• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦባንግ ከቴላቪቭ ባለስልጣናት ጋር ይመክራሉ

June 25, 2013 03:10 am by Editor 3 Comments

እስራኤል ኢትዮጵያ ውስጥ በህዝብ ፍላጎት የሚመረጥ የተረጋጋ መንግስት እንዲቆም ከመቼውም ጊዜ በላይ የምትንቀሳቀስበት ወቅት ላይ መሆኗን ለማሳሰብ በነገው እለት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ። የሒብሩ ዩኒቨርስቲ ምሁራንና ማህበረሰብ ለአቶ ኦባንግ መልክት ድጋፍ እንዲያደርጉ የሚጠይቅ ንግግር ያደርጋሉ። በእስራኤል የሚኖሩ ስደተኛ ወገኖችን አስመልክቶ ቃል እንደተገባላቸውም አመልክተዋል። አቶ ሳሙኤል አለባቸው “መኖርና መሞት ስላለ ወደ ህሊናችን ልንመለስ ይገባል” አሉ።

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር የአሜሪካ እንደራሴ (ኮንግረንስማን) ክሪስ ስሚዝ በመሩት የምክክር ሸንጎ ላይ ንግግርና ማብራሪያ ካሰሙ በኋላ ወዲያውኑ በቀጥታ ወደ እስራኤል አምርተው ነበር። ለሁለት ጉዳዮች ወደ እስራኤል ያመሩት አቶ ኦባንግ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ከእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በነገው ዕለት እንደሚመክሩ ለጎልጉል ሲያስታውቁ ስለሚናገሩበት ጉዳይም ፍንጭ ሰጥተዋል።

የሚያገኟቸውን ባለስልጣናት ሳይዘረዝሩ ስለ ምክክሩ የተናገሩት አቶ ኦባንግ “ዛሬ እስራኤል ኢትዮጵያ ላይ ህዝብ አምኖና መርጦ የሚያቆመው መንግስት እንዲመሰረት ከማንም በላይ መስራት እንዳለበት ወቅታዊ እውነቶችን በማንሳት አሳስባለሁ” ብለዋል። “እስራኤል” አሉ ጥቁሩ ሰው “እስራኤል አሁን ባለው የኢህአዴግ ተጨባጭ ሁኔታ ዝምታን አትመርጥም። ዝም ልበል ካለች የመጀመሪያዋ ተጎጂ አገር ትሆናለች። የምንግባባበት ወቅት ላይ ስለደረስን በማስረጃ እንነጋገራለን። ቀና ምላሽ እንጠብቃለን” በማለት አስረድተዋል፡፡hebrew-university

ምክክሩ እንዴት ሊዘጋጅ እንደቻለ ተጠይቀው “እቅድ ተይዞለት የተሰራ፣ ጊዜው ሲደርስ የተደረገ” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። በሒብሩ ዩኒቨርስቲ የሕግ ፋኩልቲ ተገኝተው ለምሁራኖችና ተተኪ ፖለቲከኞችና የአዲሱ ትውልድ አባላቶች ንግግር እንደሚያቀርቡ አቶ ኦባንግ አስገንዝበዋል።

በዩኒቨርስቲው በሚያደርጉት ንግግር የሁሉንም ስሜት የሚነካ፣ ከራሳቸውና ከኢትዮጵያ ህዝብ ፍላጎት አንጻር  የወደፊቱን በመተንበይ መንግስታቸው ኢትዮጵያ ላይ ያለውን አቋም በተረጋጋ መሰረት ላይ እንዲተክል የቀረበለትን ጥሪ እንዲቀበል ድጋፍ እንዲያደርጉ እንደሚጠይቁ ታውቋል።

በህንድ አገር ያቀረቡትን የትግል ጥሪ ተቀብለው ካራቱሪ ላይ ዘመቻ የጀመሩ “የመሃትማ ጋንዲ ፍሬዎች”  መገኘታቸውን አቶ ኦባንግ አስታውሰዋል። አሁንም በነጻ አውጪ ሰም አገር እየመራ ያለው ህወሃት እየፈጸመ ያለውን አሰቃቂ ተግባር ናዚ ከፈጸመው ተግባር ጋር እንዲመዝኑት በስፋት በመረጃ የተደገፈ ንግግር እንደሚያደርጉ ከገለጻቸው ለመረዳት ተችሏል። ስራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ዝርዝር ማብራሪያ እንደሚያቀርቡም አመልክተዋል።

አቶ ኦባንግ እስራኤል ስለሄዱበት ሌላው አንገብጋቢ ጉዳይ ሲያስረዱ፣ በመጀመሪያ የገለጹት “በመደራጀት ድል ይገኛል” በሚል መገረማቸውን በመግለጽ ነው። የተደረገላቸው አቀባበል ልባቸውን እንደነካው፣ የተሰራው ስራና የተገኘው ውጤት ደግሞ እንዳረካቸው የገለጹት የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል አመራር አባላትን በማመስገን ነው።

ከተቋቋመ አስር ወር ያልሞላው ማህበር በእስራኤል የኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት ውስጥ እየሰሩ የዜጎችን መረጃ በማበላሸት፣ በማስተርጎም ስራ ወቅት መረጃ በማዛባት፣ በማሳሳትና ዓ.ም. በማሳከር የስደት ማመልከቻቸው እንዲበላሽ ሲያደርጉ የነበሩ የህወሃት አባላት ላይ ማስረጃ በማሰባሰብ ባካሄዱት ትግል ድል ተቀዳጅተዋል። የእስራኤል የኢሚግሬሽን መስሪያ ቤት የቀረበለትን ማስረጃ ተመልክቶ የወያኔ አባላት የሆኑትን ሰራተኞች እንዲያስወግድ የተደረገው ጥረት አድካሚ እንደነበር ወ/ሮ ጽጌ ማርያም አቤ ለጎልጉል ተናግረዋል።israel israel 1

የማህበሩ የፋይናንስ ሃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ጽጌ ማሪያም አብረዋቸው የሚኖሩ የህወሃት ደጋፊዎች አገር ቤት እንደሚያደርጉት በማስፈራራት፣ በካሜራና በቪዲዮ በመቅረጽ ምስላችንን ለኤምባሲ በመስጠት፣ ወደ አገር ቤት የሚሄዱ እንደሚታሰሩ ወዘተ ተግባራት በመዘርዘር እንደሚያስፈራሩ አመልክተዋል። አገሩ ግን ኢትዮጵያ ባለመሆኑ ከጫጫታ እንደማያልፍ የተናገሩት ጽጌ ማርያም፣ “ስንሰባሰብ፤ ገንዘብ በመሰብሰብ አሸባሪዎችን ሊረዱ ነው። የአክራሪ ደጋፊዎች ናቸው፤ ወዘተ በሚል ለፖሊስ ይከሱናል። አሁን ግን ሁሉም ዝምታውን ሰብሮ ተባብሯል። እነሱም ሟምተዋል” ብለዋል።

የማህበሩ ጸሐፊ አቶ ጥላሁን በሻህ በበኩላቸው ከትናንት በስቲያ አቶ ኦባንግ በተገኙበት በተካሄደው ስብሰባ ላይ የተገኙት የህወሃት ሰዎች ስብሰባውን ለማወክ ጥረት አድርገው አንደነበር አመልክተዋል። አቶ ኦባንግን ጥያቄ እንጠይቃለን በማለት “አንተ ኢትዮጵያዊ አይደለህም” በማለት ለመዛለፍ እንደሞከሩም ተናግረዋል። ስብሰባው ሲጀመር አገር ቤት ህወሃት በበደኖ ያስፈጸመውን ጭፍጨፋ ያካተተ ቀንጭብ ምስል (ቪዲዮ ክሊፕ) መታየቱ ያናደዳቸው የህወሃት ደጋፊዎች “ይህ በኃይለሥላሴ አስተዳደር ወቅት የተፈጸመና እናንተ ቆርጣችሁ ቀጥላችሁ ያዘጋጃችሁት ነው” ማለታቸውን አቶ ጥላሁን ተናግረዋል።

በበደኖ እልቂት ቤተሰቦቿን ያጣች አንድ እህት ባጋጣሚ ስብሰባው ላይ ተገኝታ ስለነበር በሰማቸው ክህደት የተነሳ ራስዋን መቆጣጠር ተስኗት እያነባች መነሳቷን አቶ ጥላሁን ያስታውሳሉ። ጭፋጨፋውን ህወሃት በውክልና አስፈጽሞ ከኦነግ ጋር ሲጣላ ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ጭፋጨፋው ከተከናወነ ከሁለት ዓመት በኋላ  ይፋ መሆኑንን “እኔ እማኝ ነኝ” በማለት መናገሯን አመልክተዋል።

በስብሰባው ላይ የተገኙ ወገኖች ቢበሳጩም ራሳቸውን በመቆጣጠርና አስቀድሞ በማህበሩ በተሰጠ መመሪያ መሰረት በሰላም የተፈለገለትን ዓላማ አሳክቶ መጠናቀቁን አቶ ጥላሁን አስረድተዋል። ከአቶ ጥላሁን በሻና ጽጌ ማርያም አቤ ጋር ያደረግነውን ቃለ መጠይቅ ሙሉ ሪፖርት በቀጣይ እናቀርባለን።

በስብሰባው ላይ “ኢትዮጵያዊ አይደለህም” የተባሉት አቶ ኦባንግ ምን ምላሽ እንደሰጡ ተጠይቀው “ምን ምላሽ እሰጠዋለሁ! ከመለስ የሚገኘው ትምህርት ውጤቱ ይህ ነው። የመለስ ፍሬዎች መጠናቸው እዚህ ድረስ ነው። እኔም ሆንኩ መላው ጋምቤላ ህዝብ ስለ ኢትዮጵያዊነታቸው ጥያቄ ሲያቀርቡ ተሰምቶ አይታወቅም። ለአገራቸው ከመሞት ውጪ በባንዳነት ስማቸው ተነስቶም ሆነ ተከስሰው አያውቅም። እንዲህ ዓይነት ሰዎችን ጭምር ነጻ ለመውጣት እንደምንሰራ ግን ነግሬያቸዋለሁ። እምነታችን ጥላቻ ስላልሆነ ላይገባቸው ይችላል። እኛ እንደዚህ ነን” ብለዋል።israel meeting

ጉባኤው በእስር ላይ ባሉት የሰላም ታጋይ አቶ አንዷለም አራጌ ስም የተሰየመ ሲሆን ማህበሩ ከጎናቸው መቆሙን ለመግለጽ ውስን አንድ ሺህ ዶላር ለቤተሰብ ለማድረስ መወሰኑን አስታውቋል። በስም የሚታወቁና የማይታወቁትን የህሊና እስረኞች ከልብ ለመደገፍና አለኝታነታቸውን ለመግለጽ ወደፊትም እንሰራለን ብለዋል። አዳዲስ መሪዎችንም እናበረታታለን ብለዋል።

የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ሳሙዔል አለባቸው ጉባኤውን ሲከፍቱ “መኖር አለ፤ መሞት አለ። በጉባኤው ላይ ገለልተኞች፣ ተቃዋሚዎችና አገር ቤት ያለውን አገዛዝ የሚደግፉ አሉ። ሁሉንም መሆን ይቻላል ግን በስርዓት እናድርገው” በማለት ተናግረዋል። አቶ ኦባንግ ከሚመሩት የጋራ ንቅናቄ ጋር በመሆን በጀመሩት ፕሮጀክት በስደት ከለላ ካገኙ በኋላ ወገኖቻቸውን የሚሰልሉትን በማጋለጥና በወንጀል ለማስቀጣት ከፍተኛ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል። ሰማያዊ ፓርቲ ለፈጸመው ታላቅ ተግባርና ህዝብ ለፈጸመው አኩሪ ገድል ክብር እንዳላቸው አመልክተዋል። ለጉባኤው መሳካት ትብብር ላደረጉላቸው ሚዲያዎች ምስጋና አቅርበዋል። የሽግግር ካውንስል ላደረገላቸው ተደጋጋሚ ትብብር ያላቸውን አድናቆት ሰንዝረዋል። የአቶ ኦባንግ በመካከላቸው መገኘት ታላቅ ክብር እንደተሰማቸው አስታውቀዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mfas says

    June 25, 2013 03:40 pm at 3:40 pm

    Selam!! Ezy ene balehubet hager (JOBURG) y-kale meteyek geze astergamy honew yeseru yetechawetuben alu!!!! Aun degmo tekawamywoch nen eyalu newe!! Abzangochachenem werketachen seletebelashe mewcha belen yeyazenew pasport newe! Enezy sewoche ahun enkoan des yemil sera ayserum!! Yemikefafel sera siseru newe yemitayut! Egnanes man yetadegen?

    Reply
    • Basso Orana says

      July 13, 2013 07:51 pm at 7:51 pm

      Ayezowachihu! semachewun le eprp.com lakulachew

      Reply
  2. Mario says

    June 28, 2013 04:44 am at 4:44 am

    አቶ ኦባንግ ሜቶ ታልቅ ሰው ናቸው:: ላገርቸው እና ለህዝባቸው ከማንም በላይ ይሰራሉ:: ሲሰሩ ምሳሌ በመሆን ነው:: ሌሎቻችን ከርሳቸው የምንማረው ብዙ ነገር አለ:: በተለይ በተለይ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራር ላይ ያሉ ግለሰቦች ሁሉ ከርሳቸው የሚማሩት ብዙ ነገር ስላለ በጣም ሊያስቡበት ይገባል:: አስበውበት ቢሆብ ኖሮ እንደ አቶ ኦባንግ ሜቶ አይነት አክትቪስቶችት (activists) እና ታጋዮች በብዛት ይኖረን ነበር::

    ረጅም እድሜ እና ጤና ለአቶ ኦባንግ ሜቶ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule