• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በደቡብ ክልል የመሆን ጥያቄ ይቆይ፤ በዕርጋታ ይታይ – የክልሉ ነዋሪዎች አስተያየት

July 25, 2019 08:31 am by Editor Leave a Comment

ከ17ሺህ በላይ ሰዎች ያሳተፈው የሰባት ወር ጥናት ይፋ ሆኗል

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ በደቡብ ክልል የሚነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ምላሽ ለመስጠት ያስጠናው ጥናት ውጤት ዛሬ ይፋ ሆነ። በጥናቱ የተሳተፉት ክልል የመሆንን ጥያቄ በዕርጋታ እንዲታይ ተናግረዋል።

ላለፉት ሰባት ወራት በምሁራን የተካሄደው የደቡብ ክልል አዲስ አከላለልን የተመለከተው ጥናት ውጤትን በተመለከተ ጥናቱን ያካሄዱት ባለሙያዎች ረቡዕ ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የደቡብ ክልል የብዝሃነት ምልክት አብሮ የመኖር አርአያ መሆኑን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎች የክልል ምስረታ ጥያቄ በክልሉ በስፋት ቀርቧልም ብለዋል።

የጥናት ቡድኑ ከተለያዩ የትምህርት ዘርፎች የተውጣጡ ምሁራንን የያዘ ሲሆን፥ ምሁራኑ በአንትሮፖሎጂ፣ ታሪክ፣ የሕዝብ አስተዳደር፣ ፖለቲካ ሳይንስና ፌዴራሊዝም ተመራማሪና ልሂቃን ናቸው።

በጥናቱ ከአንድ ዞን በስተቀር በሁሉም የደቡብ ክልል ዞኖች የተውጣጡ ከ17 ሺህ በላይ ሰዎች መረጃ ተስብስቧል። ጥናቱ የ1987ቱን የደቡብ ክልል አደረጃጀት ሂደት፣ የክልሉ ሕዝቦች በአከላለሉ ያገኙት ትሩፋት እና የአዳዲስ ክልሎች ምስረታ ጥያቄ መንስኤዎች ተዳስሰዋል።

የ1987ቱን የደቡብ ክልል አወቃቀር በፌዴራል መንግስት ውሳኔ በዘፈቀደ ነው ወይስ የክልሉ ህዝብ ተሳትፏል በሚለው ጉዳይ ህዝብ የሰጠው ምላሽ የደቡብ ክልል በመንግሥት ተጠፍጥፎ የተሠራ አይደለም የሚል ሆኗል። የክልሉ ምሁራን ያለ መንግሥት ተፅእኖ ክልሉ በደቡብ ክልልነት እንዲመሠረት ተስማምተው ክልሉ መመሥረቱን ተናግረዋል።

የጥናት ቡድኑ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንዳሉት 20 አባላት ያሉት የጥናት ቡድን ተዋቅሮ ላለፉት ሰባት ወራት ሰፊ ጥናት ሲያካሂድ ቆየቷል። በዚህም መሠረት ሶስት አማራጮችን አስቀምጧል ብለዋል ምክትል ሰብሳቢዋ።

በጥናቱ የተለየው የመጀመሪያው አማራጭ አብዛኛው የክልሉ ሕዝብ አሁን ያለው የክልሉ አደረጃጀት ቢቀጥል የሕዝቦችን አብሮነትና ያጠናክራል፤ ጠንካራ የደቡብ ሕዝቦች ክልልንና የኢትዮጵያን አንድነት ያጠናክራል የሚል ነው።

በጥናቱ የተለየው መጀመሪያ አማራጭ አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሮ ተቀባይነት የሚያጣ ከሆነ በጥናቱ በሁለተኝነት የተለየው አማራጭ ደግሞ ክልሉን በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በመክፈል ከዚህ በፊት ይነሱ የነበሩ የፍትሐዊነት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ማድረግ ነው።

በጥናቱ በሶስተኝነት የተቀመጠው ሃሳብ ደግሞ ሁለቱ አማራጮች ተግባራዊ የማይሆኑ ከሆነና ሁኔታው ከክልል አልፎ በአገሪቱ ሰላምና አንድነት ላይ ጫና የሚፈጥር ከሆነ ጉዳዩ ለጊዜው ቢቆይና በእርጋታ ቢታይ የሚል ነው። እንደጥናት ቡድኑ ምክትል ሰብሳቢ ከ17 ሺህ በላይ ሰዎች በላይ ለጥናቱ በመረጃ ሰጪነት ተሳትፈዋል።

ጎልጉል ከኢፕድና ከፋና ካገኘው ዜና ያጠናቀረው

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule