለት ለማለሳለስ በብዙ የስቃይ ውጣውረድ ውስጥ አልፈዋል። ቅኝ ገዢዎቻቸው በቀደዱላቸው ቦይ ብቻ በመፍሰስ የትኛውም የትህነግ አመራር አንዴ እንኳ ያልተነገረውን ተናገሩ።

በንግግራቸው ማጠናቀቂያ ላይ ሊደረጉ የሚገባቸው ነገሮች በማለት የተወሰኑ ነጥቦችን ከጠቀሱ በኋላ ለኢትዮጵያ ፓርላማ ምክር ቢጤ ትዕዛዝ ሰጡ። “ፓርላማው በትህነግ ላይ የጣለውን አሸባሪ የሚለውን መጠሪያ ሊያነሳ ይገባል” በማለት ጌታቸው ረዳ እንኳን እስከዛሬ ደፍሮ ያልተናገረውን ተናግረዋል። “ጦርነት አማላይ ነው” በማለትም ኅልውናውን ለማስከበር በተነሳው የሕዝብ ሠራዊት ላይ ተሳልቀዋል።  

ዲፕሎማቱ ልክ ትዕዛዝ እንደፈጸመ አገልጋይ ይህቺ ንግግራቸው የምታስከፍላቸውን ዋጋ በመገመትም በስተመጨረሻ ላይ ኢትዮጵያን በመካብ ንግግራቸውን አጠናቅቀዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Slider Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. alfa woyane says

    August 27, 2021 11:31 am at 11:31 am

    kenya idea is real because ethiopia is not big country ethiopia lake of smart people
    ethiopia is full of stupid people because we didn’t solve our internal problem
    especially AMHARA is the cancer of the country i know ethiopia have 3 big cancer amhara oromo and tigray but the fack nationals they create unstable backward country
    down for amhara running prosperity party

    Reply
  2. Mesber says

    August 27, 2021 11:44 am at 11:44 am

    የኬኒያዉ ልዑክ የኢትዮዽያ ችግር በሁለት አመለካከት ውስጥ ያለ ችግር ነዉ ብለዋል :: በማዕከላዊነት የማስተዳደርና በፌዴራላዊነት የመተዳደር መካከል ያለ ልዩነት ነዉ ብለዋል ::
    የመልክታቸዉ ዋናዉ ፍሬ ነገሩ ዪህ ነዉ

    Reply

Leave a Reply to alfa woyane Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule