• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዕርቅን የሚፈልግና የሚቀበል በራሱ የሚተማመንና ደፋር ነው

November 6, 2013 10:02 am by Editor Leave a Comment

ከዝግጅት ክፍሉ፡ “በህወሃት ውስጥ የዕርቅ ሃሳብ መነሳቱ ተሰማ” በሚል ርዕስ ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ላቀረበው የዜና ዘገባ አቶ አንዱ ዓለም ተፈራ የሚከተለውን የአጸፋ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በቅድሚያ ጊዜያቸውን ወስደው ይህንን ምላሽ ስለጻፉ እያመሰገንን ይህንን ዓይነቱን ባህል ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሚያደፋፍር መሆኑን እንወዳለን፡፡


በኢትዮጵያዊያን ዘንዳ፤ ይቅር ለፈጣሪ ብሎ ከተጣሉት ጋር እንዲታረቁ፤ ከልበ ሙሉዎች፣ ከባህል አካሪዎችና ለነገ ግምት ካላቸው ሰዎች ይጠበቃል። እናም አመዛዛኝ የሆኑ፤ አክብሮት፣ ርጋታና ፍቅር ያላቸው፤ ለእርቅ ምን ጊዜም በራቸው ክፍት ነው። አጉል የሆኑት ደግሞ፤ እኔ ስህተት አልሠራም፣ እኔ ምን ጊዜም ትክክለኛ ነኝ፤ ስለሚሉና ሌላው ሁሉ ለነሱ ሰግዶ እንዲልመጠመጥ ስለሚፈልጉ፤ ለእርቅ በራቸው ዝግ ነው። አጉል የሆኑ ማለት፤ እብሪተኞች፣ ፈሪዎች፣ በራሳቸው የማይተማመኑ፣ የግልና የአሁን ሕይወታቸውና ጥቅማቸው እንጂ፤ የኅብረተሰብ ወይንም የሀገር ጉዳይ የማይዋጥላቸው ናቸው። ትናንት በጎልጉል ገፅ፤ በህወሃት ውስጥ የዕርቅ ሃሳብ መነሳቱ ተሰማ፤ – “የኢህአዴግ የአፈና ገመድ ነትቧል፣ ድርጅቱ ተናግቷል” በሚል ርዕስ አዘጋጆች የጻፉትን ደጋግሜ ተመለከትኩትና እኔ ይኼን በሚመለከት፤ የትም የሚደርስ አይደለም በማለት ሀሃስቤን እንደሚከተለው አቅርቤአለሁ።

በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሀቅ ለማንኛውም ሰው ዓይን የሚያስፈጥጥ፣ የሚረብሽና እረፍት የሚነሳ ነው። ይኼን በምንም መንገድ ቢያዩት፤ የነገውን አስፈሪ መጪ ሊያስበረግገው አይችልም። አስፈሪ ነገ ከፊታችን ላይ ተገትሯል። እንግዲህ ጥያቄዎቹ፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ይኼን እንዴት ሊያየው ይችላል? ነው። ማየቱ ብቻ ሳይሆን ምን ያደርጋል? ነው።

አንድ ግልፅ መሆን ያለበት ሀቅ አለ። ለዚህ ሁኔታ ተጠያቂው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ነው። ይህን ግን ግንባሩ አይቀበለውም። እናም መፍትሔ ፍለጋ የሚሮጠው ከዚህ ተነስቶ አይደለም። እናም ዕርቅ አይዋጥለትም። በተመሳሳይ መንገድ፤ አፄ ኃይለ ሥላሴ ለሕዝቡ ትንሽ መፈናፈኛ የሥልጣን መንገድ አለመክፈታቸውን፤ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ከሱ ሌላ አዋቂና መፍትሔ ሠጪ የለም ብሎ ማመኑን፤ በተመሳሳይ ምንገድ ደግሞ መለስ ዜናዊ የዚሁ ቅጂ መሆኑን ማጤን ይኖርብናል። ሶስቱም ገዥዎች ከራሳቸው በላይ ነፋስ ብቻ ባይ እንደነበሩ ሁላችን እናውቃለን።

አንዳንዶቻችን የራሳችንን ኃላፊነት ወደ ሌላው በማሻገር፤ ህወሃት በራሱ ፈርሶ ወይንም በፈቃዱ ሥልጣን ሊያጋራ እንደሚችል ማስረጃው ሳይሆን ምኞቱ አለን። ደግ! ምኞት ብለን መቀበል አንድ ነገር ነው። ምኞት ብቻ ነው ብለን መቀበል አለብን። ከዚያ አያልፍም። በርግጥ የሕዝቡ እየደፈረ መምጣትና በተለያዩ ቦታዎች የሚነሱት ጥያቄዎች የትግሬዎችን ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት መሪዎች ሊያቁነጥንጥ ይችላል። መቀመጫዎቻቸውን ከማደላደል ያለፈ ግን፤ የሚያደርጉት እንደሌለ መረዳት አለብን። ከደረስብን ግፍና በደል ተነስተን፤ ምኞታችን በዝቶ አስተሳሰባችንን እየጋረደው፤ ምኞታችንን ሀቅ እያደረግን የምንዋዥቅ ሞልተናል። ግን ታሪክ የሚያስተምረን፤ ከእባብ እንቁላል እርግብ እንዳንጠብቅ ነው።

በትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት መሪዎች መካከል ዕርቅ ለውይይት ሊነሳ ይችላል። ይኼን መቼም አይደረግም ብዬ አፌን ሞልቼ መናገር አልችልም። በመካከላቸው አንድነት ስለሌለ፤ አንዳንዶቹ ያገኙትን ጥቅም ይዘው የተደላደለ የወደፊት ኑሮ ከፊታቸው ብልጭ ሊልባቸው ይችላል። እነዚህ ግን አቅራቢዎቹ ግለሰቦች ብቻ ናቸው። ወሳኙ ደግሞ ተሰባስበው በአንድነት የሚስማሙበት ብቻ ነው። እናም ማተኮር ያለብን፤ የጠቅላላ ስብስቡ ቅኝት ላይ ነው። የጠቅላላ ስብስቡ ቅኝት ደግሞ ከራሱ ታሪክና ከሌሎች መሰሎቹ ታሪክ የተጻፈ ስለሆነ ማወቁ አይቸግርም። ታሪክ ታስተምራለች ሲባል፤ ማገናዘቡን ለኛ ትታ ነው። ከታሪክ የማንማር ከሆን፤ አሁንም በዚያው ስንዳክር ለወጪዎቹ በሽታችንን እናተላልፍላቸዋለን። ትጥቅ መፍታት እንዳይሆን መገንዘብ አለብን።

እርቅ ወርዶ ሀገራችን በሰላም የወደፊቷን የምትጀምር ከሆነ፤ ከማንም በማያንስ ደረጃ ደስተኛ እሆናለሁ። በምኞት ፈርስ ግን መጋለቡን እስከዛሬ አድርገነዋልና የዚያ ፈረስ ጥላውም ከኔ ጋር የለም። ፈረሱ ደክሞት ሕይወቱን ጨርሶ ሞቷል። ጥላውም አብሮ ተቀብሯል። የሀገራችን አደጋ ከባድ ነው። የተመሰቃቀለ ነው። እንዲያው አንድ ቀን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ተነስቶ ከዛሬ በኋላ ሁሉ ነገር ተለውጧል! የሚልበትና የሚቀየርበት እውነታ ገና መጻፊያ ቀለሙ አልተበጠበጠም።

እንዲህ ነው። የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት መሪዎች ዕርቅ ይፈልጋሉ ብለን ስንጀምር፤ ከኛ ምኞትና እምነት ሳይሆን መነሳት ያለብን፤ ከነሱ እምነትና እውነታ ነው። መመልከቻ መነፅራችን የነሱ መሆን አለበት። ለምን ይፈልጋሉ? በነሱ እምነት፤ ጠንካራ ተቃዋሚ የለም። ሥልጣኑ ሁሉ በጃቸው ነው። ሀብቱ ሁሉ በጃቸው ነው። ጉልበቱ ሁሉ በጃቸው ነው። መንግሥታዊ መዋቅሩ ሁሉ በጃቸው ነው። የውጭ ሀገር መንግሥታት ሁሉ የሚያውቋቸው እነሱን ብቻ ነው። ብዙ የድርጅት አባላት ያሏቸው እነሱ ብቻ ናቸው። በሌላ በኩል እኛ ይኼ ሁሉ ገለባ እንደሆነ እናውቃለን። ለዚህ ነው፤ እንዲህ ስለሆነ፣ ያ በዚያ ሰለመጣ . . . እያልን የምንደራርተው። ይኼንን የተረዱ፣ የሚይውቁትና የሚቀበሉት ቢሆን ኖሮ፤ ብዙ አምባገነን መሪዎች ቀድመው እርምጃ ይወስዱ ነበር። አላደረጉም። የኛዎቹ አምባገነኖች ከሌሎች ተለይተው አዋቂና ጥንቃቄ ይወስዳሉ ማለት፤ የምኞትን ቦታ ለእውነታ ማስረከብ ነው። አልፎ ተርፎም፤ ማንም ሳይጠይቀን ራሳችን ራሳችንን ትጥቅ እያስፈታን እንዳይሆ አፈራለሁ።

አሁንም አንድ ታሪክ የሚያስተምረንን ቁም ነገር እዚህ ላይ ልጥቀስ። እንደሌሎቹ አምባገነኖች ሁሉ፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት መሪዎች ሁሉ፤ ለሁሉም ጥያቄዎች ያላቸውና የሚሠጡት መልስ፤ በጉልበት መደምሰስ ነው፤ ከሕዝቡም በኩል ይምጣ ከራሳቸው መካከል። ይልቁንስ ኢትዮጵያዊያን በአንድ ሆነን፤ አንድ አጀንዳ ብቻ ይዘን፤ ከሕዝቡ ጎን በመሠለፍ፤ እውነተኛ መፍትሔ የሚመጣበትን መንገድ አብረን እንፈልግ።

የኢትዮጵያን ነገ የሚወስነው፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት የሚያደርገው ወይንም የማያደርገው ሳይሆን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚተገብረውና የሚጽፈው ብቻ ነው። የየካቲት ፲፱፻፷፮ ዓመተ ምህረት ታሪክ የኢትዮጵያ ሕዝብ መነሳት እንጂ፤ የንጉሠ ነገሥት ዝም ማለት አይደለም። የደርግም የመጨረሻ ታሪክ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ እምቢታና የታጠቁ ኃይሎች ደርግን መደምሰስ እንጂ የደርግ ተግባር አልነበረም። አሁንም በድጋሜ፤ የነገው ታሪካችን የኢትዮጵያ ሕዝብ መነሳት እንጂ፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ተግባር አይደለም የሚጻፈው። ሲጀምርና ሲጨርስ፤ “የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ተነስቶ በማመፅ፤ የትግሬዎችን ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ደመሰሰ!” ነው የሚለው።

አስከመቼ

eske.meche@yahoo.com

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule