• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ

January 25, 2021 01:02 pm by Editor Leave a Comment

ጁንታው ትግራይን ለ፴ ዓመታት ያስተዳደረው በሴፍቲ ኔት ነው

በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ እንዳልሆነ ተደርጎ የሚናፈሰው ወሬም ከእውነት የራቀ ነው አሉ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ።

የፌዴራል መንግሥት በክልሉ የተጠናከረ ሰብአዊ ድጋፍ እያደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል። “ድጋፉ እየቀረበ አይደለም” በሚል ሃሰተኛ መረጃ የሚያናፍሱ አካላት የፖለቲካ ትርፍ በመፈለግ የሚፈጽሙት ድርጊት ነው ሲሉም ገልፀዋል።

በክልሉ የመብራት፣ የውሃ እና የባንክ አገልግሎቶች በበርካታ አካባቢዎች መጀመራቸውን አንስተው፤ አገልግሎት ባልተጀመረባቸው አንዳንድ አካባቢዎች ደመወዝ ላልተከፈላቸው የመንግስት ሰራተኞች እንዲከፈላቸው እየተሰራ ነው ብለዋል።

ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ሙሉ ነጋ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ የትግራይ ሕዝብ ካለበት የባሰ ሰብዓዊ ችግር ውስጥ እንዳይገባ የፌደራል መንግሥቱ በከፍተኛ ትኩረትና ቁርጠኝነት አጋርነቱን እያሳየ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። እስከ አሁን ባለው ሁኔታ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚደርስ ሕዝብ እርዳታ እንደሚፈልግ መገመቱን ጠቁመዋል።

ጁንታው በስልጣን ላይ በነበረባቸው ወቅቶች በክልሉ ቁጥራቸው ከፍ ያለ የህብረተሰብ ክፍሎች በሴፍቲኔት እየታገዙ ይኖሩ ነበር። አሁን ደግም በሕግ ማስከበር ዘመቻው ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ተጨማሪ ድጋፍ ፈላጊ መሆናቸውን አመልክተዋል።

የኤሌክትሪክ፤ የቴሌኮምና ባንክ አገልግሎቶች ተቋርጦ በመቆየቱ ምክንያት ከዚህ ቀደም ድጋፍ የማይፈልጉ ሁሉ አሁን ድጋፍ ፈላጊ ሆነዋል፤ የፌደራል መንግሥቱ ይህንን ሁኔታ ከግምት በማስገባት ህብረተሰቡ የተባባሰ ችግር ውስጥ እንዳይገባ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰራና እያገዘ መሆኑን አስታውቀዋል።

እንደ ዶክተር ሙሉ ገለጻ ከዚህ ቀደም በክልሉ የነበረው የኢኮኖሚ እድገት ጥሩ ቢሆን ኖሮ ለጥቂት ጊዜያት እንኳን ይህንን ችግር ማለፍ ይቻል ነበር፤ ሆኖም ክልሉ ቀድሞም የተጎዳ ስለነበር እንደዚህ ዓይነት ችግር ሲጨመርበት ከፍተኛ የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ተከስቷል ብለዋል።

ጁንታው ቡድን ጦርነት የለኮሰበት ወቅት አርሶ አደሩ የዘራውን ምርት በሚሰበስብበት ጊዜ መሆኑ ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ እንዳባባሰው የተናገሩት ዶክተር ሙሉ፣ በዚህም በክልሉ የተሰበሰበ ምርት የለም፤ የእርዳታና የድጋፍ ፍላጎቱም ይህንን ሁሉ ከግምት ያስገባ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

“አሁን እንደ መጀመሪያ ገንዘብ ያለውም ሰው እርዳታ ማግኘት ይፈልጋል፤ ሆኖም ባንኮች ወደ ስራ እየገቡ በመሆኑ ህብረተሰቡ ገንዘብ ማውጣት ከጀመረ የተረጂው ቁጥር ይቀንሳል። እስከ አሁን ባለው ሁኔታ ግን 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ እርዳታ እንደሚፈልግ ይገመታል፤ እዚህ ላይ ግን ቁጥሩ ከዚህም ሊጨምር ይችላል” ብለዋል።

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ በመቀሌ ከተማ ድገፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ርዳታ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የመቀሌ ከተማ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ሃይለስላሴ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በከተማዋ ለሚኖሩና ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው ለመጡ 379 ሺህ አቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል  ዝግጅት ተጠናቆ ርዳታ እየቀረበ ይገኛል።

እንደ አቶ አታኽልቲ ገለጻ፤ እስካሁን ለ180ሺ ዜጎች ስንዴ እና ዱቄት እንዲሁም ለህጻናት ደግሞ አልሚ ምግቦች ተሰጥቷል።

የተቀሩት ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ደግሞ በቀጣይቀናት ውስጥ እርዳታው እንደሚሰጣቸው  ከንቲባው ገልፀዋል።

የትግራይ ክልልን መልሶ በመገንባት ሂደት ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ አመራሮቹ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule