• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓይን እያየ ወደገደል? ምን ይባላል!

August 29, 2016 04:47 am by Editor 2 Comments

በአገዛዙ ወንበር ላይ ተጣብበው የተቀመጡት ሰዎች ሁሉ ብዙ ቢሆኑ ይነጋገሩ ነበር፤ ቢነጋገሩ ሁሉም በየፊናውና በየአቅጣጫው በራሱ ዓይኖች ያየውንና በራሱ ጆሮዎች የሰማውን፣ በራሱ አእምሮ አብሰልስሎ እያቀረበ ክርክር ይፈጠር ነበር፤ ከክርክሩ የሚፈልቀው እሳት ከተለያዩ ሰዎች የሚወረወሩትን ሀሳቦች እያቀለጠ አዲስ መመሪያ ያወጣ ነበር፤ ነገር ግን ተጣብበው የተቀመጡት ተጣብቀው አንድ በመሆናቸው ዓይን የሚያየውና ጆሮ የሚሰማው አንድ ነው፤ አእምሮ ሲጨፈለቅና ሲጣበቅ ሕይወቱን ያጣል፤ ስለዚህም የታየውና የተሰማው ጎዳ ሆኖ ሲቀርብ ውጤቱም ጎዳ በመሆኑ ክርክር የለም፤ ክርክር አለመኖሩ የመካንነት ምልክት ነው፡፡

አገር ተረብሽዋል፤ ሥርዓት ጠፍቷል፤ መደማመጥ ተስኖናል፤ የገነፈለው ስሜት እያቀለጠ ወደሞት ጅረት እየወሰደን እንደሆነ ወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት ገና አልተገነዘቡም፤ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ተገንዝቦታል፤ በወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት በሚገነዘቡበት ጊዜ የሞት ጅረት አጥለቅልቆናል፤ መድኅን የሚመጣው ከሞት በፊት ነው፤ የዱሮ አዝማሪ እንዳለችው፡–

አንጀቴ ተቆርጦ ከሆዴ ከወጣ፣
እንግዲህ ሀኪሙ ምን ሊቀጥል መጣ!

ሳምሶን ‹‹ውጽዒ ነፍስየ ምስለ ነፍሶሙ፤›› ብሎ ምሰሶውን ገፍቶ እንደጣለው ዛሬም በወንበሩ ላይ የተጣበቁት ምሰሶውን ገፍቶ የመጣልና የሦስት ሺህ ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ ለማፈራረስ ጉልበቱ እንዳላቸው ያምኑ ይሆናል፤ ‹‹ውጽዒ ነፍስየ ምስለ ነፍሶሙ›› ለማለትና ውጤቱንም ለመቀበል ከቆረጡ ያለምንም ጥርጥር በቂ ጉልበት አላቸው፤ ነገር ግን ይህ ጉልበት የተባረከና የተቀደሰ አይደለም፤ ዝናብ እንደሚወርድበት ክምር ጨው ነው፤ ዝናቡ ከጉልበት ቁጥጥር ውጭ ነው፤ በዚያ ላይ አንድ የሁሉም አገር ታሪክ ያረጋገጠው እውነት አለ፤ አሸናፊ ይጠናከራል፤ ተሸናፊ ይዳከማል፤ ሕዝብ ተሸናፊ ሆኖም አያውቅ፡፡

በዚያ ላይ ወደእምነት ደረጃ ከፍ ስንል ኃያል እምኃያላን የሆነ አምላክ አለ፤ በጉልበታቸው የሚታበዩትን ይታገሳቸዋል እንጂ ለመጨረሻ ድል አያበቃቸውም፤ የደካሞቹንም ስቃይና መከራ የሚያበዛው የድል አክሊል አዘጋጅቶላቸው ይሆናል፤ ጉልበተኞች ከዕብሪታቸው ሲጸዱና የእግዚአብሔርን ኃያልነት ሲቀበሉ በነሱ ላይ ድልን ለተጎናጸፉት ያስተምራሉ፤ የጉልበተኛ ሥርዓት ወድቆ የሕግ ሥርዓት ይተከላል፤ አሸናፊም ተሸናፊም በሕግ ጥላ ስር ይተዳደራሉ፡፡

አሸናፊም ተሸናፊም አንድ ዋና ነገር ቦግ ብሎ እንዲታያቸው እመኛለሁ፤ ትግላቸውም ሆነ ውጤቱ የግል አይደለም፤ ከመሀከላቸው የአምባ-ገነንነት ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ቀስ በቀስ ትግሉን የግል እያደረጉ ሄደው በመጨረሻ ድሉንም የግል ያደርጉታል፤ ሌላ ቀርቶ ቤተ-ሰቦቻቸውንም ይረሳሉ፤ አሸናፊም ሆነ ተሸናፊ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ የብዙ ሰዎችን ትብብርና ከባድ መስዋእትነትን የከፈሉ ሰዎችን የያዘ ነው፤ እነዚህ በብዙ መንገድ ብዙ ዓይነት መስዋእት የከፈሉ ሰዎች ለሚቀጥሉት ትውልዶች የሚያወርሱት ብዙ ነገር አለ፤ ራሳቸውን ሀብታም ማድረጋቸውንና ሰዎችን እንደፈለጉ ሲቆርጡና ሲፈልጡ መኖራቸውን ማንም እንደውርስ አይቀበላቸውም፤ ዘመን አልፎበታል፤ ታሪክም አይሆንም፤ የተጋድሎ ታሪካቸው፣ ለነጻነት፣ ለእኩልነትና ለአገር ባለቤትነት የሚያበቃና ለተከታይ ትውልዶች ሁሉ አርአያ የሚሆን ታሪክ በኩራት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡

በቀል፣ ጭካኔና በስሜት መገዛት ውሎ አድሮ ያጋልጣል፤ የሀብታሙ (አያሌው)ና የተመስገን (ደሳለኝ) ተገቢውን ህክምና ማጣትና መሰቃየት በምድርም በሰማይም ያስቀጣል፤ ይህንን ባህል አድርገን እንዳንቀጥል እሰጋለሁ፤ አእምሮአችንን ጡንቻ ብቻ ስናደርገው የማሰብ ሥራውን ያቆማል፤ ጠላት ለሚባለው ሰው የተመኙለት ገደል ላይ ዓይኖችን ተክሎ መራመድ ራስን ወደዚያ ገደል ማስገባት ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ነሐሴ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Wondefraw says

    August 30, 2016 08:23 am at 8:23 am

    Long life for u it sensible writing now they should think in different mind.

    Reply
  2. Naji says

    September 1, 2016 01:37 am at 1:37 am

    Wishing you good health,many more years with strength and energy, you are truly and educator and national figure. You are absolutely correct when you said that those who are in leadership positions are guided and manipulated by a single mind attached to a single brain. If there had been honest dialogue and consensus all the messes we are seeing right now would not have happened. Greed, when it becomes boundless it damages the brain and cripples the senses. I guess greed like leprosy diseases kill the senses. I watch, I see, I hear what is going on in every corner of the country. I am sorry, I can not find any other explanations and believe that is coming from sensible entity, thinking rational being.
    I am sorry, I am angry, sad and upset I do not what tell those arrogant, senseless, immoral, hateful bunch of groups.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule