• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በህወሃት “የትግራይ ኩራት ተነክቷል” ባዮች አይለዋል

September 30, 2014 08:34 am by Editor Leave a Comment

የሰሞኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ካቢኔያቸውን “ከኋላ” አስከትለው ከፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ያካሄዱት የፊት ለፊት ንግግር ያስደሰታቸውና ያስኮረፋቸው ክፍሎች አሉ። “በህወሃት መንደር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ የመወከል ባለጊዜው ህወሃት ነው። ህወሃት የኢትዮጵያ ምልክትና ተምሳሌት ነው” የሚሉት ወገኖች ቀደም ሲል ሲሰማ የነበረውን “የትግሬ ኩራት ተነክቷል” ስሜት በገሃድ ሲያንጸባርቁ ታይቷል።

አስገድደው ከሚመሩት ህዝብ ይልቅ ለውጪው ዓለም በመስገድና በማጎብደድ ወደር እንደሌላቸው የሚነገርረላቸው አቶ መለስ meles at g20ሰሞኑን አቶ ሃይለማርያም ያገኙትን ዕድል አላገኙም። ከታላቋ አሜሪካ መሪ ጋር በግል የፊት ለፊት ወግ አላደረጉም። በተለያዩ መድረኮች ላይ በጅምላ ተገኝተው ከመጨባበጥና ውስን ቃላቶችን ሲለዋወጡ ከመታየቱ ውጪ ያላገኙትን ይህንን ዕድል አቶ ሃይለማርያም ማግኘታቸው ቅር ያሰኛቸው ክፍሎች “መለስ ከመሬት በታች ሆነው የዲፕሎማሲውን ስራ ሰርተው መድረኩን እንዳመቻቹ አስመስለው በተለያዩ መንገዶች መግለጻቸው የዚሁ የኩራታችን ተነካ ስሜት ነጸብራቅ ነው” የሚሉ ወገኖች አሉ።

ስብሰባው በኋይት ሃውስ እልፍኝ ወይም በተባበሩት መንግስታት ሳሎን ውስጥ አልነበረም የተካሄደው። ዓለምአቀፉ ሒልተን በሚያስተዳድረው የኒውዮርኩ ዋልዶርፍ አስቶሪያ ሆቴል አንድ ክፍል ውስጥ የአሜሪካ “ባንዲራ” እና የኢህአዴግ አርማ እንዲሰቀል ተደርጎ ንግግሩ መደረጉን ያወሱ ክፍሎች፣ ፕሬዚዳንት ኦባማ ምርጫ እየተቃረበ መሆኑንን ጠቁመው “የሲቪል ማኅበረሰቡ እንዴት መንቀሳቀስ እንዳለበት መታየት አለበት” በማለት ያነሱት ሃሳብ ከስብሰባው በላይ ሚዛን አንስቷል። ኢህአዴግ የመያዶች ህግ በሚል በማተም የዘጋውን የሲቪል ማኅበረሰቡን ተሳትፎ አስመልክቶ ኦባማ ማንሳታቸው ውሎ አድሮ የሚመነዘሩ ጉዳዮችን እንደሚያስነሳ አመላክቷል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም በፌስቡካቸው የለጠፉት የዚሁ የሆቴል ክፍል ስብሰባ በርካታ አስተያየት ተሰንዝሮበታል። “ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር አንተ መሆን አለብህ” ከሚሉት የስጋና የደም አስተያየት ጀምሮ የዚሁ የፊት ለፊት ንግግር የቀድሞው “ባለ ራዕይ” መሪ “ራዕይ” ፍሬ አጎምርቶ የመታየቱ ብስራት ተደርጎ ተወስዷል፤ ታምኗል። ክብሩና ታሪኩም ለመለስ መቃብርና አጽም ህይወት ማላበሻ የአበባ ጉንጉን በረከት ሆኖላቸዋል።meles and hailemariam

የመለስ ሞት ዱብዳ የሆነበት ህወሃት፣ ከዱብዳው ማግስት ጀምሮ መርዶውን ሚስጥር ያደረገው የርዕሰ መንበሩ ወንበር ለይስሙላም ቢሆን እንዳይወሰድ አስፈላጊውን ዝግጅት ለማድረግ እንደሆነ በወቅቱ ብዙ የተባለበት ጉዳይ ነው። የመለስን የጥድፊያ ሞት “የግፍ ዋጋ፣ የአምላክ ቅጣት” በማለት ጮቤ የረገጡ ቢኖሩም፣ በህወሃት መንደር ግን ዜናው መሬት የተደረመሰ ያህል ስሜታቸውን ያራደ፣ ከሞት ጋር እልህ የተጋቡ የሚመስሉ፣ በዚሁ እሳቤ መለስ ቢሞቱም ያሉ ለማስመሰል የተደረገውና እየተደረገ ያለው ግብ ግብ “አምልኮ መለስ” ማስረጃ እንደሆነ ብዙዎች ተችተዋል።

ከዩኒቨርሲቲ የዲንነት በርጩማቸው ጀምሮ የሚያውቋቸው ሃይለማርያምን “የቆረጣ አካሄድን የተካነ” ሲሉ ይገልጹዋቸዋል። የሲዳማን ብሄረሰብ ለማስደሰት ከክልል ፕሬዚዳንትነታቸው ተነስተው አቶ መለስ ኢህአዴግ ቢሮ የተዛወሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም፣ በብሄር ውክልና ማመጣጠን ሰበብ ምክትል ጠ/ሚ ከመባላቸው ሌላ መለስ ቢሮ ለመጠጋት የሳቸው ሚና የለበትም። እንዳው አጋጣሚ ነው በሚል የሚከራከሩ ሃይለማርያም በኦባማ አስተዳደር ጫና ወንበሩን እንዲይዙ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ ህወሃቶች ውሳኔው “የትግሬዎችን ኩራት የነካ” መሆኑንን በመግለጻቸው በተደጋጋሚ መመከራቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ዲፕሎማቶች ይገልጻሉ።

ለጎልጉል ቅርብ የሆኑ የአሜሪካ ዲፕሎማት ሰሞኑን እንደጠቆሙት ህወሃቶች “በኩራታችን ተወሰደ” ስሜት ሃይለማርያም ደሳለኝን በቀጣዩ ምርጫ በራሳቸው ሰው ለመተካት እየሰሩ መሆናቸውን አመልክተዋል። በተለያዩ ሚዲያዎች ቴድሮስ አድሃኖም ቀጣዩ ጠ/ሚ/ር ይሆናሉ ስለመባሉ ለተጠየቁት “ቴድሮስ የግራውን መስመር የማያውቁ በመሆናቸው አምባገነን፣ ፈላጭ ቆራጭ መሪ ሊሆኑ አይችሉም፤ መስፈርቱን አያሟሉም በሚል ፈተናውን ሊያልፉ የማይችሉ ተደርገው ስለመወሰዳቸው መረጃው አለኝ” ብለዋል።

“የህወሃት የስለላው ማሽን” የሚባሉትና በፈላጭ ቆራጭነቱ አግባብ ግንባር ቀደም እንደሆኑ የሚነገርላቸው “ዶ/ር” ደብረጽዮን ሌላው እጩ ናቸው። ለመጀመሪያ ጊዜ ጎልጉል ስማቸውን ጠቅሶ ለጠ/ሚኒስትርነት ህወሃት ወደ ግንባር እያቀረባቸው መሆኑንን መግለጹ አይዘነጋም። የመረጃችን ምንጭ የሆኑት እኚሁ ዲፕሎማት፣ “ዶ/ር” ደብረጽዮን አምባገነንና ፈላጭ ቆራጭ በመሆን መስፈርቱን የሚያሟሉ ቢሆኑም ዓለምአቀፍ እውቅና የሌላቸውና ለዚያ የሚበቁ እንደማይሆኑ በራሳቸው በህወሃት ሰዎች መታመኑን ጠቁመዋል።haile fortune

በቀጣዩ ምርጫ ህወሃቶች ዋናውን “የኢትዮጵያ ውክልና” የሚባለውን ወንበር መልሶ የመያዝ እቅድ እንዳላቸው በቂ መረጃ አሜሪካ እንዳላት የጠቆሙት ዲፕሎማት፣ ከህወሃት ቁልፍ ሰዎች መካከል ሃይለማርያም ደሳለኝ ምክንያት ተፈጥሮ በቀጣዩ ምርጫ እንዳይወዳደሩ የማድረግ ዕቅድ ስለመኖሩ መስማታቸውን ጠቁመዋል። “ለጊዜው መረጃው ጥሬ ነው” ሲሉም ዝርዝር ውስጥ ለመግባት እንደማይችሉ አመልክተዋል።

የመለስ ሞት ይፋ በሆነበት ቅጽበት አቶ ሃይለማርያምን ከህወሃት እውቅና ውጪ ያነገሱት በረከት ስምዖን “የወንበሩ የወቅቱ ባለንብረት ህወሃት ነው” በሚሉት ክፍሎች ጥርስ ተነክሶባቸው እንደነበር ምንጭ እየጠቀሱ በርካታ ሚዲያዎች መዘገባቸው አይዘነጋም። በመተካካት ከኢህአዴግ መንበር ይወገዳሉ ወይም ተወግደዋል የሚባሉት አንጋፋ የድርጅቱ መሪዎች ጥላቸውና እጃቸው መዋቅሩን ነክሶ በመያዙ አሁንም በቀጣዩ ምርጫ የሃይለማርያም ጉዳይ በነዚሁ ሰዎች እጅ እንደሆነ የሚጠቁሙ አሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule