• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ

January 25, 2021 01:02 pm by Editor Leave a Comment

ጁንታው ትግራይን ለ፴ ዓመታት ያስተዳደረው በሴፍቲ ኔት ነው

በትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ እንዳልሆነ ተደርጎ የሚናፈሰው ወሬም ከእውነት የራቀ ነው አሉ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉ ነጋ።

የፌዴራል መንግሥት በክልሉ የተጠናከረ ሰብአዊ ድጋፍ እያደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል። “ድጋፉ እየቀረበ አይደለም” በሚል ሃሰተኛ መረጃ የሚያናፍሱ አካላት የፖለቲካ ትርፍ በመፈለግ የሚፈጽሙት ድርጊት ነው ሲሉም ገልፀዋል።

በክልሉ የመብራት፣ የውሃ እና የባንክ አገልግሎቶች በበርካታ አካባቢዎች መጀመራቸውን አንስተው፤ አገልግሎት ባልተጀመረባቸው አንዳንድ አካባቢዎች ደመወዝ ላልተከፈላቸው የመንግስት ሰራተኞች እንዲከፈላቸው እየተሰራ ነው ብለዋል።

ሥራ አስፈጻሚው ዶክተር ሙሉ ነጋ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ የትግራይ ሕዝብ ካለበት የባሰ ሰብዓዊ ችግር ውስጥ እንዳይገባ የፌደራል መንግሥቱ በከፍተኛ ትኩረትና ቁርጠኝነት አጋርነቱን እያሳየ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። እስከ አሁን ባለው ሁኔታ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚደርስ ሕዝብ እርዳታ እንደሚፈልግ መገመቱን ጠቁመዋል።

ጁንታው በስልጣን ላይ በነበረባቸው ወቅቶች በክልሉ ቁጥራቸው ከፍ ያለ የህብረተሰብ ክፍሎች በሴፍቲኔት እየታገዙ ይኖሩ ነበር። አሁን ደግም በሕግ ማስከበር ዘመቻው ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ተጨማሪ ድጋፍ ፈላጊ መሆናቸውን አመልክተዋል።

የኤሌክትሪክ፤ የቴሌኮምና ባንክ አገልግሎቶች ተቋርጦ በመቆየቱ ምክንያት ከዚህ ቀደም ድጋፍ የማይፈልጉ ሁሉ አሁን ድጋፍ ፈላጊ ሆነዋል፤ የፌደራል መንግሥቱ ይህንን ሁኔታ ከግምት በማስገባት ህብረተሰቡ የተባባሰ ችግር ውስጥ እንዳይገባ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየሰራና እያገዘ መሆኑን አስታውቀዋል።

እንደ ዶክተር ሙሉ ገለጻ ከዚህ ቀደም በክልሉ የነበረው የኢኮኖሚ እድገት ጥሩ ቢሆን ኖሮ ለጥቂት ጊዜያት እንኳን ይህንን ችግር ማለፍ ይቻል ነበር፤ ሆኖም ክልሉ ቀድሞም የተጎዳ ስለነበር እንደዚህ ዓይነት ችግር ሲጨመርበት ከፍተኛ የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ተከስቷል ብለዋል።

ጁንታው ቡድን ጦርነት የለኮሰበት ወቅት አርሶ አደሩ የዘራውን ምርት በሚሰበስብበት ጊዜ መሆኑ ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ እንዳባባሰው የተናገሩት ዶክተር ሙሉ፣ በዚህም በክልሉ የተሰበሰበ ምርት የለም፤ የእርዳታና የድጋፍ ፍላጎቱም ይህንን ሁሉ ከግምት ያስገባ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

“አሁን እንደ መጀመሪያ ገንዘብ ያለውም ሰው እርዳታ ማግኘት ይፈልጋል፤ ሆኖም ባንኮች ወደ ስራ እየገቡ በመሆኑ ህብረተሰቡ ገንዘብ ማውጣት ከጀመረ የተረጂው ቁጥር ይቀንሳል። እስከ አሁን ባለው ሁኔታ ግን 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን የሚደርስ ሕዝብ እርዳታ እንደሚፈልግ ይገመታል፤ እዚህ ላይ ግን ቁጥሩ ከዚህም ሊጨምር ይችላል” ብለዋል።

በሌላ በኩል በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ በመቀሌ ከተማ ድገፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ ርዳታ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የመቀሌ ከተማ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ሃይለስላሴ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በከተማዋ ለሚኖሩና ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው ለመጡ 379 ሺህ አቅመ ደካሞችና አረጋዊያን ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል  ዝግጅት ተጠናቆ ርዳታ እየቀረበ ይገኛል።

እንደ አቶ አታኽልቲ ገለጻ፤ እስካሁን ለ180ሺ ዜጎች ስንዴ እና ዱቄት እንዲሁም ለህጻናት ደግሞ አልሚ ምግቦች ተሰጥቷል።

የተቀሩት ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ደግሞ በቀጣይቀናት ውስጥ እርዳታው እንደሚሰጣቸው  ከንቲባው ገልፀዋል።

የትግራይ ክልልን መልሶ በመገንባት ሂደት ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ አመራሮቹ ጥሪ ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule