• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓይን እያየ ወደገደል? ምን ይባላል!

August 29, 2016 04:47 am by Editor 2 Comments

በአገዛዙ ወንበር ላይ ተጣብበው የተቀመጡት ሰዎች ሁሉ ብዙ ቢሆኑ ይነጋገሩ ነበር፤ ቢነጋገሩ ሁሉም በየፊናውና በየአቅጣጫው በራሱ ዓይኖች ያየውንና በራሱ ጆሮዎች የሰማውን፣ በራሱ አእምሮ አብሰልስሎ እያቀረበ ክርክር ይፈጠር ነበር፤ ከክርክሩ የሚፈልቀው እሳት ከተለያዩ ሰዎች የሚወረወሩትን ሀሳቦች እያቀለጠ አዲስ መመሪያ ያወጣ ነበር፤ ነገር ግን ተጣብበው የተቀመጡት ተጣብቀው አንድ በመሆናቸው ዓይን የሚያየውና ጆሮ የሚሰማው አንድ ነው፤ አእምሮ ሲጨፈለቅና ሲጣበቅ ሕይወቱን ያጣል፤ ስለዚህም የታየውና የተሰማው ጎዳ ሆኖ ሲቀርብ ውጤቱም ጎዳ በመሆኑ ክርክር የለም፤ ክርክር አለመኖሩ የመካንነት ምልክት ነው፡፡

አገር ተረብሽዋል፤ ሥርዓት ጠፍቷል፤ መደማመጥ ተስኖናል፤ የገነፈለው ስሜት እያቀለጠ ወደሞት ጅረት እየወሰደን እንደሆነ ወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት ገና አልተገነዘቡም፤ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ተገንዝቦታል፤ በወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት በሚገነዘቡበት ጊዜ የሞት ጅረት አጥለቅልቆናል፤ መድኅን የሚመጣው ከሞት በፊት ነው፤ የዱሮ አዝማሪ እንዳለችው፡–

አንጀቴ ተቆርጦ ከሆዴ ከወጣ፣
እንግዲህ ሀኪሙ ምን ሊቀጥል መጣ!

ሳምሶን ‹‹ውጽዒ ነፍስየ ምስለ ነፍሶሙ፤›› ብሎ ምሰሶውን ገፍቶ እንደጣለው ዛሬም በወንበሩ ላይ የተጣበቁት ምሰሶውን ገፍቶ የመጣልና የሦስት ሺህ ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ ለማፈራረስ ጉልበቱ እንዳላቸው ያምኑ ይሆናል፤ ‹‹ውጽዒ ነፍስየ ምስለ ነፍሶሙ›› ለማለትና ውጤቱንም ለመቀበል ከቆረጡ ያለምንም ጥርጥር በቂ ጉልበት አላቸው፤ ነገር ግን ይህ ጉልበት የተባረከና የተቀደሰ አይደለም፤ ዝናብ እንደሚወርድበት ክምር ጨው ነው፤ ዝናቡ ከጉልበት ቁጥጥር ውጭ ነው፤ በዚያ ላይ አንድ የሁሉም አገር ታሪክ ያረጋገጠው እውነት አለ፤ አሸናፊ ይጠናከራል፤ ተሸናፊ ይዳከማል፤ ሕዝብ ተሸናፊ ሆኖም አያውቅ፡፡

በዚያ ላይ ወደእምነት ደረጃ ከፍ ስንል ኃያል እምኃያላን የሆነ አምላክ አለ፤ በጉልበታቸው የሚታበዩትን ይታገሳቸዋል እንጂ ለመጨረሻ ድል አያበቃቸውም፤ የደካሞቹንም ስቃይና መከራ የሚያበዛው የድል አክሊል አዘጋጅቶላቸው ይሆናል፤ ጉልበተኞች ከዕብሪታቸው ሲጸዱና የእግዚአብሔርን ኃያልነት ሲቀበሉ በነሱ ላይ ድልን ለተጎናጸፉት ያስተምራሉ፤ የጉልበተኛ ሥርዓት ወድቆ የሕግ ሥርዓት ይተከላል፤ አሸናፊም ተሸናፊም በሕግ ጥላ ስር ይተዳደራሉ፡፡

አሸናፊም ተሸናፊም አንድ ዋና ነገር ቦግ ብሎ እንዲታያቸው እመኛለሁ፤ ትግላቸውም ሆነ ውጤቱ የግል አይደለም፤ ከመሀከላቸው የአምባ-ገነንነት ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ቀስ በቀስ ትግሉን የግል እያደረጉ ሄደው በመጨረሻ ድሉንም የግል ያደርጉታል፤ ሌላ ቀርቶ ቤተ-ሰቦቻቸውንም ይረሳሉ፤ አሸናፊም ሆነ ተሸናፊ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ የብዙ ሰዎችን ትብብርና ከባድ መስዋእትነትን የከፈሉ ሰዎችን የያዘ ነው፤ እነዚህ በብዙ መንገድ ብዙ ዓይነት መስዋእት የከፈሉ ሰዎች ለሚቀጥሉት ትውልዶች የሚያወርሱት ብዙ ነገር አለ፤ ራሳቸውን ሀብታም ማድረጋቸውንና ሰዎችን እንደፈለጉ ሲቆርጡና ሲፈልጡ መኖራቸውን ማንም እንደውርስ አይቀበላቸውም፤ ዘመን አልፎበታል፤ ታሪክም አይሆንም፤ የተጋድሎ ታሪካቸው፣ ለነጻነት፣ ለእኩልነትና ለአገር ባለቤትነት የሚያበቃና ለተከታይ ትውልዶች ሁሉ አርአያ የሚሆን ታሪክ በኩራት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡

በቀል፣ ጭካኔና በስሜት መገዛት ውሎ አድሮ ያጋልጣል፤ የሀብታሙ (አያሌው)ና የተመስገን (ደሳለኝ) ተገቢውን ህክምና ማጣትና መሰቃየት በምድርም በሰማይም ያስቀጣል፤ ይህንን ባህል አድርገን እንዳንቀጥል እሰጋለሁ፤ አእምሮአችንን ጡንቻ ብቻ ስናደርገው የማሰብ ሥራውን ያቆማል፤ ጠላት ለሚባለው ሰው የተመኙለት ገደል ላይ ዓይኖችን ተክሎ መራመድ ራስን ወደዚያ ገደል ማስገባት ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ነሐሴ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Wondefraw says

    August 30, 2016 08:23 am at 8:23 am

    Long life for u it sensible writing now they should think in different mind.

    Reply
  2. Naji says

    September 1, 2016 01:37 am at 1:37 am

    Wishing you good health,many more years with strength and energy, you are truly and educator and national figure. You are absolutely correct when you said that those who are in leadership positions are guided and manipulated by a single mind attached to a single brain. If there had been honest dialogue and consensus all the messes we are seeing right now would not have happened. Greed, when it becomes boundless it damages the brain and cripples the senses. I guess greed like leprosy diseases kill the senses. I watch, I see, I hear what is going on in every corner of the country. I am sorry, I can not find any other explanations and believe that is coming from sensible entity, thinking rational being.
    I am sorry, I am angry, sad and upset I do not what tell those arrogant, senseless, immoral, hateful bunch of groups.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule