• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዘረፋ ውሎ በእንዳማሪያም

April 29, 2013 04:04 am by Editor 2 Comments

ስብሃት ነጋ ባለፈው ሳምንት አዲስ አበባ በሚታተመው የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የሰጠውን ቃለ መጠይቅ አነበብኩት:: ስብሃት ነጋ “ኢህዴግን የመሰለ ፓርቲ በአፍሪካ የለም” እና ሌላም ብዙ ፣ ብዙ ይላል:: ይዘብታል ፣ ይፎክራል ፣ ይሸመጥጣል ፣ ያቀረሻል ፣በህዝብ ሞራል ላይም ያላግጣል::  ብዙም አልደነቀኝም::  ስብሃትም ሆኑ የዚህ ፋሺስታዊ ስርዓት አንቀሳቃሾች በብዙሃን ደም ላለፉት አርባ አመታት ታጥበዋል ፣ ታሪክ አውድመዋል ፣ እጅግ ከፍተኛ ዘረፋ ፈጽመዋል ፣ አገር ቆርሰው ሸጠዋል::  በጣም ከፍተኛ ወንጀል የሰሩ ሰዎች እንደመሆናቸው በአገሪቷ የፖለቲካ ለውጥ  ከመቼውም ጊዜ በላይ መቀጣጠሉ እንቅልፍ እንደነሳቸው እያየን ነው:: አዎን ስብሃት ገና ፣ ገና ከዚህም በላይ ብዙ ይናገራል ፤ ቁጣው እያየለ በሄደ ቁጥር ብዙ ወንጀሎችም ይሰራል::

ዛሬ ወያኔ ኢህአዴግ ከመቼውም ጊዜ በበዛ ፍጥነት እና ማን አለብኝነት ኢትዮጵያዊ የሆኑ መሰረቶችን የመናዱን ስራ አጠናክሮ እየሰራ ለመሆኑ በየእለቱ የምንሰማቸው ዜናዎች እና ዘገባዎች ያሳያሉ:: እንደ እኔ ፣ እንደ እኔ የወያኔ የጥፋት ስራ ሳይሆን የጨመረው ይልቁንስ ረጅም እድሜ ለኢሳት ይስጠውና የዜና ዘገባ ብዛት እና አይነቱ መጨመሩ ይመስለኛል:: ወያኔ ሲፈጠር ጀምሮ ኢትዮጵያዊ መሰረት ያላቸውን እሴቶችን የማጥቃት ስራን እንደ መጨረሻ ግብ(strategic goal) አስቀምጦ የሚንቀሳቀስ ድርጅት መሆኑን ቀድመን ላወቅን እና ለተረዳን ሰዎች ግን እምብዛም አዲስ ነገር አይደለም:: ዛሬ ላይ ከኢትዮጵያ ከሚወጡ ዜናዎች በብዛት የምንሰማው ብዙዎች ሲያለቅሱ እና ጥቂት ዘረኞች ደግሞ ያለ ይሉኝታ ሲዘርፉ ፣ ሰዎችን አስረው ሲያሰቃዩ፣ እና ኢትዮጵያውያንን ዘር ቆጥረው ከቀያቸው ሲያፈናቅሉ ሆኗል::

የኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ዋይታ በቤኒሻንጉል እና ጉራፈርዳ፣ የባህታውያን ለቅሶ በዋልድባ ፣ የእስልምና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን የፍትህ ጥያቄ በመላ ሃገሪቱ ፣ ሌላም ፣ ሌላም:: ወያኔ ኢህአዴግ በአገር እና በወገን ላይ የሚያደርሰው ጥቃት በግብ ደረጃ የተያዘ በመሆኑ ይብሱን ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚችል በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል:: ዛሬ ላይ ከዳር ቆመው የሚመለከቱ ሰዎችም ሆነ በስርዓቱ ውስጥ ያሉ ካድሬዎች እና አገልጋዮች ይህንን ሃቅ በደንብ ልብ ብለው ሊመለከቱት ይገባል:: የጥቃት ዱላው በአንድ ወይም በሌላ በኩል አይደርስ የሚመስልበት ቦታ ሁላ ይደርሳል::

ኢትዮጵያውያን ከምንም ነገር በላይ ለሃይማኖት እና የእምነት ተቋሟት ታላቅ ክብር ይሰጣሉ:: በዛሬ ጽሁፌ ለማንሳት የፈለግኩት ጉዳይ በአንድ ወቅት በወያኔ ኢህአዴግ ውስጥ ታጋይ በነበርኩበት ወቅት በዘመቻ ከስብሃት ነጋ እና ከሃለቃ ጸጋይ በርሄ ጋር ሌሎች ሁለት ታጋዮችም ተጨምረውበት አንድ ገዳም እንዴት እንደፈርን እና እንደዘረፍን በማሳየት ስብሃትም ሆነ ድርጅቱ እንዴት ለአገራዊ እና ሃይማኖታዊ ተቋማት ያላቸውን ንቀት ለማሳየት ነው:: ጊዜው ሕዳር ወር 1971ዓ.ም. እና የተ.ሓ.ህ.ት. 1ኛ ጉባኤ እየተቃረበ የመጣበት ወቅት ነበር። ድርጅቱ ለጉባኤው ማካሄጃ በሚል ሰበብ የትግራይ ደሃ ገበሬዎችን ንብረት እና ገንዘብ በስፋት መቀማቱን በዘመቻ ተያይዞታል::  ሃብትና ንብረታቸው የተዘረፈ ንጹሃን የትግራይ ገበሬዎችንም ሃለዋ ወያኔ በማስገባት መፍጀቱ ተጧጡፏል፤ በወቅቱ የተ.ሓ.ህ.ት. ቤዝ በለሳ፤ እገላ ወረዳ ውስጥ ይገኛል። ብዙ ክፍሎች፤ ማለትም 02 ወታደራዊ ማሰልጠኛ፤ 03 ህክምና፤ 04 ፖለቲካ ጽ/ቤት፤ 05 ክፍሊ ኢኮኖሚ፤ 09 መሳሪያ ግምጃ ቤትና 06 ሃለዋ ወያነ ተበለው ተከፋፍለው እዚሁ ቦታ ላይ በተለያየ አቀማመጥ ሆነው ይሰራሉ። አቦይ ስብሃት በ04 ፖለቲካ ጽ/ቤት በሚታዘዙ እና በአዲ ጨጓር እና በለሳ ምይ ሃማቶ ላይ በሚገኙ ሁለት ሃለዋ ወያኔዎች(እስር ቤቶች) ንጹሃንን አሳስሮ ያስገርፋል፣ ያስገድላል:: እኔ በወቅቱ የህክምናው ክፍል ሃላፊ ነበርኩኝ:: እና ታዲያ በዚሁ አንድ የህዳር ቀን በስብሃት የተጻፈ ቀጭን ደብዳቤ በምሰራበት የህክምና ክፍል ደረሰኝ:: ደብዳቤው እንዲህ ይላል : ነገ ጠዋት ልክ በ2 ሰዓት መሬቶ እንድትጠብቀኝ፤ ወደ ሽራሮ ለሥራ ጉዳይ አብረን እንሄዳለን:: ለምን ፣ እንዴት ፣ በምን ተብሎ አይጠየቅም፤

በነጋታው እንደታዘዝኩት በተባለው ሰዓት መሬቶ ቁሽት ቀድሜ ደረሼ ቆየሁት። እሱም በሰዓቱ መጣ። ተያይዘን ጉዞአችንን ወደ ጭላ ወረዳ ቀጠልን። ቀኑን ሙሉ ስንጓዝ ውለን በመሃልም ግርማይ ጀብር የሚመራት አንድ ሃይል ተቀብላን አንድ ቦታ አደርን። ከአስመራ ወደ አድዋ የሚወስደውን መንገድ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ አሻገሩን። ይህ መንገድ ሁልጊዜ የኢትዮጵያ ጦር አይለየውምና ለመሻገር ጥንቃቄ ይሻል::

ጭላ ከጥዋቱ 2 ሰዓት ገባን። እዛ የቆዩን ሃለቃ ፀጋይ በርሄ–የላይ አድያቦ ሕዝብ ግንኙነት፤ አጽብሃ ሀ/ማርያም–የአንከረ ሕዝብ ግንኙነት፤ ቀሺ ታደሰ–የክርቢት ነውጠኛ መሪ ነበሩ። እኔና ስብሃት ተደምረን አምስታችን ጭላ ውለን ስብሃት ቀድሞ ለወጠነውና አስቅድሞ መረጃው ለሌለኝ የዘረፋ ስራ ወደ እንዳማርያም ገዳም ጉዞ ጀመርን:: ሃለቃ ፀጋይ በርሄ በስብሃት በታዘዘው መሰረት አስቀድሞ ጥናቱን ጨርሶ ስለነበር፤ የቤት ክርስትያኑን አቃቤ ግምጃ ቤት ባህታዊ ማን መሆናቸውን እና የት አካባቢ እንደሚኖሩ አውቋል። ሌሎቻችን ታጣፊ ክላሽንኮቭ ስብሃት ነጋ ደፍሞ ሽጉጥ ታጥቋል። ለምን እና ወዴት እንደምንሄድ ቀሺ ታደሰ፤ አጽብሃ ሃይለማርያምም ሆነ እኔ አናውቅም። ኋላም ተጉዘን እንዳማርያም ቤተ ክርስቲያን ገባን። ቤተ ክርስቲያኑ በጥንት ዘመን በአብርሃ ወአፅብሃ ዘመነመንግሥት የተሰራ፤ በጣም ሰፊና ብዙ የአትክልት እና ፍራፍሬ እርሻ የሚለማበት ገዳም ነው:: በመነኮሳት ጉልበት በመስኖ የለማ ሎሚ፤ ሙዝ፤ ብርቱካን፤ ትርንጎ፤ መንደሪን ገዳሙን ከቦታል። መቼም አካባቢው ውብ እና ለመንፈሳዊ ህይወት የተመቸ ነው:: በእድሜ የበለጸጉ ባህታውያን፤ ቀሳውስት፤ መናንያን እና ዲያቆናት በገዳሙ ዙሪያ መንፈሳዊ ህይወታቸውን ይመራሉ። ውስጥ ለውስጥ ብዙ ከሄድን በኋላ ከፊታችን አንድ ዲያቆን አገኘን። ሃለቃ ፀጋይ ዲያቆኑን ለብቻ ነጥሎ አናገረው፤ ምን እንደተነጋገሩ እኔ ካለሁበት ብዙም አይሰማም ብቻ ሁለቱ ተያይዘው  ከፊት እየመሩ ወደ አንድ ቤት ውስጥ አስገቡን። ቀጥሎም ስብሃት ነጋ እንዲህ አለ፤  ሌሎቻችሁ እዚሁ ቆዩ::  እኔ ፣ ገ/መድህን እና ሃለቃ ፀጋይ ብቻ የገዳሙን አስተዳዳሪ ለማናገር እንሄዳለን:: ከዚያም ሶስታችንም ተያይዘን ከነትጥቃችን ወደ ገዳሙ አስተዳዳሪ ቤት አቀናን:: የገዳሙንም አስተዳዳሪ ከቤታቸው አገኘናቸው:: ለአፍ ያህል ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ስብሃት ጊዜ ሳያጠፋ “የመጣነው ገንዘብ እንዲሰጡን ስለሆነ ያለዎትን ሁሉ ይስጡን!” አላቸው። ለመነኩሴው ግር የሚል ትዕዛዝ ነበር:: ብዙም ሳያቅማሙ “እኔ አልሰጥም፤ የእመቤቴ ብርሃን ንብረትና ሃብት ላይ የማዘዝ መብት የለኝም:: አልሰጥም::” በማለት እቅጩን በግልጽ አማርኛ ተናገሩ:: ስብሃትም አይኑን እያጉረጠረጠ ድምጹን ከፍ አድርጎ አምጡ ማለቱን ቀጠለ:: ስብሃት በቀላሉ  እንደማይመለስ በድምጽም ፊቱን በመቀያየርም እንዲረዱ አደረገ ፣ ምስኪኑ አባትም አማራጭ እንደሌላቸው ተረዱ::ትንሽ  አስብ አደረጉና  ወደውስጥ ገብተው የተቋጠረ ከረጢት ተሸክመው መጡ።

ባዘነ አንደበት እንዲህም ሲሉ ተናገሩ ፤ “የቤተ ክርስቲያን ሃብት ወድጄ ፈቅጄ ሳይሆን የሰጠኋችሁ አስገድዳችሁ እና አንቃችሁ እንደወሰዳችሁ እወቁት::” ከዚያም ከረጢቱን አልሰጥም በማለት ብር 50,000 የታሰረ ገንዘብ ከፊቱ ዘረገፉለት። ስብሃትም በፍጥነት ይዘነው በመጣነው ‘ሃቨር ሳክ’ በሚባል ወታደራዊ ሻንጣ ሞልተን ተሸክመን እንድንወጣ አዘዘ::  እኛም የተባልነውን አደረግን:: ባህታዊውም በመውጫችን ላይ እንዲህ አሉ፤ “ነገ ጠዋት ለሕዝበ ክርስቲያኑ የሆነውን ሁሉ እናገራለሁ::” የተዘረፈውን ገንዘብ እኔና ስብሃት ተሸክመን ተመልሰን በለሳ ማይሃምቶ ገባን።

የተፈጸመውን የዘረፋ እና የገዳም ደፈራ የአካባቢው ሕዝብ ሁሉ ሰማው፤ በተሰራው ስራም ክፉኛ አዘነ፤ አወገዘውም። ስብሃት ድርጊቱ የየግል ምስጢራችን ሆኖ መጠበቅ እንዳለበት አስጠነቀቀን። ለዘረፋው ስራም ባለን ድርጅታዊ ታማኝነት እንደተመረጥን ገለጸልን። እንግዲህ ይህ አንድ ገጠመኝ ብቻ ነው:: ዘረፋ፣ ማውደም ፣ ታሪክ እና ቅርስ ማጥፋት ፣ የእስላምም ይሁን የክርስቲያን ቤተ እምነቶችን መድፈር እና ማበላሸት ለህወሃት የሰርክ ስራዎች ናቸው::

በአለቃ ገበረ ሃና ስም የሚነገር አንድ ታሪክ አለ:: ልጅቷ አለቃ ጋር ሄዳ “ጎረምሶቹ ሁሉ ድንቼ ፣ ድንቼ እያሉ ይጠሩኛል:: ለምን ይመስልዎታል::” ብትላቸው አለቃም እንዲህ አሉ:: “ሊልጡሽ ፈልገው ነዋ!”:: ትናንትና በዘር እና በሃይማኖት እየመረጠ የአንድን አገር ወንድማማቾችን አንዱን ለአንዱ ታሪካዊ ጠላትህ ነው ፤ ላንተ ህልውና ከኔ በላይ ላሳር እያለ ሲመጻድቅባቸው የነበሩ የሃይማኖትም ሆነ የብሄር ቡድኖችን ከነጠለ በኋላ ያለ ሃይ ባይ ሲያጠቃ እያየን ነው:: ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ እስር ቤቶች አስር ሺህ በሚቆጠሩ ኦሮሞዎች ታጭቀዋል::  በቃሊቲ ፣ በጨለንቆ ፣ በዝዋይ ፣ በሸዋ ሮቢት ፣  እና በሌሎችም በይፋ ባልተመዘገቡ የወያኔ ማጎሪያዎች ውስጥ ዜጎች ያለሃጥያታቸው ታስረው ይሰቃያሉ::

ስርዓቱ ዛሬ ላይ በሰፊው በእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ የመጨረሻውን ዱላ ከማንሳቱ በፊት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን የማጥቃቱን ስራ ሙሉ አቅሙን አሳርፎ ሰርቷል:: ከኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በቀር በጉዳዩ ብዙም ግድ ያለው አልነበረም:: ነገ ደግሞ ተረኛ የካቶሊካዊት ወይም የሌላ ወንጌላውያን ቤተክርስቲያናት ሊሆኑ እንደሚችሉ መገመት አይከብድም::  ይህን ዘረኛ እና ከፋፋይ ስርዓት በመታገስ እና በማስታመም የትኛውም የህብረተሰብ ክፍል ነገ ጥቃት ተቀባይ ሊሆን አይገባም::

ስለወያኔ ማንነት ይኸው ለአመታት የተናገርኩት አንድ በአንድ ጊዜውን እየጠበቀ ሲፈጸም አየን:: አሁን ከመቼውም ጊዜ በላይ ኢትዮጵያውያን በአንድ ድምጽ በቃ የሚሉበት ጊዜ ላይ ደርሰናል:: የለውጥ ጊዜ እየቀረበ ነው:: ኢትዮጵያውያን አይን ለአይን ተያይተው ፤ ልብ ለልብ ተግባብተው ይህንን ዘረኛ እና ፋሺስታዊ ስርዓት ከዚያች ቅዱስ አገር የሚያጠፉበት ጊዜ በእውነትም እየቀረበ ነው:: ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሲሰሩ ምን ማድረግ እንደሚችሉ እስከ አፍንጫው በታጠቀው የወራሪው የፋሺስት ኢጣልያ ጦር ላይ የተቀዳጁትን የአድዋውን ድል ማስታወሱ ብቻ በቂ ነው::በአዲስ ተስፋ ለህልውናቸው እና ለቀጣይ ትውልድም የምትበቃ አገር እና መንግስት ለማቆም ሊሰሩ የሚገባበት ወቅት እየመጣ ነው:: በመጨረሻም ከሰሜን እስከ ደቡብ ፤ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ:: እስላም እና ክርስቲያን ሳይሉ ፤ ኦሮሞ ፣ አማራ ፣ ትግሬ ፣ ጉራጌ ፣ ወላይታ ፣ አገው ፣ አፋር ፣ ቤኒሻንጉል ፣ ስልጤ ፣ አደሬ ነኝ ብለው ወያኔ በሰፋላቸው የዘረኝነት ወጥመድ ውስጥ ሳይወድቁ እጅ ለእጅ ተያይዘው ለወሳኝ የፖለቲካ ለውጥ እንዲሰሩ ጥሪዬን አስተላልፋለሁኝ:: (ፎቶ: ሐራ ዘተዋሕዶ)

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Birhanu Kebede says

    May 4, 2013 11:21 pm at 11:21 pm

    Sibhat Nega is finished. What a useless and litter old guy he is!! He always preaches about TPLF. What a narrow minded!!!

    Reply
    • seble says

      May 8, 2013 03:07 am at 3:07 am

      beka endi eyaregachu sewun yalhone immage lemestet atitegnum aydel? poor u.
      miasazinew, weyane ena ehadeg betam yeteleyayu negeroch nachew. enante mitawerut weyane eyalachu new aydel? ageritua mitimeraw degmo be ehadeg new. ehadeg demo, amaram, tigrem, oromom, guragem,…….. lelam lelam yakatete new. enji enante endemtilut aydelem. nway, am not in to politics n i don’t support any of Ethiopian party. i only care abt the country. esuan demo sint meriwoch aytena yeteshale yelem. yekefa enji yeteshalem demo yimetal biye alasbim. but PLS stope on poisoning pples mind with such kind of hates. u can hate it for ur self but keep the hate for ur self! dont be narrow minded!!!

      Reply

Leave a Reply to seble Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule