• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኤርትራ መንግሥት አልተገለበጠም

January 22, 2013 03:08 am by Editor 5 Comments

“ኩዴታ ሲደረግ በቅድሚያ በቁጥጥር ስር ሊውል የሚገባው የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ጣቢያ ነው። በአስመራ  ይህ ስለመሆኑ የተባለ ነገር የለም። ታዲያ እንዴት ነው ኩዴታ ተከናውኗል ሊባል የሚችለው? በርግጥ ገለልተኛና ነጻ የውጪ ሚዲያዎች አለመኖራቸው የመረጃውን መጠንና ጥራት ቢገድበውም እስካሁን የሚወጡት መረጃዎች እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ እንጂ የማስገደድ አይመስልም። በዚህ መነሻ ኢሳያስ ሙሉ በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው ማለት አይቻልም። ግን የመደራደር ነገር ሊኖር ይችላል” አውሮፓ የሚኖር ኤርትራዊ ለጎልጉል የተናገው ነው።

አስር ሺህ የሚደርሱ የፖለቲካ እስረኞች እንዳሏት የሚነገርላት ኤርትራ ዛሬ አመሻሹ ላይ አዲስ ዜና አሰምታለች። የተቀየሙ የጦር ሃይሎች የማስታወቂያ ሚኒስቴርን ከበው የፖለቲካ እስረኞች እንዲለቀቁ በማስገደድ ላይ እንደሆኑ የተለያዩ የዓለም መገናኛዎች እየዘገቡ ነው። የመፈንቅለ መንግሥት መደረጉንና ፕሬዚዳንት ኢሳያስ እንዳበቃላቸው የገለጹም አሉ። ተቃዋሚዎችን ጨምሮ፡፡

የጎልጉል ዝግጅት ክፍል በቀጥታ አስመራ በመደወል ባገኘው መረጃ መሰረት ዋናውን አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቁጥራቸው ከፍተኛ የተባለ ወታደሮች ተቆጣጥረውታል። ወታደሮቹ አፍቃሪ ኢሳያስ የሚባሉት ይሁኑ፣ አፈነገጡ የተባሉት ለማጣራት ግን አልቻለም። “ከተለመደው ውጪ በርካታ ወታደሮች ይመላለሳሉ። አውሮፕላን ጣቢያው ጤነኛ እንቅስቃሴ አይታይበትም” በማለት የተመለከተውንና የታዘበውን ይገልጻል። አያይዞም በከተማዋ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከወትሮው የተለየ እንደሆነ ተናግሯል።

የቴሌቪዥን ጣቢያ የአገር ውስጥ ስርጭቱ እንደተቋረጠ የነገረን የአስመራ ነዋሪ፣ ህዝቡ ሁኔታውን የተረዳና አንድ ነገር እንደሚፈጠር የተረዳ በሚመስል መልኩ ተረጋግቶ ሁኔታዎችን እየተከታተለ እንደሆነ አስታውቋል። በኤርትራ ሁለተኛ ታላቅ ከተማ የምትባለው ባጽዕ (ምጽዋ) ኩዴታ ባከናወኑት ሃይሎች እጅ እንደሆነች መስማቱንም ይናገራል።

አዲስ አበባ መቀመጫቸውን ያደረጉት የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ተቃዋሚዎች ለአልጃዚራ እንደተናገሩት የጦር ሃይሉ በኑሮ ውድነት ተማሯል። እለት እለት እየተባባሰ በመጣው የኑሮ ቀውስ መንግስትና ወታደሩ አለመተማመን ደረጃ መድረሳቸውን ከመጠቆም ውጪ በትክክል ምን እየተደረገ እንደሆነ አልገለጹም።

አስመራ የውጪ አገር መገናኛዎችና ገለልተኛ የዜና ወኪሎች ባለመኖራቸው እስካሁን ትክክለኛና ሁሉንም ወገኖች ያካተተ መረጃ አልተሰማም። ይሁን እንጂ በተባበሩት መንግስታት የኤርትራ አምባሳደር አርአያ ደስታ “ምንም ችግር የለም፣ ሁሉም ነገር መፍትሄ ተበጅቶለታል። ሁሉም ነገር መልካም ነው” ሲሉ ለአልጃዚራ አስታውቀዋል።

ታዛቢዎች እንደሚሉት የታሰሩት የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ከሚጠይቁት ውጪ የመፈንቅለ መንግሥት ይዘት እንደማይታይ ይናገራሉ። በሌላ በኩል ግን ኢሳያስ አስመራ እንደማይገኙና ምን አልባትም ምጽዋ እንደሚገኙ የሚጠቁሙት ክፍሎች የኤርትራ መንግስት ኮማ ውስጥ ስለመሆኑ ከበቂ በላይ ምልክቶች እንዳሉ ይናገራሉ። ከአስመራ በስልክ ያነጋገርነው የከተማዋ ነዋሪ እንዳለው ባጽዕ (ምጽዋ) ያለው ሃይል ከከዳ በርግጥም ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ችግር ውስጥ ናቸው ማለት እንደሆነ ገልጾዋል።

በመጨረሻ ባገኘነው መረጃ ኤርትራ ውስጥ መንግስት እንዳልተገለበጠና መንግስትን ለመገልበጥ የሚያስችል እንቅስቃሴ አለመስተዋሉን ነው። ፕሬዚዳንቱ በትክክል ያሉበት ባይገለጽም በቅርብ በመከታተል መመሪያ በመስጠት ላይ እንደሆኑ ከአስመራ በስልክ ሰምተናል። አፈንጋጮቹን ለሚመሩት  የጦር መኮንኖች የፖለቲካ እስረኞች የሚፈቱበት አግባብ እንደሚመቻች ቃል መግባታቸውም ተነግሯል።

የአሜሪካ ሬዲዮ አላዝቦ ያቀረበው ዜና  አማጺ ያላቸው ወታደሮች የማስታወቂያ ሚኒስቴርን በመቆጣጠር የታሰሩ እንዲፈቱ፣ እኤአ በ1997 የተዘጋጀው ህገመንግስት ይከበር የሚል መግለጫ በማስገደድ ማስነበባቸውን አስደምጧል።ዘግይቶ የደረሰን ዜና በማለት አሜሪካ ዜጎቿ ወደ አስመራ የሚያደርጉትን ጉዞ እንዲገድቡ ትዕዛዝ መስጠቷን ተናግሯል።

አፈንጋጮቹ በግዳጅ ላይ ካለው የጦር ሃይል ዘንድ ስላላቸው የጠበቀ ግንኙነት እስካሁን የተባለ ነገር የለም። ይሁን እንጂ የማስታወቂያ ሚኒስቴርን በመቆጣጠር አስገድደው ያስነበቡትን መግለጫና የፖለቲካ አስረኞች ይፈቱ ጥያቄ ተከትሎ ከዋናው ስቱዲዮው በመቀበል ዜናውን የሚያሰራጨውን መስመር (ዋናውን አንቴና) እንዲቋረጥ በታዘዘው መሰረት ዜናው የጦር ሃይሉና ህዝብ ጆሮ በሚፈለገው ደረጃ እንዳልተዳረሰ ለማወቅ ተችሏል። አስመራ ያልተለመደ የወታደሮች እንቅስቃሴ ከመታየቱ በቀር ሁሉም ነገር የተረጋጋና የመንግስት ማስወገድ እንቅስቃሴ አለ የሚያስብል አይስተዋልም።

(ፎቶ፡ madot)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ast says

    January 22, 2013 04:30 am at 4:30 am

    Fair and balanced reporting from an Ethiopian website. gd job

    Reply
    • Milkias berhane says

      January 22, 2013 12:31 pm at 12:31 pm

      Be eritrea guday lay mizanun yetebek report ke ethiopian web lay saneb lemejemeria new thank yuo GOLGUL

      Reply
  2. Jimma says

    January 23, 2013 04:03 pm at 4:03 pm

    For a simple argument let us say the current government of Eritrea is gone. What good will that bring to the nation? Can we not learn what is happening in the rest of the world with likes of Somalia, Libya, Egypt and the mess we see in Syria. I am not a supporter of removing Mr. Isaias by force. It will create a huge problem that will not be resolved in years to come. Think people! Hardship is better than bloodshed!!

    Reply
  3. Azeb says

    January 24, 2013 10:02 pm at 10:02 pm

    The photo is dated!

    Reply
  4. andnet berhane says

    February 20, 2013 11:33 pm at 11:33 pm

    ባጠቃላይ የነበረው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ድራማ ለመሆኑ ከይዞቱና አቶ ኢሳያስ ቃለመጠየቅ እምንወስዳቸው ቁምገሮች አሉ ለመሆኑ በብዙ ሃገራት ኩዴታ በሚካሄድበት ብዙ የደም መፍሰስና አለመረጋጋት ይኖራል ሆኖም ግን በኢሳያስ አባባል እንቅስቃሴውን ሲያደርጉ ቁጭ ብለን እንከታተለው ነበር ሲሉ ተደምጠዋል እነኛም ኩዴታ ሊያደርጉ የተነሰት የዜና ማእከኑን በመቆጣጠር የነበራችቸውን ጥያቄ ማለት ፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ሕገመንግስቱ ይሻሻል የሚል ተናግራእ ወደ ጦር ሰፈራቸው ትመለሱ ይልና የኩዳታው አነሳሽ የነበሩት አንዱ ራሱን ገደለ የተቀሩት ይቅርታ አሳስተውን ነው የሚል ነበር በቃል ምልልሱ የሰጡት፡ ኩዴታ ማለት የኳስ ግጥሚያ የሰፈር ልጆች ጥል ሳይሆን ሕገመንግስትን መጣስ በመሆኑ በይቅርታ የመታለፉ ጉዳይ አነጋጋሪ ሲሆን ከሁሉም የሚደንቀው ለጉዳዩ መግለጫ ለመስጠት ያልፈለግንው ሕዝቡን ላለ መረበሽ ነው ይላሉ በሌላው በኩል እኛ የምንሰራው የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻል ያለረፍት እየሰራን ወሬኞች በሩቅ ሆነው ይዋሻሉ ሕዝብን ይቆሰቁሳሉ እኛግን ስራችንን እየሰራን ነው ይሉና አንድ አስደናቂ የሆነ የአረብኝ ምሳሌ ተናግራዋል “ለልክዛብ ገድም ለልባብ” ውሸታምን እስከበር ሸኘው ማለት ነው ስለዚህም እንደ አቻቸው የትግል ጓድኛቸው መለሰ ድራማ መስራት ያውቁበታል ፡ እንዲሁም የሚቀናቀኑዋቸውን ለማጥፋት ምክንያቶች በመፍጠር እነኝህ መቶ የሚሆኑ መኮንኖች እነማን ናቸው ብሎ መጠየቅና ለማወቅ አስቸጋሪ አይሆንም ከበረሃ ጀምረው ያደጉ የትምሕርት እድል ያላገኙ ኢሳያስን እንደ ጣኦት የሚያመልኩ የሱ ታዛዞች በመሆናቸው ድራማውን እንዲተውኒዩ ተደርጋው እነኛም ተጠርጣሪዎች ወደቄራ መውረዳቸው የታወቀ በመሆኑ ፡ ለዚህ ምንም አይነት አሰሳና መረጃ አያስፈልግም የሚል እምነት አለኝ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule