• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አምባሳደሩ ወዳገራቸው መመለስ አለባቸው” የናይጄሪያ እንደራሴዎች

April 18, 2015 04:39 am by Editor 1 Comment

* “ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን” ቴድሮስ አድሃኖም

በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ አፍሪካውያን ላይ የተጀመረው ጥቃት ያስቆጣቸው የናይጄሪያ እንደራሴዎች በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት አምባሳደር ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ የሩዋንዳውን ፕሬዚዳንት በማስተናገድ የተጠመዱት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ በደቡብ አፍሪካ “የተፈጠረው ጊዜያዊ ችግር ነው ብለን እናምናለን” በማለት አስተያየት ሰጡ፡፡ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴድሮስ ከየቦታው ሃሳብ እየሰበሰብኩ ነው፤ “ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉ ድጋፍ እናደርጋለን” አሉ፡፡ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ግን የመመለስ ፍላጎት እንደሌላቸው ይናገራሉ፡፡

ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ የተነሳው አሰቃቂ ግድያና ዘረፋ ብዙዎችን እኤአ በ2008 የተከሰተውን እንዲያስታውሱ አድርጓቸዋል፡፡ በወቅቱ ከስድሳ በላይ አፍሪካውያን የተገደሉና የበርካታዎች ንብረት የተዘረፈ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ሰሞኑን በተነሳው ሁከት ሶስት ኢትዮጵያውያን መሞታቸውንና አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ከዚያው የወጡ መረጃዎች ቢጠቁሙም የኢህአዴግ ባለሥልጣናት ግን የሞተው አንድ ብቻ ነው ማለታቸውን ኢቲቪ ዘግቧል፡፡

ከኢትዮጵያውያኑ ሌላ ዜጎቿ እንደሞቱባት የምትጠቀሰው ናይጄሪያ በድርጊቱ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጅቶች እያደረገች መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የናይጄሪያ እንደራሴዎች በደቡብ አፍሪካ ላይ የከረረ እርምጃ እንዲወሰድ እየሞገቱ ነው፡፡ የናይጄሪያ ተወካዮች ምክርቤት በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ካደረገ በኋላ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት የናይጄሪያ አምባሳደር ወደ አገራቸው እንዲመጡ አጽድቋል፡፡

sa2sa4በተለያዩ ድረገጾች ላይ የተነበበው ይህ ዜና እንደሚያስረዳው የተከበሩት እንደራሴዎች እጅግ በጋለና አገር ፍቅር ስሜት በወገኖቻቸው እንዲሁም በአፍሪካውያን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አውግዘዋል፤ ኮንነዋል፡፡ የኤዶ ግዛት እንደራሴ ረቂቅ ሕጉ ላይ የናይጄሪያ መንግሥት ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲያቋርጥ የማሻሻያ ሃሳብ አቅርበው ነበር፡፡ ሃሳቡን የዴልታው እንደራሴ በአጽንዖት የደገፉ ቢሆንም ውሳኔ ድምጽ ላይ ሲደርስ አምባሳደሩ ወደ አገራቸው በአስቸኳይ እንዲጠሩ የሚለው ሲያልፍ ማሻሻያው ግን በቂ ድምጽ ሳያገኝ ቀርቷል፡፡ ማሻሻያውን የደገፉ እንደራሴዎች በጉዳዩ ላይ እንደሚሰሩ የተሰማ ቢሆንም አምባሳደሩን ወዳገራቸው ማስመጣቱ በፍጥነት እንዲፈጸም ፕሬዚዳንት ጉድላክ ዮናታን የጉዳዩን አስቸኳይነት ለፕሬዚዳንት ያዕቆብ ዙማ እንዲገልጹ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በኢትዮጵያ ጉብኝት የሚያደርጉትን የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት እያስተናገዱ ያሉት ሃይለማርያም ደሳለኝ በደቡብ አፍሪካ የደረሰውን በተመለከተ በእንግሊዝኛ ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡ ጠ/ሚ/ሩ ታሪክን የዘነጋ በሚመስል ለስላሳ አነጋገር “ደቡብ አፍሪካ ከቅኝ አገዛዝም ሆነ ከአፓርታይድ አገዛዝ ነጻ እንድትወጣ ድጋፍ መስጠታችን ይሰማናል” በማለት አጭሩን ንግግራቸውን አሰምተዋል፡፡ ሲቀጥሉም “አፍሪካውያን በፈለጉበት መኖር” እንደሚችሉ ከገለጹ በኋላ “አሁን የተፈጠረው ጊዜያዊ ክስተት ነው ብለን እናምናለን፤ የደቡብ አፍሪካ መንግሥትና ፓርቲ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን” በማለት ወደ ግብዣቸው ተመልሰዋል፡፡

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት አራተኛዋ ባለሥልጣን የሆኑትን የበታች ጸሃፊ ዌንዲ ሸርማንን በማስተናገድ የተጠመዱት ቴድሮስ አድሃኖም በፌስቡክ በለቀቁት አጭር መልዕክት “በደቡብ አፍሪቃ ከሚገኙ አንዳንድ ወገኖች” ጋር በስልክ እየተነጋገሩ መሆናቸውን እና ምን መደረግ እንዳለበት ከየቦታው እስካሁን ሃሳብ በመሰብሰብ ሥራ ላይ መጠመዳቸውንsouth-africa-foreigners የሚገልጽ እንደምታ ያለው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ “ወደ አገራቸው መመለስ የሚፈልጉትን” ለመደገፍ መዘጋጀታቸውን በዚሁ መልዕክት ገልጸዋል፡፡

ነዋሪዎችን ከየመኖሪያቸው በማፈናቀል፤ መኖሪያ በማሳጣት እና በግዳጅ ባልፈለጉበት ቦታ በማስፈር የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸሙ በተለያዩ ዘገባዎች በማስረጃ የሚነገርለት ኢህአዴግ ወደ አገር ለመመለስ ለሚፈልጉ ዝግጅቱ ማድረጉን ቢገልጽም በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ግን ሁኔታው አስፈሪ ቢሆንም ወደ አገራቸው መመለስ እንደማይፈልጉ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ አንዳንዶችም “ከአገራችን የወጣነው የኢኮኖሚ ጥገኝነት አስገድዶን ብቻ አይደለም፤ የመኖር ኅልውናችን አደጋ ላይ በመውደቁም ጭምር ነው” ሲሉ ተሰምተዋል፡፡

ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንዳሉት “ደቡብ አፍሪካውያን ኢትዮጵያዊ ስለተባልን አገር ያለን መስሏቸው ከአገራቸው እንድንወጣ ይነግሩናል፤ በህይወት እያለን ወደ ኢትዮጵያ ሄደን በደኅንነት መኖር ስለማንችል እኮ ነው ስንሞት አስከሬን የምንልከው፤ ይህንን ግን የተረዱት አይመስለኝም” በማለት ሃሳባቸውን ተናግረዋል፡፡

sa9እኤአ በ2000 መጀመሪያዎች አካባቢ በአገራቸው የሚኖሩ ነጭ ሰፋሪዎችን ያባረሩት የዚምባብዌው ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ በዚሁ የደቡብ አፍሪካ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጎቿ ደቡብ አፍሪካ እንደሚኖሩ የሚነገርላት ዚምባብዌ የዜጎቿን ጉዳይ ቀዳሚው ስፍራ የሰጠችው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በተለይ ግን ሙጋቤ ጉዳዩን አስመልክቶ በላኩት መልዕክት እንዲህ በማለት በደቡብ አፍሪካውያን ላይ ተሳልቀዋል፤ ዘልፈዋቸውማል፡፡

“ደቡብ አፍሪካውያን አንድ ነጭ በህይወት እያለ በጥፊ ለመምታት ሙከራ እንኳን ስለማያደርጉ (ስለሚፈሩ) ነጭ ሲሞት ሃውልቱን ይደበድባሉ፤ ነገር ግን አንድ ጥቁር የሌላ አገር ዜጋ በመሆኑ ብቻ በድንጋይ ወግረው ይገድላሉ፡፡”


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. seba says

    April 18, 2015 08:01 am at 8:01 am

    Is Jonathan still there ?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule