• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አምባሳደሩ ወዳገራቸው መመለስ አለባቸው” የናይጄሪያ እንደራሴዎች

April 18, 2015 04:39 am by Editor 1 Comment

* “ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉት ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ነን” ቴድሮስ አድሃኖም

በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ አፍሪካውያን ላይ የተጀመረው ጥቃት ያስቆጣቸው የናይጄሪያ እንደራሴዎች በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት አምባሳደር ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላለፉ፡፡ የሩዋንዳውን ፕሬዚዳንት በማስተናገድ የተጠመዱት ጠ/ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ በደቡብ አፍሪካ “የተፈጠረው ጊዜያዊ ችግር ነው ብለን እናምናለን” በማለት አስተያየት ሰጡ፡፡ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴድሮስ ከየቦታው ሃሳብ እየሰበሰብኩ ነው፤ “ወደ አገራቸው መመለስ ለሚፈልጉ ድጋፍ እናደርጋለን” አሉ፡፡ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ግን የመመለስ ፍላጎት እንደሌላቸው ይናገራሉ፡፡

ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ የተነሳው አሰቃቂ ግድያና ዘረፋ ብዙዎችን እኤአ በ2008 የተከሰተውን እንዲያስታውሱ አድርጓቸዋል፡፡ በወቅቱ ከስድሳ በላይ አፍሪካውያን የተገደሉና የበርካታዎች ንብረት የተዘረፈ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ሰሞኑን በተነሳው ሁከት ሶስት ኢትዮጵያውያን መሞታቸውንና አስከሬናቸውን ወደ ኢትዮጵያ መላኩን ከዚያው የወጡ መረጃዎች ቢጠቁሙም የኢህአዴግ ባለሥልጣናት ግን የሞተው አንድ ብቻ ነው ማለታቸውን ኢቲቪ ዘግቧል፡፡

ከኢትዮጵያውያኑ ሌላ ዜጎቿ እንደሞቱባት የምትጠቀሰው ናይጄሪያ በድርጊቱ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጅቶች እያደረገች መሆኑ ተሰምቷል፡፡ የናይጄሪያ እንደራሴዎች በደቡብ አፍሪካ ላይ የከረረ እርምጃ እንዲወሰድ እየሞገቱ ነው፡፡ የናይጄሪያ ተወካዮች ምክርቤት በጉዳዩ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ካደረገ በኋላ በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት የናይጄሪያ አምባሳደር ወደ አገራቸው እንዲመጡ አጽድቋል፡፡

sa2sa4በተለያዩ ድረገጾች ላይ የተነበበው ይህ ዜና እንደሚያስረዳው የተከበሩት እንደራሴዎች እጅግ በጋለና አገር ፍቅር ስሜት በወገኖቻቸው እንዲሁም በአፍሪካውያን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አውግዘዋል፤ ኮንነዋል፡፡ የኤዶ ግዛት እንደራሴ ረቂቅ ሕጉ ላይ የናይጄሪያ መንግሥት ከደቡብ አፍሪካ ጋር ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዲያቋርጥ የማሻሻያ ሃሳብ አቅርበው ነበር፡፡ ሃሳቡን የዴልታው እንደራሴ በአጽንዖት የደገፉ ቢሆንም ውሳኔ ድምጽ ላይ ሲደርስ አምባሳደሩ ወደ አገራቸው በአስቸኳይ እንዲጠሩ የሚለው ሲያልፍ ማሻሻያው ግን በቂ ድምጽ ሳያገኝ ቀርቷል፡፡ ማሻሻያውን የደገፉ እንደራሴዎች በጉዳዩ ላይ እንደሚሰሩ የተሰማ ቢሆንም አምባሳደሩን ወዳገራቸው ማስመጣቱ በፍጥነት እንዲፈጸም ፕሬዚዳንት ጉድላክ ዮናታን የጉዳዩን አስቸኳይነት ለፕሬዚዳንት ያዕቆብ ዙማ እንዲገልጹ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

በኢትዮጵያ ጉብኝት የሚያደርጉትን የሩዋንዳ ፕሬዚዳንት እያስተናገዱ ያሉት ሃይለማርያም ደሳለኝ በደቡብ አፍሪካ የደረሰውን በተመለከተ በእንግሊዝኛ ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡ ጠ/ሚ/ሩ ታሪክን የዘነጋ በሚመስል ለስላሳ አነጋገር “ደቡብ አፍሪካ ከቅኝ አገዛዝም ሆነ ከአፓርታይድ አገዛዝ ነጻ እንድትወጣ ድጋፍ መስጠታችን ይሰማናል” በማለት አጭሩን ንግግራቸውን አሰምተዋል፡፡ ሲቀጥሉም “አፍሪካውያን በፈለጉበት መኖር” እንደሚችሉ ከገለጹ በኋላ “አሁን የተፈጠረው ጊዜያዊ ክስተት ነው ብለን እናምናለን፤ የደቡብ አፍሪካ መንግሥትና ፓርቲ ተገቢውን እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን” በማለት ወደ ግብዣቸው ተመልሰዋል፡፡

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት አራተኛዋ ባለሥልጣን የሆኑትን የበታች ጸሃፊ ዌንዲ ሸርማንን በማስተናገድ የተጠመዱት ቴድሮስ አድሃኖም በፌስቡክ በለቀቁት አጭር መልዕክት “በደቡብ አፍሪቃ ከሚገኙ አንዳንድ ወገኖች” ጋር በስልክ እየተነጋገሩ መሆናቸውን እና ምን መደረግ እንዳለበት ከየቦታው እስካሁን ሃሳብ በመሰብሰብ ሥራ ላይ መጠመዳቸውንsouth-africa-foreigners የሚገልጽ እንደምታ ያለው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ “ወደ አገራቸው መመለስ የሚፈልጉትን” ለመደገፍ መዘጋጀታቸውን በዚሁ መልዕክት ገልጸዋል፡፡

ነዋሪዎችን ከየመኖሪያቸው በማፈናቀል፤ መኖሪያ በማሳጣት እና በግዳጅ ባልፈለጉበት ቦታ በማስፈር የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸሙ በተለያዩ ዘገባዎች በማስረጃ የሚነገርለት ኢህአዴግ ወደ አገር ለመመለስ ለሚፈልጉ ዝግጅቱ ማድረጉን ቢገልጽም በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ግን ሁኔታው አስፈሪ ቢሆንም ወደ አገራቸው መመለስ እንደማይፈልጉ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ አንዳንዶችም “ከአገራችን የወጣነው የኢኮኖሚ ጥገኝነት አስገድዶን ብቻ አይደለም፤ የመኖር ኅልውናችን አደጋ ላይ በመውደቁም ጭምር ነው” ሲሉ ተሰምተዋል፡፡

ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንዳሉት “ደቡብ አፍሪካውያን ኢትዮጵያዊ ስለተባልን አገር ያለን መስሏቸው ከአገራቸው እንድንወጣ ይነግሩናል፤ በህይወት እያለን ወደ ኢትዮጵያ ሄደን በደኅንነት መኖር ስለማንችል እኮ ነው ስንሞት አስከሬን የምንልከው፤ ይህንን ግን የተረዱት አይመስለኝም” በማለት ሃሳባቸውን ተናግረዋል፡፡

sa9እኤአ በ2000 መጀመሪያዎች አካባቢ በአገራቸው የሚኖሩ ነጭ ሰፋሪዎችን ያባረሩት የዚምባብዌው ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ በዚሁ የደቡብ አፍሪካ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጎቿ ደቡብ አፍሪካ እንደሚኖሩ የሚነገርላት ዚምባብዌ የዜጎቿን ጉዳይ ቀዳሚው ስፍራ የሰጠችው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ በተለይ ግን ሙጋቤ ጉዳዩን አስመልክቶ በላኩት መልዕክት እንዲህ በማለት በደቡብ አፍሪካውያን ላይ ተሳልቀዋል፤ ዘልፈዋቸውማል፡፡

“ደቡብ አፍሪካውያን አንድ ነጭ በህይወት እያለ በጥፊ ለመምታት ሙከራ እንኳን ስለማያደርጉ (ስለሚፈሩ) ነጭ ሲሞት ሃውልቱን ይደበድባሉ፤ ነገር ግን አንድ ጥቁር የሌላ አገር ዜጋ በመሆኑ ብቻ በድንጋይ ወግረው ይገድላሉ፡፡”


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. seba says

    April 18, 2015 08:01 am at 8:01 am

    Is Jonathan still there ?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule