• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ነገሪ ሌንጮ፣ አቦይ ስብሃት በሙስና መታሰራቸውን ይንገሩን!

July 26, 2017 07:41 am by Editor 1 Comment

የነጋዴዎች አድማ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። ገዥው ፓርቲ ከየአቅጣጫው በመወጠሩ – የችግሩን ትኩረት አቅጣጫ ማስቀየር አለበት። የተለመደ የፉገራ ካርዳቸውን መዘዝ አድርገው ለዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ሰጡዋቸው።

ኦቦ ነገሪ ሌንጮ 34 የመንግስት ባለስልጣናት እና ነጋዴዎች በሙስና ተጠርጥረው መታሰራቸውን ለመገናኛ ብዙሃን ትናንት ምሽት አብስረዋል። እነማን እንደታሰሩ ግን አልገለጹም። ታሳሪዎቹን ሊያውቁዋቸው ስለማይችሉ ሊገልጹ እንደማይችሉ ግልጽ ነው። እንደወትሮው ተጽፎ የተሰጣቸውን ከማንበብ ውጭ አማራጭ የላቸውም። የፕሮፌሰር መረራ ጉዲናን መታሰር እንደማንኛውም ተራ ሰው በዜና የሰሙት ነገሪ ሌንጮ ምን አፍ ኖሯቸው ስለ ባለስልጣናት መታሰር ይነግሩናል? ስራዎቼን ሁሉ በግምት ነው የምሰራው – መረጃ እንኳን አይሰጡኝም የሚሉ ጠቅላይ ሚኒስትርስ ምን አቅም ኖሯቸው ጉዳዩን ያስፈጽሙታል?

የሙስና ጉዳይ በየአመቱ ነው የሚነሳው። ችግር ሲመጣ እየጠበቁ ለአቅጣጫ ማስቀየርያ ይለቁብናል። አንዳንዴ በሙስና ታሳሪ ገጸ-ባህርያትን ይፈጥሩና አስቂኝ ድራማ ያሳዩናል። ሌላ ግዜ ደግሞ የንግድ ባላንጣዎቻቸውን ለመበቀል ይጠቀሙበታል። አንዳንዴም ለመታመን ሲሉ ተራ የመንግስት ሰራተኞችን እና ነጋዴዎችን ይዘው ያጉሯቸውና ግርግሩ ሲረሳሳ ደግሞ ይለቋቸዋል።

በእርግጥ የሙስና ተጠርጣሪዎችን ማሰር ቢያስቡ – መጀመርያ አቦይ ስብሀትን ወይንም አዜብ መስፍንን በማሰር ያሳዩን ነበር። ጸረ-ሙስናው ዘመቻ እውን ቢሆን ኖሮ የህወሃት የጦር አለቆች በሙሉ መኖርያቸው ቂሊንጦ በሆነ። የአቶ ስብሀት ነጋ ልጅ ተከስተ ስብሀት ነጋ እና እህት ቅዱሳን ነጋ ህልቕ መሳፍርት ንብረት ቢታገድ ነበር ጸረ-ሙስና ዘመቻ ተጀመረ ምንለው።

የሙሰኞች ንብረት ታገደ የምንለው የጄነራል ሳሞራ የኑስ፣ የሌ/ጄ ታደሰ ወረደ፣ የሌ/ጄ ገዛኢ አበራ፣ የሌ/ጄ ብርሃነ ነጋሽ፣ የሌ/ጄ ሳእረ መኮንን ቦሌ ላይ ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ ቤቶች ሲታገዱ ነው።

ሌ/ጄ ገዛኢ አበራ፣ ሌ/ጄ ብርሃነ ነጋሽ፣ ሌ/ጄ ሳእረ መኮንን፣ ሌ/ጄ አበባው ታደሰ፣ ሜ/ጄ አብርሃ ው/ገብርኤል፣ ሜ/ጄ ዮሃንስ ገ/መስቀል፣ ሜ/ጄ ስዮም ሃጎስ፣ ሜ/ጄ ሃየሎም አርአያ፣ ሜ/ጄ ገ/እግዚአብሄር መብራቱ፣ ብ/ጄ ታደሰ ጋውና፣ ብ/ጄ ተክላይ አሽብር፣ ብ/ጄ ፍስሃ ኪዳነ፣ ብ/ጄ ፓትሪስ፣ ብ/ጄ መስፍን አማረ፣ ብ/ጄ ምግበ ሃይለ፣ ብ/ጄ ሃለፎም ቸንቶ፣ ኮ/ል ታደስ ንጉሴ፣ ኮ/ል ጸሃየ መንጁስ በህዝብ ገንዘብ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ያሰሩዋቸው በሚሊዮኖች የሚገመቱ ቤቶች በወር ደሞዛቸው እንዳልሆነ ፖሊስና አቃቤ ህግ ሳያውቁት ቀርተው ነው?

እነ ብርሃኔ ገብረ ክርስቶስ፣ አባዲ ዘሙ፣ ስብሃት ነጋ፣ ሽመልስ ኪዳኔ፣ አርከበ እቁባይ፣ አባይ ጸሃዬ፣ ገብረ መድህን ገብረ ዮሃንስ፣ ደብረጽዮን ገብረ ሚካአኤል፣ ቴዎድሮስ ሃጎስ፣ ታደሰ ሃይሌ፣ ሰምሃል መለስ ዜናዊ ከባህር ማዶ ያከማቹት በቢሊዮን የሚቆጠር የህዝብ ገንዘብ እስቲ ይታገድ እና ነገሪ ሌንጮን እንመን።

ይህን መራራ ሃቅ የሚክድ የለም። ራሳቸውም የሚሉት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲፈሩ ሲቸሩ “ሙስና አለ – ማስረጃ የለም” ብለውናል። አቦይ ስብሃት ደግሞ በሰንደቅ ጋዜጣ አዳልጧቸው “መቶ ሚልዮን የሰረቁና ያስዘረፉ፤ 10ሺህ ብር የሰረቀውን ሲያገላብጡት ሲያስፈራሩት ይታያሉ” ብለው ነበር። የየሃገራቱን የሙስና መጠን ደረጃ በየአመቱ የሚዘግበው ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የተባለዉ ተቋም ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሙስና ከሚፈፀምባቸዉ ሃገራት አንዷ መሆኗን አመልክቷል። እንደ ተቋሙ ዘገባ ከሆነ ከኢትዮጵያ በህወሃት ዘመን ተዘርፎ የወጣው ገንዘብ 17 ቢሊየን ዶላር ይደርሳል። ጥናት ከተደረገባቸው 174 ሃገሮች መካከል ኢትዮጵያ 113ኛ ቦታን ይዛለች። ይህ ቁጥር መንግስታዊ ሙስናው ሃገሪቱን ምን ያህል እንደ መዥገር እመጠጠ መሆኑን ያሳየናል። ታቦ ኢምቤኪ የመሩት ሌላ ጥናት ደግሞ በአምስት ዓመታት ዉስጥ ብቻ ከኢትዮጵያ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ 10 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ወደ ዉጭ እንዲወጣ ተደርጓል።

በአንድ ወቅት በጸረ-ሙስና ኮሚሽን የባለስልጣናቱን ንብረት የመመዝገብ ደንብ ወጣና ስራውን ጀመረ። ብዙ የተወራለት ይህ ኮሚሽን ወደ ጀነራል ሳሞራ የኑስ ቤት ነበር ቀድሞ ያመራው። አይተ ሳሞራም የጸረ-ሙስናውን ቡድን አስቀምጦ “ስራችሁን አደንቃለሁ። ጥሩ ጅምር ነው። ግን ከላይ ጀምሩ” ብሎ ወደ አዜብ መስፍን መራቸው። ንብረት መዝጋቢዎቹ ወደ አዜብ ቤት ሳይደርሱ ግማሽ መንገድ ላይ እንደጠፉ ይነገራል። አዲዮስ ፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን!

የሲቪክ ማኅበራት በነፃነት መንቀሣቀስ በማይችሉበት፣ የፕሬስ ነጸነት በታፈነበትና የህግ የበላይነት በሌለበት ሃገር ሙስናን እናጠፋለን ማለት በህዝብ ሳይሆን በራስ ላይ መቀለድ ነው የሚሆነው። አላማው ከችግሩ አቅጣጫ ለማስቀየር ከሆነ ደግሞ ሌላ ካርታ መጠቀሙ የሚበጅ ይመስላል። ደጋግማችሁ በተባላ ካርታ አትጫወቱ።

ክንፉ አሰፋ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው! says

    July 30, 2017 06:03 pm at 6:03 pm

    “ከሚኒስተሮች ይልቅ ግንዘብ ላይ ከፈተኛ ሥልጣን ያላቸው ዳይሬከተሮቶች ናቸው” ጠ/ዓ/ሕግ አቶ ጌታቸው አምባዬ
    ” የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች ተደርገው የሚወሰዱት ሚኒስትሮችና ሚኒስትር ዴኤታዎች የፖለቲካ ተሿሚዎች ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ በዚህ ጉዳይ የሉበትም ባይባልም እንኳን፣ ዋነኛ ሥራቸው ፖለቲካዊ አቅጣጫ መስጠት ነው፡፡….(የፖለቲካ አቅጣጫ ማለት? ጠዋት ጠዋት ሥራ ሲገቡ የፖለቲካ ንቃት አብዮታዊ ዴሞክራሲ፤ አክራሪነት፡ጠባብነት፡ጽንፈኝነት በዴሞክራሲያዊ ብሔረትኝነት እየተቆላመጠ ኮርስ በእየሕንጻው ላይ ይሰጣል ማለት ነው!?)

    ___” ከፍተኛውን የመወሰን ድርሻ ያለው በዳይሬክተር ደረጃ ያለው ኃይል ነው፡፡ አጠቃላይ የገንዘብ እንቅስቃሴውንና በቢሮክራሲው ላይ የመወሰን ሥልጣን በእነዚህ ጫንቃ ላይ የወደቀ ነው፡፡” ታዲያ እነኝህ እየሰሩ ሌላው ጫንቃቸው ላይ ተቀምጦ የፖለቲካ ሹመኛ የሚሆነው በነጻ እያገለገለ ነው? ወይንስ ሌላው በሰራው እነሱ በታጋይ ሥም ተቀምጠው የራሳቸው ቡድን ካልተጠቀመና ከንግዱ ስላልተመሳጠረ እነኝህን በሙስና አስወግዶ የራሳቸውን የፖለቲካ አቀንቃኝ መረብ ለመዘርጋት የመንገድ ጠረጋ ነው ማለት ነው።አደለም እንዴ ዋሸን እንዴ?
    >» የህወአት/ኢህአዴግ ሙስና መር ኢኮኖሚ…ማኒፌስቶአዊ የልዩ ጥቅማጥቅም(እከክልኝ ልከክልህ…ብላና አባላ…ለአንተ ልጆች እስታዲየም ለነጻ አውጭህ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ…በመፈቃቀድና በመፈቃቀር መድፈር…ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት… አብዮታዊ ዲሞክራሲ…ብሶት የወለደው ስኳር ሲቅም ሌላው በምሬት ይሰደዳል፡ የባህር ገብቶ አዞ ይበላዋል፡ ከፎቅ ተፈጥፍጦ ይሞታል።…እንዲያው በዚህ የሙስና ድሪያ ላይ እንደ ደህንነቱና መከላከያው እንደኢኮኖሚው ዕድገት የብሔር ተዋፅዎው እንዴት ነው!?
    የስኳሩ አባት አባይ ጸሐዬ ሚስት ወ/ሮ ሳሌም ከበደ… እንደጂነዲን ሳዶ ሚስት ይሆንና ባለቤቷን ለህወአት ኢኮኖሚና ሥልጣን ግንባታ፡ ለአማራ ልጆች ውድቀት፡ ለሠራውና ለሠረሰረው ውለታ ሲባል በክብር ለትምህርት ውጭ ሀገር ልኮ እንዲከዳ መረዳት፡ ኢሳት ላይ እሳት እንዲጭር ማድረግ የተለመደ አሠራር ነው።
    __ በልዩ ጥቅማጥቅምና አድርባይነት ሲበሉና ሲያባሉ የነበሩ ባለውለታዎች የእንባ አሳዳሪነት ማዕረግ ተሰጥቶ እራቅ ብለው እንዲቆሙ ሲደረግ፡ ለህወአት ኢኮኖሚ ሞኖፖል ሲዋደቁ የነበሩ፡ ጥቁር ልብስና መነጽር ተከራይተው/ተውሰው ለታላቁ መሪ አልቃሽ የመለመሉ፡ ካኒቲራና ፎቶ ያባዙ ዛሬ አገልግሎታቸውን ጨርሰው ዶ/ር የለም፡ መሐንዲስ፡ አገልግል አስቋጥሮ አቧራ ላይ አንደባለለው!…እነኝህ ምልምል ተሞሳሟሾች ከባለቤቶቹ (ሚኒስተሮችና ሚኒስተረ ዴታዎች ) በፊት ወድቀው “ኢኮኖሚው፡ ዕድገቱ፡ ትምህርቱ፡ጤናው፡ ግድቡ፡ ሀዲዱ፡መብራቱ፡ ፈጠራው ህወሓት/ኢህአዴግ ከአፍሪካ አንደኛ፡ ከዓለም ሁለተኛ፡ እያሉ ትምህርታዊ ትንታኔና ቱልቱላ/ጥሩ’ንባ ሲነፉ/ሲረጩ አልነበረም!?
    __ ለመሆኑ ይቺ ገንዘብ ለዚህ ሁሉ አድርባይ ሲካፈል ምን አላት? ይህ ገንዘብ በሶስት ጡረተኛ ጄነራሎች ሥም ብቻ ያለ የገንዘብ መጠን አደለምን!? በአንድ ክልል ፵፭ ትላልቅ ነጋዴዎች ግብር ካልከፈሉ ፳ ተጠርናፊ ቢኖራቸው ፱፲፻ ተሞሳሟሽ ጠርንፈው ታላቁ መሪ ላይ ንፍጥና ልሃጫቸውን በማዝረከረክ የተካኑ በክልል የተፈለፈሉ ጥቅማጥቅመኞች ሕዝቤ የሚሉትን አጅዝበው/የበይ ተመልካች ሆኖ እነሱም ባንዳ(ሹምባሽ) በመሆናቸው ሥርዓት እንዳይለወጥ፡ ሀገር እንዲናወጥ፡ ወገናቸውን ያስበሉ ስንቶች ቃሚና ተጠቃሚ ናቸው?።
    ** “የአዲስ አበባን የንግድ ኢኮኖሚ የሚወስኑት ፹፭ ነጋዴዎች ናቸው” ተጠቅላዩ ሚ/ር መለስ ዜናዊ
    **”፻ ሚሊዮን ብር የወሰዱና የበሉ አውቃለሁ ግን አልነግራችሁም ” ” የራሳቸው የግል እሥር ቤት ያላቸው ነጋዴዎች አሉ” ኅይለማረያም ደስለኝ
    እዚህ እንዴት ሥማቸው የለም? ጭር ሲል ሊወጡ ነው? ይህ በብድርና በልመና የቆመ አብዮታዊ ገዢ/አውራ ፓርቲና መንግስት(!?)
    ” የሕንጻውን መሠረት ሳያወቁ ቅርንጫፍ ባንክ የሚከፍቱ” አለ ከያኒው.. አብዮት ልጇን ትበላለች ካላችሁ ግቡ እንያችሁ።

    Reply

Leave a Reply to በለው! Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule